" በዚህ ዓመት ብቻ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ አግኝተናል !! "
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦
" ዩኒቲ ፓርክ ፣ ፍሬንድሺፕ ፣ ሳይንስ ሙዝየም ፣ ናሽናል ፓላስ ብቻ በዚህ ዓመት 1.5 ሚሊዮን ሰው ጎብኝቷል። ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አግኝተንበታል።
አስቡት ' ዩኒቲ ፣ ፍሬንድሺፕ ለምን ይሰራል ? ' ሲባል የነበረበትን ዘመን። በአንድ አመት 1.5 ሚሊዮን ሰው መሄጃ አዘጋጀንለት ማለት ነው። ያ አንድ ሚሊዮን ሰው ዩኒቲ ባይኖር ፣ ፍሬንድሺፕ ባይኖር ወይ ጫት ላይ ነው ወይ ድራፍት ላይ ነው።
ባለፉት ጥቂት አመታት በነዚህ ቦታዎች 13. 5 ሚሊዮን ሰው ጎብኝቷል። ሳይንስ ሙዝየም፣ ፍሬድሺፕ እና ዩኒቲ። ይሄ የተመዘገበና ብር የሚከፍል ነው። የሚታወቅ ቁጥር ነው።
አዲስ አበባ ላይ ባለው ዳታ በዚህ ዓመት ያለው የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስት እድገት በጣም ከፍተኛ ነው። "
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦
" ዩኒቲ ፓርክ ፣ ፍሬንድሺፕ ፣ ሳይንስ ሙዝየም ፣ ናሽናል ፓላስ ብቻ በዚህ ዓመት 1.5 ሚሊዮን ሰው ጎብኝቷል። ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አግኝተንበታል።
አስቡት ' ዩኒቲ ፣ ፍሬንድሺፕ ለምን ይሰራል ? ' ሲባል የነበረበትን ዘመን። በአንድ አመት 1.5 ሚሊዮን ሰው መሄጃ አዘጋጀንለት ማለት ነው። ያ አንድ ሚሊዮን ሰው ዩኒቲ ባይኖር ፣ ፍሬንድሺፕ ባይኖር ወይ ጫት ላይ ነው ወይ ድራፍት ላይ ነው።
ባለፉት ጥቂት አመታት በነዚህ ቦታዎች 13. 5 ሚሊዮን ሰው ጎብኝቷል። ሳይንስ ሙዝየም፣ ፍሬድሺፕ እና ዩኒቲ። ይሄ የተመዘገበና ብር የሚከፍል ነው። የሚታወቅ ቁጥር ነው።
አዲስ አበባ ላይ ባለው ዳታ በዚህ ዓመት ያለው የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስት እድገት በጣም ከፍተኛ ነው። "
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በዚህ ዓመት ብቻ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ አግኝተናል !! " ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦ " ዩኒቲ ፓርክ ፣ ፍሬንድሺፕ ፣ ሳይንስ ሙዝየም ፣ ናሽናል ፓላስ ብቻ በዚህ ዓመት 1.5 ሚሊዮን ሰው ጎብኝቷል። ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አግኝተንበታል። አስቡት ' ዩኒቲ ፣ ፍሬንድሺፕ ለምን ይሰራል ? ' ሲባል የነበረበትን ዘመን። በአንድ አመት 1.5 ሚሊዮን ሰው መሄጃ አዘጋጀንለት…
#EthiopianAirlines🇪🇹
የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዚህ ዓመት ተጨማሪ 13 አውሮፕላኖችን መግዛቱን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
አሁን ላይ አየር መንገዱ ያሉት አውሮፕላኖች ብዛት 180 መድረሱን ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ በዚህ ዓመት ብቻ 6 አዳዲስ መዳረሻዎችን በመጨመር አጠቃላይ መዳረሻውን ወደ 136 ከፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
አየር መንገዱ በዚህ ዓመት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ከ19 ሚሊዮን ሰው በላይ ማጓጓዙን አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዚህ ዓመት ተጨማሪ 13 አውሮፕላኖችን መግዛቱን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
አሁን ላይ አየር መንገዱ ያሉት አውሮፕላኖች ብዛት 180 መድረሱን ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ በዚህ ዓመት ብቻ 6 አዳዲስ መዳረሻዎችን በመጨመር አጠቃላይ መዳረሻውን ወደ 136 ከፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
አየር መንገዱ በዚህ ዓመት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ከ19 ሚሊዮን ሰው በላይ ማጓጓዙን አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines🇪🇹 የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዚህ ዓመት ተጨማሪ 13 አውሮፕላኖችን መግዛቱን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። አሁን ላይ አየር መንገዱ ያሉት አውሮፕላኖች ብዛት 180 መድረሱን ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚህ ዓመት ብቻ 6 አዳዲስ መዳረሻዎችን በመጨመር አጠቃላይ መዳረሻውን ወደ 136 ከፍ ማድረጉን ገልጸዋል። አየር መንገዱ በዚህ…
#HoPR🇪🇹
" 3.5 ቢሊየን ዶላር ከዚህ ቀደም የነበሩ መንግስታት የተበደሩትን ገንዘብ ያለፉትን ሶስት እና አራት አመታት ተደራድረን የእዳ ሽግሽግ እንዲኖር አድርገናል የገንዘብ ሚንስቴር በትላንትናው እለት በፈረንሳይ ተፈራርሟል" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
የበጀት አመቱን አፈጻጸም በየዘርፉ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ፣ በኢንዱስትሪ ፣በፋይናንስ እና በቱሪዝም ዘርፍ ተመዘገቡ ያሏቸውን ለውጦች ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባነፈው አመት የ8.1 በመቶ እድገት ኢትዮጵያ ማስመዝገቧን በመግለጽ ዘንድሮ 8.4 በመቶ እድገት ለማስመዝገብ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚንስትሩ በየዘርፉ አስመዘገብናቸው ስሏሏቸው ለውጦች ምን አሉ ?
ግብርና
- በግብርና ዘርፍ 6.1 በመቶ እድገት እንዲያመጣ ታቅዶ ነው እየተሰራ ያለው።
- ባለፈው አመት 26 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማረስ ችለን ነበር ዘንድሮ 31.8 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማረስ ተችሏል።
- ባለፈው አመት በሁሉም አይነት የእርሻ ምርቶች 1.2 ቢሊየን ኩንታል ምርት ነበር የሰበሰብነው ዘንድሮ 1.5 ቢሊየን ኩንታል ምርት መሰብሰብ ችለናል ይህም 24.7 በመቶ ጭማሪ አለው።
- ከ100 በላይ አነሰተኛ እና መካከለኛ ግድቦች ይሰራሉ።
- 50 ሺ ሄክታር አሲዳማ መሬት ታክሞ ወደ እርሻ ገብቷል።
ኢንዱስትሪ
° 12.8 በመቶ እድገት እንደሚያመጣ ታስቦ እየተሰራ ነው።
° የኢንዱስትሪው ሴክተር የኢነርጂ ፍላጎት 40 በመቶ ጨምሯል።
° የሲሚንቶ ምርት 6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
° የብረት ውጤቶች 18 በመቶ አድጓል።
° የመስታወት ፋብሪካ በቂ አልነበረም በአመት 600 ሺ ቶን የሚያመርት የመስታወት ፋብሪካ እየተሰራ ይገኛል ጥሬ እቃውንም ከሃገር ውስጥ ይጠቀማል ታህሳስ ወይም ጥር ላይ ያልቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ማእድን
- ባለፈው አመት 4 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገናል ዘንድሮ 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገናል።
- አምና በወርቅ ኤክስፖርት 300 ሚሊየን ዶላር ዘንድሮ 3.5 ቢሊየን ዶላር አግኝተናል።
- ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚቀጥለው አመት የመጀመሪያውን የጋዝ ምርት ለገበያ ታቀርባለች።
- ምክር ቤቱ ከእረፍት ሳይመለስ ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ መስራት ትጀምራለች ከ 40 ወራት በኋላም ግንባታው ይጠናቀቃል።
- የማዕድን ዘርፍ በጋዝ ፣በወርቅ እና በማዳበሪያ የተለያዩ እድገቶችን እያመጣ ነው።
ቱሪዝም
° 1.3 ሚሊየን የውጭ ቱሪስት ኢትዮጵያን ጎብኝቷል።
° ዩኒቲ ፣ፍሬንድ ሺፕ ፣ ፓላሱን እና ሳይንስ ሙዚየምን ብቻ ከ 1.5 ሚሊየን ህዝብ በላይ ጎብኝቶታል ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አግኝተንበታል።
° አየር መንገድ በሃገር ውስጥ እና በውጭ 19 ሚሊየን ህዝብ አጓጉዟል።
ፋይናንስ
- ብድር ከአምና 75 በመቶ ጨምሯል የግሉ ሴክተር 80 በመቶ ድርሻ አላቸው።
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 900 ቢሊየን ብር እዳ የነበረበት ተቋም ነበር እዳው ከባንኩ ወደ መንግሥት በመዘዋወሩ እና ለባንኩም 700 ሚሊየን ዶላር ድጎማ በመሰጠቱ ተቋሙንም ሆነ ሴክተሩም ማዳን ተችሏል።
- የሞባይል መኒ ተጠቃሚ 55 ሚሊየን ደንበኛ ደርሷል።
- ወደ 11 ሚሊየን ደንበኞች 24.5 ሚሊየን ብር ብድር በሞባይል መኒ አግኝተዋል።
ኤክስፖርት
° 5.1 ቢሊየን ዶላር ከኤክስፖርት ገቢ እናገኛለን ብለን አቅደን 8.2 ቢሊየን ዶላር አግኝተናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" 3.5 ቢሊየን ዶላር ከዚህ ቀደም የነበሩ መንግስታት የተበደሩትን ገንዘብ ያለፉትን ሶስት እና አራት አመታት ተደራድረን የእዳ ሽግሽግ እንዲኖር አድርገናል የገንዘብ ሚንስቴር በትላንትናው እለት በፈረንሳይ ተፈራርሟል" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
የበጀት አመቱን አፈጻጸም በየዘርፉ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ፣ በኢንዱስትሪ ፣በፋይናንስ እና በቱሪዝም ዘርፍ ተመዘገቡ ያሏቸውን ለውጦች ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባነፈው አመት የ8.1 በመቶ እድገት ኢትዮጵያ ማስመዝገቧን በመግለጽ ዘንድሮ 8.4 በመቶ እድገት ለማስመዝገብ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚንስትሩ በየዘርፉ አስመዘገብናቸው ስሏሏቸው ለውጦች ምን አሉ ?
ግብርና
- በግብርና ዘርፍ 6.1 በመቶ እድገት እንዲያመጣ ታቅዶ ነው እየተሰራ ያለው።
- ባለፈው አመት 26 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማረስ ችለን ነበር ዘንድሮ 31.8 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማረስ ተችሏል።
- ባለፈው አመት በሁሉም አይነት የእርሻ ምርቶች 1.2 ቢሊየን ኩንታል ምርት ነበር የሰበሰብነው ዘንድሮ 1.5 ቢሊየን ኩንታል ምርት መሰብሰብ ችለናል ይህም 24.7 በመቶ ጭማሪ አለው።
- ከ100 በላይ አነሰተኛ እና መካከለኛ ግድቦች ይሰራሉ።
- 50 ሺ ሄክታር አሲዳማ መሬት ታክሞ ወደ እርሻ ገብቷል።
ኢንዱስትሪ
° 12.8 በመቶ እድገት እንደሚያመጣ ታስቦ እየተሰራ ነው።
° የኢንዱስትሪው ሴክተር የኢነርጂ ፍላጎት 40 በመቶ ጨምሯል።
° የሲሚንቶ ምርት 6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
° የብረት ውጤቶች 18 በመቶ አድጓል።
° የመስታወት ፋብሪካ በቂ አልነበረም በአመት 600 ሺ ቶን የሚያመርት የመስታወት ፋብሪካ እየተሰራ ይገኛል ጥሬ እቃውንም ከሃገር ውስጥ ይጠቀማል ታህሳስ ወይም ጥር ላይ ያልቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ማእድን
- ባለፈው አመት 4 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገናል ዘንድሮ 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገናል።
- አምና በወርቅ ኤክስፖርት 300 ሚሊየን ዶላር ዘንድሮ 3.5 ቢሊየን ዶላር አግኝተናል።
- ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚቀጥለው አመት የመጀመሪያውን የጋዝ ምርት ለገበያ ታቀርባለች።
- ምክር ቤቱ ከእረፍት ሳይመለስ ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ መስራት ትጀምራለች ከ 40 ወራት በኋላም ግንባታው ይጠናቀቃል።
- የማዕድን ዘርፍ በጋዝ ፣በወርቅ እና በማዳበሪያ የተለያዩ እድገቶችን እያመጣ ነው።
ቱሪዝም
° 1.3 ሚሊየን የውጭ ቱሪስት ኢትዮጵያን ጎብኝቷል።
° ዩኒቲ ፣ፍሬንድ ሺፕ ፣ ፓላሱን እና ሳይንስ ሙዚየምን ብቻ ከ 1.5 ሚሊየን ህዝብ በላይ ጎብኝቶታል ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አግኝተንበታል።
° አየር መንገድ በሃገር ውስጥ እና በውጭ 19 ሚሊየን ህዝብ አጓጉዟል።
ፋይናንስ
- ብድር ከአምና 75 በመቶ ጨምሯል የግሉ ሴክተር 80 በመቶ ድርሻ አላቸው።
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 900 ቢሊየን ብር እዳ የነበረበት ተቋም ነበር እዳው ከባንኩ ወደ መንግሥት በመዘዋወሩ እና ለባንኩም 700 ሚሊየን ዶላር ድጎማ በመሰጠቱ ተቋሙንም ሆነ ሴክተሩም ማዳን ተችሏል።
- የሞባይል መኒ ተጠቃሚ 55 ሚሊየን ደንበኛ ደርሷል።
- ወደ 11 ሚሊየን ደንበኞች 24.5 ሚሊየን ብር ብድር በሞባይል መኒ አግኝተዋል።
ኤክስፖርት
° 5.1 ቢሊየን ዶላር ከኤክስፖርት ገቢ እናገኛለን ብለን አቅደን 8.2 ቢሊየን ዶላር አግኝተናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " 3.5 ቢሊየን ዶላር ከዚህ ቀደም የነበሩ መንግስታት የተበደሩትን ገንዘብ ያለፉትን ሶስት እና አራት አመታት ተደራድረን የእዳ ሽግሽግ እንዲኖር አድርገናል የገንዘብ ሚንስቴር በትላንትናው እለት በፈረንሳይ ተፈራርሟል" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። የበጀት አመቱን አፈጻጸም…
#Ethiopia 🇪🇹
#GERD🇪🇹
" መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! "
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን።
ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው ነገ ክረምቱ ሲያልቅ።
ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ያለኝ መልዕክት ህዳሴ ለሱዳን ህዳሴ ለግብፅ በረከት ነው። በፍጹም ጉዳት አያመጣባቸውም። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ልማት ልማታቸው ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ኢነርጂ ለሁሉም ጎረቤቶች የሚዳረስ ነው።
የኛ ግድብ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ ቱርካና አጀንዳ አይሆንም ነበር። ታስታውሳላችሁ ግቤ 3 ሲሰራ 'ቱርካና ይደርቃል የሚል ከፍተኛ ችግር ነበር። እንኳን ሊደርው ከግድቡ በኋላ ይኸው ሞልቶ እያስቸገረ ነው ያለው።
አሁንም ግብፅ ብትሄዱ የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም። ወደፊትም ኢትዮጵያ እስከበለጸገች ድረስ እስካለች ድረስ የግብፅ ወንድሞቻችንን ጉዳት እኛ አናይም ተባብረን ከወንድሞቻች ጋር ማደግ እንፈልጋለን።
ግብፅ እንድትጎዳ ፣ ሱዳን እንድትጎዳ አንፈልግም። ኢነርጂውን በጋራ እንጠቀማለን ውሃውን በጋራ እንጠቀማለን ልማት በጋራ ይመጣል። ንግግር ካስፈለገ እንነጋገራለን ችግር የለም።
እኛ ለረጅም ጊዜ ስናነሳ የነበረው ' አትስሩ ' አትበሉን ነው ያልነው እንጂ በኛ ገንዘብ በኛ ምድር የሚሰራውም ስራ አታግዱ ነው ያልነው እንጂ ያን እስካልከለከሉ ድረስ አሁንም ከግብፆች ጋር ለመነጋገር፣ ለመደራደር ፣ ለመስራት ኢትዮጵያ ዝግጁ ናት፤ምንም ችግር የለብንም።
በእርግጠኝነት የምናገረው ህዳሴ ለግብፅም ለሱዳንም ጉዳት አያመጣም።
በዚሁ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የስልጣን ባለቤት ይህ የተከበረው ምክር ቤት ስለሆነ ለግብፅ መንግሥት ፣ ለሱዳን መንግሥት እንዲሁም ለተፋሰሱ ሀገራት መንግሥታት በሙሉ መስከረም ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን ስናስመርቅ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ግብዣ አቀርብላቸዋለሁ።
የጋራ ሃብታችን ነው ፤ በጋራ እናስመርቀዋለን በጋራ እናየዋለን፣ የሚታዩ ጉዳዮች ካሉ በጋራ እናያለን።
ከድርቅ ጋር ተያይዞ ግብፅ የሚነሳው ነገር ