" ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል "- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ አሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ሦስት ወራት ለክረምት ዝግጅት ሲያከናውን የቆያቸውን ስራዎች በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።
አገልግሎቱ በከተማዋ ለሚያጋጥም የሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ብሎ የለያቸውን የመስመሮች ከዛፍ ጋር የሚፈጥሩት ንክኪ እና የረገቡ መስመሮች ላይ የተለያዩ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አሳውቋል።
ተቋሙ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል ነው ያለው።
ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ካላቸው ግኝቶች ውስጥም ተቋሙ መፍታት የቻለው 56 በመቶዎቹን ብቻ ነው።
የአገልግሎቱ የኔትወርክ ኢንፍራስትራክቸር እና ኮርፖሬሽን ኤክሰለንስ ዳይሬክተር አቶ ፈሪድ አብዱሰላም ምን አሉ ?
" በስታንዳርዱ መሰረት ሽቦዎች እርስ በእርስ ሊኖራቸው የሚገባው ርቀት ከ 40-60 CM ፣ ከግራ እና ከቀኝ ካሉ ህንጻዎች እና ዛፎች 3 ሜትር እንዲሁም ከመሬት ያለው ከፍታ 5.5 ሜትር ከፍ ማለት የሚጠበቅባቸው ቢሆንም ይህ ሳይሆን በመቅረቱ ብልሽት እና አልፎ አልፎም አደጋ እያጋጠመ ነው።
ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ 973 በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል።
ከተገኘው ግኝት አብዛኛው ወይም 30 በመቶ የሚሆነው የ ሃይል መቆራረጥ ምክንያት ዛፎች ናቸው።
በመዲናዋ 7,277 የሚሆኑ መስመር ውስጥ የገቡ እና ከ ኤሌክትሪክ መስመር 3 ሜትር መራቅ ያለባቸው ዛፎች የተገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 5 ሺ 585 የሚሆኑትን የማጽዳት ስራ ተሰርቷል።
ያረጁ እና መቀየር የሚያስፈልጋቸው የኤሌክትሪክ ገመድ ተሸካሚ ፖሎች ቁጥር ከ 6 ሺ 367 በላይ ናቸው እዚህም ላይ ስራዎች ተሰርተዋል ይህም ለ ሃይል መቆራረጥ 25 በመቶ ምክንያት ነው።
በተጨማሪም 2 ሺ 425 ከግንባታዎችና እርስ በእርስ የተቀራረቡ መሥመሮች፣ 6 ሺ 298 የረገቡ እና የተለያዩ የመስመር ችግር ያለባቸው ሆነው ተገኝተዋል።
ከ 25 ሺ ግኝቶች ውስጥ 56 በመቶ የሚሆነውን ችግር ፈተናል።
በከተማዋ 10 ሺ 498 ትራንስፎርመሮች ላይ በተደረገ ምርምራ መጠነኛ ችግርች አግኝተንባቸዋል ለዚህም መፍትሄ በመስጠት ላይ እንገኛለን።
ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል።
የሃይል መቆራረጥ መንስኤዎች ለስራ በሚል የሚቋረጡ ፣በብልሽት እና በሃይል አቅራቢው በኩል የሚያጋጥሙ ችግሮች ተጨማሪ ምክንያት ናቸው " ብለዋል።
ተቋሙ 20 ሚሊየን ብር በመመደብ ከነገ ጀምሮ 100 ሺ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ሦስት ወራት ለክረምት ዝግጅት ሲያከናውን የቆያቸውን ስራዎች በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።
አገልግሎቱ በከተማዋ ለሚያጋጥም የሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ብሎ የለያቸውን የመስመሮች ከዛፍ ጋር የሚፈጥሩት ንክኪ እና የረገቡ መስመሮች ላይ የተለያዩ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አሳውቋል።
ተቋሙ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል ነው ያለው።
ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ካላቸው ግኝቶች ውስጥም ተቋሙ መፍታት የቻለው 56 በመቶዎቹን ብቻ ነው።
የአገልግሎቱ የኔትወርክ ኢንፍራስትራክቸር እና ኮርፖሬሽን ኤክሰለንስ ዳይሬክተር አቶ ፈሪድ አብዱሰላም ምን አሉ ?
" በስታንዳርዱ መሰረት ሽቦዎች እርስ በእርስ ሊኖራቸው የሚገባው ርቀት ከ 40-60 CM ፣ ከግራ እና ከቀኝ ካሉ ህንጻዎች እና ዛፎች 3 ሜትር እንዲሁም ከመሬት ያለው ከፍታ 5.5 ሜትር ከፍ ማለት የሚጠበቅባቸው ቢሆንም ይህ ሳይሆን በመቅረቱ ብልሽት እና አልፎ አልፎም አደጋ እያጋጠመ ነው።
ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ 973 በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል።
ከተገኘው ግኝት አብዛኛው ወይም 30 በመቶ የሚሆነው የ ሃይል መቆራረጥ ምክንያት ዛፎች ናቸው።
በመዲናዋ 7,277 የሚሆኑ መስመር ውስጥ የገቡ እና ከ ኤሌክትሪክ መስመር 3 ሜትር መራቅ ያለባቸው ዛፎች የተገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 5 ሺ 585 የሚሆኑትን የማጽዳት ስራ ተሰርቷል።
ያረጁ እና መቀየር የሚያስፈልጋቸው የኤሌክትሪክ ገመድ ተሸካሚ ፖሎች ቁጥር ከ 6 ሺ 367 በላይ ናቸው እዚህም ላይ ስራዎች ተሰርተዋል ይህም ለ ሃይል መቆራረጥ 25 በመቶ ምክንያት ነው።
በተጨማሪም 2 ሺ 425 ከግንባታዎችና እርስ በእርስ የተቀራረቡ መሥመሮች፣ 6 ሺ 298 የረገቡ እና የተለያዩ የመስመር ችግር ያለባቸው ሆነው ተገኝተዋል።
ከ 25 ሺ ግኝቶች ውስጥ 56 በመቶ የሚሆነውን ችግር ፈተናል።
በከተማዋ 10 ሺ 498 ትራንስፎርመሮች ላይ በተደረገ ምርምራ መጠነኛ ችግርች አግኝተንባቸዋል ለዚህም መፍትሄ በመስጠት ላይ እንገኛለን።
ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል።
የሃይል መቆራረጥ መንስኤዎች ለስራ በሚል የሚቋረጡ ፣በብልሽት እና በሃይል አቅራቢው በኩል የሚያጋጥሙ ችግሮች ተጨማሪ ምክንያት ናቸው " ብለዋል።
ተቋሙ 20 ሚሊየን ብር በመመደብ ከነገ ጀምሮ 100 ሺ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Ethiopia🇪🇹
የ1 ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት በኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ መካከል ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ይህ የድጋፍ ስምምነት የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ ይውላል ብሏል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ነው የተፈራረሙት።
Via Ministry of Finance
@tikvahethiopia
የ1 ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት በኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ መካከል ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ይህ የድጋፍ ስምምነት የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ ይውላል ብሏል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ነው የተፈራረሙት።
Via Ministry of Finance
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia 🇪🇹 #GERD 🇪🇹 " መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! " የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ? " ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን። ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው…
#GERD🇪🇹 💪
የግብፅ ምሁራን፣ ባለስልጣናትና ሚዲያዎች የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ስራ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ስለ ግድቡ ተነግረው የማያልቁ እጅግ በርካታ መጥፎና አሉታዊ ነገሮችን ሲያስወሩ ቆይተዋል።
ይኸው አሁንም በዚሁ እኩይ በሆነው ድርጊታቸው ቀጥለዋል።
በየጊዜው አዳዲስ ሀሰተኛ ወሬዎችን እየፈበረኩ ያሰራጫሉ።
በቅርቡ ከግድቡ ብዙ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እያለ የግብፅ ሰዎችና ሚዲያዎቻቸው " ግድቡ በመሬት መንቀጥቀጡ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብቷል ፤ የከፋ አደጋ ሊደርስበት ነው ፤ የመሬት መንቀጥቀጡ ግድቡን ያፈርሰው ነው ፤ ሊያወድመው ነው " የሚሉ ፍጹም የፈጠራ ወሬዎችን ለዓለም ህዝብ ሲያሰራጩ ከርመዋል።
ግን አንዳችም የተፈጠረ ነገር የለም ፤ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥም ቆመ።
አሁን ደግሞ " የግድቡ ተርባይን ተበላሽቷል ፤ ሱዳን ካርቱም በግድቡ ምክንያት በጎርፍ ልትጥለቀለቅ ነው " የሚል የፈጠራ ወሬ ይዘው መጥተዋል።
ይህንን ወሬያቸውንም በሚዲያ እያሰራጩት ይገኛሉ።
ሀገሪቱ ግብፅ የግድቡ ስራ ገና ከመጀመሩ አንስቶ እንዲስተጓጎል ፣ እንዲደናቀፍ ያልፈነቀለችው ድንጋይ ፤ ያሞከረችው ሙከራ፣ ያልጠናችበት ደጅ አልነበረም። ያም ሆኖ ግን ምንም አልተሳካላትም።
የኢትዮጵያውያን የህይወት ፣ የደም እና የላብ ዋጋ የተከፈለበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደርሶ በመጪው መስከረም ወር 2018 ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የግብፅ ምሁራን፣ ባለስልጣናትና ሚዲያዎች የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ስራ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ስለ ግድቡ ተነግረው የማያልቁ እጅግ በርካታ መጥፎና አሉታዊ ነገሮችን ሲያስወሩ ቆይተዋል።
ይኸው አሁንም በዚሁ እኩይ በሆነው ድርጊታቸው ቀጥለዋል።
በየጊዜው አዳዲስ ሀሰተኛ ወሬዎችን እየፈበረኩ ያሰራጫሉ።
በቅርቡ ከግድቡ ብዙ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እያለ የግብፅ ሰዎችና ሚዲያዎቻቸው " ግድቡ በመሬት መንቀጥቀጡ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብቷል ፤ የከፋ አደጋ ሊደርስበት ነው ፤ የመሬት መንቀጥቀጡ ግድቡን ያፈርሰው ነው ፤ ሊያወድመው ነው " የሚሉ ፍጹም የፈጠራ ወሬዎችን ለዓለም ህዝብ ሲያሰራጩ ከርመዋል።
ግን አንዳችም የተፈጠረ ነገር የለም ፤ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥም ቆመ።
አሁን ደግሞ " የግድቡ ተርባይን ተበላሽቷል ፤ ሱዳን ካርቱም በግድቡ ምክንያት በጎርፍ ልትጥለቀለቅ ነው " የሚል የፈጠራ ወሬ ይዘው መጥተዋል።
ይህንን ወሬያቸውንም በሚዲያ እያሰራጩት ይገኛሉ።
ሀገሪቱ ግብፅ የግድቡ ስራ ገና ከመጀመሩ አንስቶ እንዲስተጓጎል ፣ እንዲደናቀፍ ያልፈነቀለችው ድንጋይ ፤ ያሞከረችው ሙከራ፣ ያልጠናችበት ደጅ አልነበረም። ያም ሆኖ ግን ምንም አልተሳካላትም።
የኢትዮጵያውያን የህይወት ፣ የደም እና የላብ ዋጋ የተከፈለበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደርሶ በመጪው መስከረም ወር 2018 ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ሂጅራባንክ
ሂጅራ ባንክ በ2024/25 የበጀት አመት ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ አስመዘገበ።
ሂጅራ ባንክ ሦስተኛ ዓመት የእድገት ስትራቴጂ (Growth Strategy) በመተግበር ላይ የሚገኝ ሲሆን 2024/25 በጀት ዓመት "ስኬታማ ውጤት በማግኘት አዲስ ምዕራፍ የከፈተበት" ነው ሲል ገልጿል።
ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ (Total Income) ማስመዝገቡን ሲገልጽ፥ ከባለፈው ዓመት ጠቅላላ ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ 148.85% በመቶ እድገት አሳይቷል።
ከ840 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን የገለጸው ሂጅራ ባንክ ይህም ውጤት ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 740% ጭማሪ ማስመዝገቡንና በዚሁ መሰረትም የባንኩ ጠቅላላ ROE 40% መድረስ መቻሉን ገልጿል።
የባንኩ ጠቅላላ ሀብትም በከፍተኛ ደረጃ በማደግ በ2024/25 የበጀት አመት ከ15 ቢሊዮን ብር አልፏል፤ ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 95.37% ጭማሪ አሳይቷል።
እንዲሁም የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ወደ 12 ቢሊዮን ብር በማሳደግ 91.4%በመቶ ስኬታማ የእድገት ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጿል።
ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ 40 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱን ሲገልጽ፥ ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 304.5% በመቶ ጭማሪ ማስመዝገብ ችሏል።
ባንኩ የማክሮ ኢኮኖሚ ነባራዊ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ተደራሽነቱን በማስፋት 135 ቅርንጫፎችን መክፈቱን የገለጸ ሲሆን በ2024/25 የበጀት አመት 35 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉን አስታውቋል።
የደንበኞችን ብዛት በተመለከተ አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት ጠቅላላ የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 931,148 ሲያሳድግ፥ ይህም ካለፈው ዓመት የደንበኞች ብዛት አንጻር 69.4%በመቶ የደንበኞች ጭማሪን ማሳየት ችሏል ብሏል።
ከዲጂታል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ የኦምኒ ፕላስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ተጠቃሚዎች ከ350 ሺህ በላይ መሆናቸውንና ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 141.86% እድገት ማሳየቱን ነው የገለጸው።
ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሀላል ፔይ ዋሌት ተጠቃሚዎች ከ811 ሺህ በላይ የደረሱ ሲሆን ባንኩ ከመሰረታዊ የባንክ አገልግሎቶች በተጨማሪ ያለ ማስያዣ የፋይናንስ አገልግሎት መጠቀም የሚያስችል ኢ-ሙራበሃ የፋይናንስ አገልግሎትን በዋሌት በማስጀመር ስኬታማ ዓመት ማሳለፉን አስታውቋል።
ከ20.9 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በዲጂታል በኩል ተንቀሳቅሷል ያለው ባንኩ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 198.60% ዕድገት ማስመዝገቡን አስታውቋል።
አጠቃላይ ከተደረገው የገንዘብ ዝውውር 34.52% በዲጂታል መንገድ ሲሆን ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 10.68% እድገት አሳይቷል።
ሂጅራ ባንክ በ2024/25 የበጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማስቀደም በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል፤ ከእነዚህም ውስጥ ማህበረሰቡን ከባንክ ተጠቃሚነት ወደ ባንክ ባለቤትነት ለማሸጋገር ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ ማከናወኑ ተጠቅሷል።
እንዲሁም "ሀላል ፋይናንሺያል ሊትረሲ ፕሮግራም" በሚል ስያሜ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ስለ ሀላል ፋይናንስ በማስተማርና ግንዛቤ በማስጨበጥ ላይ ሰፊ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።
ባንኩ ስራ ፈጣሪዎችን እና ታታሪ ወጣቶችን ለማበረታታት በማሰብ "ሲራራ አዋርድ" የተሰኘ የውድድር መድረክ በማዘጋጀት እና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ፣ ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ተቋማት እና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ሲያደርግም ቆይቷል።
ባንኩ፥ "ይህ ስኬታማ ውጤት የሂጅራ ባንክን ስትራቴጂክ አቅጣጫ፣ የደንበኞቻችን፣ የባለአክሲዮኖቻችን፣ የቦርድ ዳይሬክተሮቻችን፣ የሸሪዓ አማካሪዎቻችን፣ የማኔጅመንት አባላት እና የሰራተኞቻችን ዉጤት ነው።" ሲል ነው የገለጸው።
ካለፉት አመታት ካስመዘገበው ውጤት እጅጉን የጎላ ነው ሲል በገለጸው በዚህ ስኬት "በሀገሪቱ ከወለድ ነጻ ባንኪንግ ዘርፍ ያለውን ሰፊ እምቅ አቅም እና ዘላቂነት ዳግም ያረጋገጥንበት ዓመት ነው" ሲል አስታውቋል።
#HijraBank
https://www.tgoop.com/HijraBank
ሂጅራ ባንክ በ2024/25 የበጀት አመት ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ አስመዘገበ።
ሂጅራ ባንክ ሦስተኛ ዓመት የእድገት ስትራቴጂ (Growth Strategy) በመተግበር ላይ የሚገኝ ሲሆን 2024/25 በጀት ዓመት "ስኬታማ ውጤት በማግኘት አዲስ ምዕራፍ የከፈተበት" ነው ሲል ገልጿል።
ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ (Total Income) ማስመዝገቡን ሲገልጽ፥ ከባለፈው ዓመት ጠቅላላ ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ 148.85% በመቶ እድገት አሳይቷል።
ከ840 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን የገለጸው ሂጅራ ባንክ ይህም ውጤት ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 740% ጭማሪ ማስመዝገቡንና በዚሁ መሰረትም የባንኩ ጠቅላላ ROE 40% መድረስ መቻሉን ገልጿል።
የባንኩ ጠቅላላ ሀብትም በከፍተኛ ደረጃ በማደግ በ2024/25 የበጀት አመት ከ15 ቢሊዮን ብር አልፏል፤ ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 95.37% ጭማሪ አሳይቷል።
እንዲሁም የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ወደ 12 ቢሊዮን ብር በማሳደግ 91.4%በመቶ ስኬታማ የእድገት ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጿል።
ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ 40 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱን ሲገልጽ፥ ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 304.5% በመቶ ጭማሪ ማስመዝገብ ችሏል።
ባንኩ የማክሮ ኢኮኖሚ ነባራዊ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ተደራሽነቱን በማስፋት 135 ቅርንጫፎችን መክፈቱን የገለጸ ሲሆን በ2024/25 የበጀት አመት 35 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉን አስታውቋል።
የደንበኞችን ብዛት በተመለከተ አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት ጠቅላላ የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 931,148 ሲያሳድግ፥ ይህም ካለፈው ዓመት የደንበኞች ብዛት አንጻር 69.4%በመቶ የደንበኞች ጭማሪን ማሳየት ችሏል ብሏል።
ከዲጂታል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ የኦምኒ ፕላስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ተጠቃሚዎች ከ350 ሺህ በላይ መሆናቸውንና ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 141.86% እድገት ማሳየቱን ነው የገለጸው።
ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሀላል ፔይ ዋሌት ተጠቃሚዎች ከ811 ሺህ በላይ የደረሱ ሲሆን ባንኩ ከመሰረታዊ የባንክ አገልግሎቶች በተጨማሪ ያለ ማስያዣ የፋይናንስ አገልግሎት መጠቀም የሚያስችል ኢ-ሙራበሃ የፋይናንስ አገልግሎትን በዋሌት በማስጀመር ስኬታማ ዓመት ማሳለፉን አስታውቋል።
ከ20.9 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በዲጂታል በኩል ተንቀሳቅሷል ያለው ባንኩ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 198.60% ዕድገት ማስመዝገቡን አስታውቋል።
አጠቃላይ ከተደረገው የገንዘብ ዝውውር 34.52% በዲጂታል መንገድ ሲሆን ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 10.68% እድገት አሳይቷል።
ሂጅራ ባንክ በ2024/25 የበጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማስቀደም በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል፤ ከእነዚህም ውስጥ ማህበረሰቡን ከባንክ ተጠቃሚነት ወደ ባንክ ባለቤትነት ለማሸጋገር ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ ማከናወኑ ተጠቅሷል።
እንዲሁም "ሀላል ፋይናንሺያል ሊትረሲ ፕሮግራም" በሚል ስያሜ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ስለ ሀላል ፋይናንስ በማስተማርና ግንዛቤ በማስጨበጥ ላይ ሰፊ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።
ባንኩ ስራ ፈጣሪዎችን እና ታታሪ ወጣቶችን ለማበረታታት በማሰብ "ሲራራ አዋርድ" የተሰኘ የውድድር መድረክ በማዘጋጀት እና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ፣ ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ተቋማት እና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ሲያደርግም ቆይቷል።
ባንኩ፥ "ይህ ስኬታማ ውጤት የሂጅራ ባንክን ስትራቴጂክ አቅጣጫ፣ የደንበኞቻችን፣ የባለአክሲዮኖቻችን፣ የቦርድ ዳይሬክተሮቻችን፣ የሸሪዓ አማካሪዎቻችን፣ የማኔጅመንት አባላት እና የሰራተኞቻችን ዉጤት ነው።" ሲል ነው የገለጸው።
ካለፉት አመታት ካስመዘገበው ውጤት እጅጉን የጎላ ነው ሲል በገለጸው በዚህ ስኬት "በሀገሪቱ ከወለድ ነጻ ባንኪንግ ዘርፍ ያለውን ሰፊ እምቅ አቅም እና ዘላቂነት ዳግም ያረጋገጥንበት ዓመት ነው" ሲል አስታውቋል።
#HijraBank
https://www.tgoop.com/HijraBank
ዋሪት ፈርኒቸር
የፋይበር ትራሶች የመተንፈስ አቅም እና የአከርካሪ አጥንት ማስተካከልን
እና ማንኮራፋትን የመቀነስ አቅም አላቸው::
እንግዲያውስ በአንድ ቦታ ምቾት፣ ጤና እና ምርታማ ወደሚሆኑበት
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
*ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: 0911210706 / 07
https://web.facebook.com/WARYTZE
https://www.instagram.com/warytfurniture
https://www.tgoop.com/warytfurniture
https://www.tiktok.com/@warytzefurniture
የፋይበር ትራሶች የመተንፈስ አቅም እና የአከርካሪ አጥንት ማስተካከልን
እና ማንኮራፋትን የመቀነስ አቅም አላቸው::
እንግዲያውስ በአንድ ቦታ ምቾት፣ ጤና እና ምርታማ ወደሚሆኑበት
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
*ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: 0911210706 / 07
https://web.facebook.com/WARYTZE
https://www.instagram.com/warytfurniture
https://www.tgoop.com/warytfurniture
https://www.tiktok.com/@warytzefurniture
🔵🛜 የDSTV ተወዳጅ ቻናሎችን ከፋይበር ኢንተርኔት ጋር ያግኙ!!
በስማርት ቲቪዎ የዲ.ኤስ.ቲቪ ስትሪም መተግበሪያ በመረጡት ጥቅልና የዳታ ፍጥነት DSTVን በቤትዎ ፋይበር ያጣጥሙ።
🎬 #ጎጆ_ጥቅል ከ70 በላይ ተወዳጅ ቻናሎችን በወር ከ929 ብር ጀምሮ!
💁♂️ እስከ 26.5% በሚደርስ ቅናሽ የቀረቡትን የፋይበር ብሮድባንድ እና የዲ.ኤስ.ቲቪ ጥቅሎች ይግዙ፤ በአማራጭ ይዝናኑ።
ℹ️ ስማርት ላልሆኑ ቲቪዎች STB (Set-Top Box) ለማግኘትና አገልግሎቱን ለመጠቀም የአገልግሎት ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ!
👉 እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ይመልከቱ: https://youtu.be/5u0r_t7_WGA
#DSTV
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
በስማርት ቲቪዎ የዲ.ኤስ.ቲቪ ስትሪም መተግበሪያ በመረጡት ጥቅልና የዳታ ፍጥነት DSTVን በቤትዎ ፋይበር ያጣጥሙ።
🎬 #ጎጆ_ጥቅል ከ70 በላይ ተወዳጅ ቻናሎችን በወር ከ929 ብር ጀምሮ!
💁♂️ እስከ 26.5% በሚደርስ ቅናሽ የቀረቡትን የፋይበር ብሮድባንድ እና የዲ.ኤስ.ቲቪ ጥቅሎች ይግዙ፤ በአማራጭ ይዝናኑ።
ℹ️ ስማርት ላልሆኑ ቲቪዎች STB (Set-Top Box) ለማግኘትና አገልግሎቱን ለመጠቀም የአገልግሎት ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ!
👉 እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ይመልከቱ: https://youtu.be/5u0r_t7_WGA
#DSTV
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
“ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረነብን ነው” - የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎች
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቅርቡ በጀመረው አሰራር መሠረት በሕጋዊ መንገድ ወደ ውጩ ሀገር ለሥራ ለሚሄዱ ተጓዦች በግዴታ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የጉዞ ትኬት ካልገዛችሁ ለጉዞ የሚያስፈልጋቸው የማለፊያ ኪው አር ኮድ እንደማይሰጣቸውና ጉዟቸውን እንደማያጸድቅ መወሰኑን በውጪ ሀገር የሥሪ ስምራት የተሰማሩ ኤጀንሲዎች ተቃወሙ።
"የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የህጋዊ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረብን ነው" ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ "ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካዘጋጀው አወዛጋቢ ረቂቅ አዋጅ ጎን ለጎን ሰሞኑን ህጋዊ ኤጀንሲዎችን በተለያየ መንገድ ለምን ማዋከብና አሰራሮችን መለዋወጥ እንዳስፈለገው ግራ አጋብቶናል" ብለዋል።
የውሳኔውን ጉዳት ሲያስረዱም፣ "ከዚህ በፊት ስንገዛበት ከነበረው ትኬት ዋጋ እስከ 25 ሺሕ ብር ጭማሪ በሲስተሙ አለ፤ በቃ መቁረጥ የምትችለው በዛ ብቻ ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
“ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመለት ዋነኛ አላማ አንፃር ወደ ውጪ የጉዞ ትኬት ሽያጭ ውስጥ ከመግባቱ በተጨማሪ ዜጎች በፈለጉት ህጋዊ ቦታ ትኬት ገዝተው የመጓዝ መብታቸውን የሚገድብና የነጻ ገበያ መርህን በግልጽ የሚጣረስ ነው" ሲሉም ተቃውመዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ?
“ዋጋው እጅግ በጣም ንሮብናል፤ መናሩ ብቻ አይደለም፤ ከዚህ በፊት ትኬት ስንቆርጥ ብር ስለማናገኝ ከትኬት ኦፊሶች በብድር ነበር የምንቆርጠው፡፡ አሁን ግን ዋጋውም ጨምሮ ካሽ ብቻ ነው የምንቆርጠው፤ ይሄ ራሱ ሌላ የራስ ምታት ነው ለኛ፡፡
ገና ገንዘብ ባልተቀበልነው ሰው ላይ ነው እንድንከፍል እያስገደዱን ያሉት፡፡ ከትላንት ወዲያ የጸደቀ አዋጅ አለ፤ ግን ይሄን ነገር አዲሱ አዋጅም የድሮውም አያውቀውም ሙሉ ለሙሉ ከሕግ ውጪ ነው፡፡ በሕግ ያልተሰጠው ሥራ ውስጥ መግባቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቆ ሲሄድ ዋና ሥራውን መዘንጋት ይጀመራል፡፡
በአዋጅ የተሰጠውን የሠራተኞችን መብት የሚከታተል ሌቨር አታች ያልመደበ መስሪያ ቤት ነው ትኬት ካልቆረጥኩ ብሎ እየተሟሟተ ያለው፡፡ በሌላ በኩል ቢያንስ ተጨማሪ 60 ዶላር ትከፍላላችሁ እየተባልን ነው፡፡ ለማን ነው የምንከፍለው? ሲሉ ጠይቀዋል።
ታዲያ መፍትሄ ምንድን ነው ትላላችሁ?
“ባጭሩ ሲስተም ላይ ትኬት መቁረጥ የሚለው ነገር አስገዳጅ መሆኑ መቆም አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መሠረታዊ የሆነ ሥራ ሰርቶ ጨርሷል ብለን አናምንም፡፡ መሆን ካለበት የራሱን መሠረታዊ ሥራ ይስራ፡፡ ግን ትኬት እኔ ጋር መቆረጥ አለበት ካለ ኦፕሽናል ነው መሆን ያለበት፡፡ ኦፕሽናሊ ያስቀምጠው አወዳድረን ጥሩ ነገር ካገኘን እንሄዳለን፡፡
ግዴታ ግን ትኬት ካልቆረጣችሁ የሠራተኞች መውጫ ኪው አር አልሰጣችሁም ማለት ከጀመረ በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ መንግስት አስተዳዳር ነው እንጅ ንግድ ውስጥ አይገባም። ግን መስራት አለበት፤ ትኬት ቆረጣ መግባት አለበት ካሉ ኦፕሽናል በሆነ መልኩ ነው እንጅ ግዴታ በመስሪያ ቤቱ ካቆረጣችሁ መውጫ አንስጥም የሚሉ ከሆነ በጣም አደገኛ ነው” ብለዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ምላሽ የሚጠይቅ ይሆናል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቅርቡ በጀመረው አሰራር መሠረት በሕጋዊ መንገድ ወደ ውጩ ሀገር ለሥራ ለሚሄዱ ተጓዦች በግዴታ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የጉዞ ትኬት ካልገዛችሁ ለጉዞ የሚያስፈልጋቸው የማለፊያ ኪው አር ኮድ እንደማይሰጣቸውና ጉዟቸውን እንደማያጸድቅ መወሰኑን በውጪ ሀገር የሥሪ ስምራት የተሰማሩ ኤጀንሲዎች ተቃወሙ።
"የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የህጋዊ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረብን ነው" ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ "ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካዘጋጀው አወዛጋቢ ረቂቅ አዋጅ ጎን ለጎን ሰሞኑን ህጋዊ ኤጀንሲዎችን በተለያየ መንገድ ለምን ማዋከብና አሰራሮችን መለዋወጥ እንዳስፈለገው ግራ አጋብቶናል" ብለዋል።
የውሳኔውን ጉዳት ሲያስረዱም፣ "ከዚህ በፊት ስንገዛበት ከነበረው ትኬት ዋጋ እስከ 25 ሺሕ ብር ጭማሪ በሲስተሙ አለ፤ በቃ መቁረጥ የምትችለው በዛ ብቻ ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
“ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመለት ዋነኛ አላማ አንፃር ወደ ውጪ የጉዞ ትኬት ሽያጭ ውስጥ ከመግባቱ በተጨማሪ ዜጎች በፈለጉት ህጋዊ ቦታ ትኬት ገዝተው የመጓዝ መብታቸውን የሚገድብና የነጻ ገበያ መርህን በግልጽ የሚጣረስ ነው" ሲሉም ተቃውመዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ?
“ዋጋው እጅግ በጣም ንሮብናል፤ መናሩ ብቻ አይደለም፤ ከዚህ በፊት ትኬት ስንቆርጥ ብር ስለማናገኝ ከትኬት ኦፊሶች በብድር ነበር የምንቆርጠው፡፡ አሁን ግን ዋጋውም ጨምሮ ካሽ ብቻ ነው የምንቆርጠው፤ ይሄ ራሱ ሌላ የራስ ምታት ነው ለኛ፡፡
ገና ገንዘብ ባልተቀበልነው ሰው ላይ ነው እንድንከፍል እያስገደዱን ያሉት፡፡ ከትላንት ወዲያ የጸደቀ አዋጅ አለ፤ ግን ይሄን ነገር አዲሱ አዋጅም የድሮውም አያውቀውም ሙሉ ለሙሉ ከሕግ ውጪ ነው፡፡ በሕግ ያልተሰጠው ሥራ ውስጥ መግባቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቆ ሲሄድ ዋና ሥራውን መዘንጋት ይጀመራል፡፡
በአዋጅ የተሰጠውን የሠራተኞችን መብት የሚከታተል ሌቨር አታች ያልመደበ መስሪያ ቤት ነው ትኬት ካልቆረጥኩ ብሎ እየተሟሟተ ያለው፡፡ በሌላ በኩል ቢያንስ ተጨማሪ 60 ዶላር ትከፍላላችሁ እየተባልን ነው፡፡ ለማን ነው የምንከፍለው? ሲሉ ጠይቀዋል።
ታዲያ መፍትሄ ምንድን ነው ትላላችሁ?
“ባጭሩ ሲስተም ላይ ትኬት መቁረጥ የሚለው ነገር አስገዳጅ መሆኑ መቆም አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መሠረታዊ የሆነ ሥራ ሰርቶ ጨርሷል ብለን አናምንም፡፡ መሆን ካለበት የራሱን መሠረታዊ ሥራ ይስራ፡፡ ግን ትኬት እኔ ጋር መቆረጥ አለበት ካለ ኦፕሽናል ነው መሆን ያለበት፡፡ ኦፕሽናሊ ያስቀምጠው አወዳድረን ጥሩ ነገር ካገኘን እንሄዳለን፡፡
ግዴታ ግን ትኬት ካልቆረጣችሁ የሠራተኞች መውጫ ኪው አር አልሰጣችሁም ማለት ከጀመረ በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ መንግስት አስተዳዳር ነው እንጅ ንግድ ውስጥ አይገባም። ግን መስራት አለበት፤ ትኬት ቆረጣ መግባት አለበት ካሉ ኦፕሽናል በሆነ መልኩ ነው እንጅ ግዴታ በመስሪያ ቤቱ ካቆረጣችሁ መውጫ አንስጥም የሚሉ ከሆነ በጣም አደገኛ ነው” ብለዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ምላሽ የሚጠይቅ ይሆናል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል። ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል። " የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ…
#Ethiopia🇪🇹
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia🇪🇹
በግለሰቦች፣ በብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል " ስጋት፣ ግጭትን፣ ጥርጣሬን እና አለመተማመንን የሚፈጥር ድርጊት ፈጽሟል " ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምዝገባ እንዲሰርዝ ስልጣን የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ።
ቦርዱ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን " ህጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ያደናቀፈ " የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የመውሰድ ስልጣንም በአዋጅ ማሻሻያው ተሰጥቶታል።
ላለፉት አምስት ዓመታት በስራ ላይ የቆየውን " የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ " ያሻሻለው የህግ ረቂቅ ለፓርላማ ቀርቧል።
ዛሬ በአዋጅ ማሻሻያው ላይ የፓርላማ አባላት መታየት ያለባቸውን ጉዳዮች በጥቂቱ ካቀረቡ በኋላ በዝርዝር እንዲታይ ለምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርተውታል።
ያለምንም ተቃውሞ እና ድምጸ ተዐቅቦ ለቋሚ ኮሚቴ የተመራው ይህ የአዋጅ ማሻሻያ ከተዘጋጀባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስፈጸመው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የተስተዋሉ " የህግ ክፍተቶች " እንደሆነ የህግ ረቂቁን ለማብራራት በቀረበ ሰነድ ላይ ተጠቅሷል።
በዝርዝር ያንብቡ : https://ethiopiainsider.com/2025/16239/
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
በግለሰቦች፣ በብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል " ስጋት፣ ግጭትን፣ ጥርጣሬን እና አለመተማመንን የሚፈጥር ድርጊት ፈጽሟል " ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምዝገባ እንዲሰርዝ ስልጣን የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ።
ቦርዱ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን " ህጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ያደናቀፈ " የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የመውሰድ ስልጣንም በአዋጅ ማሻሻያው ተሰጥቶታል።
ላለፉት አምስት ዓመታት በስራ ላይ የቆየውን " የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ " ያሻሻለው የህግ ረቂቅ ለፓርላማ ቀርቧል።
ዛሬ በአዋጅ ማሻሻያው ላይ የፓርላማ አባላት መታየት ያለባቸውን ጉዳዮች በጥቂቱ ካቀረቡ በኋላ በዝርዝር እንዲታይ ለምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርተውታል።
ያለምንም ተቃውሞ እና ድምጸ ተዐቅቦ ለቋሚ ኮሚቴ የተመራው ይህ የአዋጅ ማሻሻያ ከተዘጋጀባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስፈጸመው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የተስተዋሉ " የህግ ክፍተቶች " እንደሆነ የህግ ረቂቁን ለማብራራት በቀረበ ሰነድ ላይ ተጠቅሷል።
በዝርዝር ያንብቡ : https://ethiopiainsider.com/2025/16239/
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#OFC
" በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ የምንወስነው እነዚህ መሠረታዊ ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታቸው ላይ የተመሰረተ ነው " - ኦፌኮ
የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የውጭ መረጃ አሰባሳቢ ልዑክ ጋር በዋና ፅ/ቤቱ መወያየቱን ገለጸ።
ፓርቲው ውይይቱ የነበረው በ2018 ዓ/ም የሚካሄደው 7ኛው አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምርጫ ላይ እንደሆነ አመልክቷል።
" ምርጫው ቁልፍ እና ወሳኝ የተባሉ ጥያቄዎችን አቅርቢያለሁ " ብሏል።
ኦፌኮ " ነጻ፣ ፍትሃዊ እና ተአማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲረጋገጥ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገባቸውን መሰረታዊ ጥያቄዎችን እንዲሁም የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀውስ አስመልክቶ ዝርዝር እና የማያዳግም ግምገማ አቅርበናል " ብሏል።
በውይይቱ ላይ እነማን ተገኙ ?
ኦፌኮን በመወከል ፦
- የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
- የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም ተገኝተዋል።
የተባበሩት መንግስታት ልዑካን ቡድን አራት አባላት የያዘ ሲሆን ፦
- በተመድ የአፍሪካ ህብረት ቢሮ (UNOAU) የምርጫ ድጋፍ ክፍል ዋና ኦፊሰር አኪንየሚ ኦ. አዴግባላን
- በኢትዮጵያ የተመድ የነዋሪ አስተባባሪ ጽ/ቤት የሰላምና ልማት አማካሪ ዶ/ር ዘቡሎን ሱይፎን ታክዋን እንዲሁም ሌሎች ሁለት ቁልቅ የተመድ ልዑካን አካትቷል።
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ምን አሉ ?
" ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ላይ መሳተፉ ሙሉ በሙሉ በመሠረታዊ እና በተጨባጭ ለውጦች ላይ የተመሰረተ ነው።
ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ቴክኒካዊ ሂደት ብቻ አይደለም፤ የዲሞክራሲያዊ ሂደት ውጤት ነው። ይህ ሂደት ዛሬ በኢትዮጵያ የለም። በጦርነት እና በፖለቲካ ስደት ውስጥ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማካሄድ አይቻልም። " ብለዋል።
ኦፌኮ፣ ተመድ ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖውን ተጠቅሞ እንዲያስፈጽም በማሳሰብ ለመንግስት የሚቀርቡ ዝርዝር ጥያቄዎችን አቅርቧል።
በኦፌኮ የቀረቡ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
➡️ በኦሮሚያና በመላ ኢትዮጲያ ሰላም ፣ በክልሉ ያለውን አውዳሚ ግጭት ለማስቆም በመንግስት ኃይሎች እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሰ) መካከል በአለም አቀፍ ታዛቢዎች የሚረጋገጥ አፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ።
➡️ ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች መፍታት፣ የኦፌኮ አባላትን፣ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ጨምሮ በመላ አገሪቱ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ።
➡️ በነጻነት የመንቀሳቀስ ዋስትና፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማስፈራራት፣ ወከባና እስራት እንዲቆም። ኦፌኮ የፓርቲ ጽ/ቤቶችን በነጻነት የመክፈትና የማንቀሳቀስ እንዲሁም ከሃገር ውስጥ አስተዳዳሪዎችና ከጸጥታ ኃይሎች ምንም አይነት ጣልቃ ገብነት ሳይኖር ህዝባዊ ስብሰባዎችን የማድረግ መብት እንዲከበርለት ጠይቋል።
በተጨማሪ፦
➡️ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልል የጸጥታ ኃይሎች አመራሮች በፖለቲካው ሂደት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ለመሆናቸው በይፋ ቃል የሚገቡበት እና ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ አካል የሚቋቋምበት ስምምነት እንዲፈረም።
➡️ ከምርጫ በፊት የሁሉም ፓርቲዎች ውይይት፣ በገዥው ፓርቲ እና በሁሉም ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግልጽ የሆነ የምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ለመስማማት የሚያስችል ይፋዊ ውይይት እንዲካሄድ።
➡️ የምርጫ ቦርድን እንደገና ማቋቋም፣ ገለልተኝነቱን ለማረጋገጥ ሁሉም ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚሳተፉበት ግልጽና አካታችነት ላይ በተመሰረተ ሂደት ኮሚሽነሮችን በመሾም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እንደገና እንዲዋቀር።
➡️ አሁን በስራ ላይ ያለውንና አሸናፊ ሁሉን የሚወስድበትን የአብላጫ ድምፅ የምርጫ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መልኩ መከለስ። ሁሉም ማህበረሰቦችና የፖለቲካ ቡድኖች በፓርላማ ውስጥ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራቸው ለማድረግ ወደ ተመጣጣኝ ውክልና (MMP) የምርጫ ሥርዓት እንዲሸጋገር።
➡️ ገዥው ፓርቲ በመገናኛ ብዙኃን ላይ ያለውን የበላይነት በማስቀረት ሁሉም የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግስት ሚዲያዎች (EBC, OBN የመሳሰሉት) ላይ ፍትሃዊ እና እኩል የአየር ሰዓት እንዲያገኙ የሚያስችል በገለልተኛ አካል የሚመራ ህጋዊ ማዕቀፍ እንዲዘረጋ።
➡️ በሂደት ላይ ያለው ብሔራዊ ምክክር ሁሉንም የፖለቲካና የትጥቅ ቡድኖችን ያካተተ እንዲሆንና እንደ ፌዴራሊዝምና የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ባሉ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች አስገዳጅ እንዲሆኑ ማድረግ።
የሚሉትን ጥያቄዎች በይፋ አቅርቧል።
የተመድ ልዑካን ቡድን የምርጫውን ቅድመ-ሁኔታዎች የመገምገም ኃላፊነት የተሰጠው መሆኑን ያመለከተው ኦፌኮ ቡድኑ የቀረበለትን ሃሳብ በትኩረት እንዳዳመጠው ገልጿል።
ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ የሚያደርገው ውሳኔ እነዚህ " መሠረታዊ " ያላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታቸው ላይ የተመሰረተ እንደሆነ አሳውቋል።
መረጃውን የላከው የኦፌኮ የህዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ የምንወስነው እነዚህ መሠረታዊ ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታቸው ላይ የተመሰረተ ነው " - ኦፌኮ
የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የውጭ መረጃ አሰባሳቢ ልዑክ ጋር በዋና ፅ/ቤቱ መወያየቱን ገለጸ።
ፓርቲው ውይይቱ የነበረው በ2018 ዓ/ም የሚካሄደው 7ኛው አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምርጫ ላይ እንደሆነ አመልክቷል።
" ምርጫው ቁልፍ እና ወሳኝ የተባሉ ጥያቄዎችን አቅርቢያለሁ " ብሏል።
ኦፌኮ " ነጻ፣ ፍትሃዊ እና ተአማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲረጋገጥ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገባቸውን መሰረታዊ ጥያቄዎችን እንዲሁም የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀውስ አስመልክቶ ዝርዝር እና የማያዳግም ግምገማ አቅርበናል " ብሏል።
በውይይቱ ላይ እነማን ተገኙ ?
ኦፌኮን በመወከል ፦
- የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
- የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም ተገኝተዋል።
የተባበሩት መንግስታት ልዑካን ቡድን አራት አባላት የያዘ ሲሆን ፦
- በተመድ የአፍሪካ ህብረት ቢሮ (UNOAU) የምርጫ ድጋፍ ክፍል ዋና ኦፊሰር አኪንየሚ ኦ. አዴግባላን
- በኢትዮጵያ የተመድ የነዋሪ አስተባባሪ ጽ/ቤት የሰላምና ልማት አማካሪ ዶ/ር ዘቡሎን ሱይፎን ታክዋን እንዲሁም ሌሎች ሁለት ቁልቅ የተመድ ልዑካን አካትቷል።
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ምን አሉ ?
" ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ላይ መሳተፉ ሙሉ በሙሉ በመሠረታዊ እና በተጨባጭ ለውጦች ላይ የተመሰረተ ነው።
ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ቴክኒካዊ ሂደት ብቻ አይደለም፤ የዲሞክራሲያዊ ሂደት ውጤት ነው። ይህ ሂደት ዛሬ በኢትዮጵያ የለም። በጦርነት እና በፖለቲካ ስደት ውስጥ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማካሄድ አይቻልም። " ብለዋል።
ኦፌኮ፣ ተመድ ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖውን ተጠቅሞ እንዲያስፈጽም በማሳሰብ ለመንግስት የሚቀርቡ ዝርዝር ጥያቄዎችን አቅርቧል።
በኦፌኮ የቀረቡ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
➡️ በኦሮሚያና በመላ ኢትዮጲያ ሰላም ፣ በክልሉ ያለውን አውዳሚ ግጭት ለማስቆም በመንግስት ኃይሎች እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሰ) መካከል በአለም አቀፍ ታዛቢዎች የሚረጋገጥ አፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ።
➡️ ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች መፍታት፣ የኦፌኮ አባላትን፣ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ጨምሮ በመላ አገሪቱ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ።
➡️ በነጻነት የመንቀሳቀስ ዋስትና፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማስፈራራት፣ ወከባና እስራት እንዲቆም። ኦፌኮ የፓርቲ ጽ/ቤቶችን በነጻነት የመክፈትና የማንቀሳቀስ እንዲሁም ከሃገር ውስጥ አስተዳዳሪዎችና ከጸጥታ ኃይሎች ምንም አይነት ጣልቃ ገብነት ሳይኖር ህዝባዊ ስብሰባዎችን የማድረግ መብት እንዲከበርለት ጠይቋል።
በተጨማሪ፦
➡️ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልል የጸጥታ ኃይሎች አመራሮች በፖለቲካው ሂደት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ለመሆናቸው በይፋ ቃል የሚገቡበት እና ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ አካል የሚቋቋምበት ስምምነት እንዲፈረም።
➡️ ከምርጫ በፊት የሁሉም ፓርቲዎች ውይይት፣ በገዥው ፓርቲ እና በሁሉም ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግልጽ የሆነ የምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ለመስማማት የሚያስችል ይፋዊ ውይይት እንዲካሄድ።
➡️ የምርጫ ቦርድን እንደገና ማቋቋም፣ ገለልተኝነቱን ለማረጋገጥ ሁሉም ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚሳተፉበት ግልጽና አካታችነት ላይ በተመሰረተ ሂደት ኮሚሽነሮችን በመሾም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እንደገና እንዲዋቀር።
➡️ አሁን በስራ ላይ ያለውንና አሸናፊ ሁሉን የሚወስድበትን የአብላጫ ድምፅ የምርጫ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መልኩ መከለስ። ሁሉም ማህበረሰቦችና የፖለቲካ ቡድኖች በፓርላማ ውስጥ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራቸው ለማድረግ ወደ ተመጣጣኝ ውክልና (MMP) የምርጫ ሥርዓት እንዲሸጋገር።
➡️ ገዥው ፓርቲ በመገናኛ ብዙኃን ላይ ያለውን የበላይነት በማስቀረት ሁሉም የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግስት ሚዲያዎች (EBC, OBN የመሳሰሉት) ላይ ፍትሃዊ እና እኩል የአየር ሰዓት እንዲያገኙ የሚያስችል በገለልተኛ አካል የሚመራ ህጋዊ ማዕቀፍ እንዲዘረጋ።
➡️ በሂደት ላይ ያለው ብሔራዊ ምክክር ሁሉንም የፖለቲካና የትጥቅ ቡድኖችን ያካተተ እንዲሆንና እንደ ፌዴራሊዝምና የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ባሉ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች አስገዳጅ እንዲሆኑ ማድረግ።
የሚሉትን ጥያቄዎች በይፋ አቅርቧል።
የተመድ ልዑካን ቡድን የምርጫውን ቅድመ-ሁኔታዎች የመገምገም ኃላፊነት የተሰጠው መሆኑን ያመለከተው ኦፌኮ ቡድኑ የቀረበለትን ሃሳብ በትኩረት እንዳዳመጠው ገልጿል።
ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ የሚያደርገው ውሳኔ እነዚህ " መሠረታዊ " ያላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታቸው ላይ የተመሰረተ እንደሆነ አሳውቋል።
መረጃውን የላከው የኦፌኮ የህዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia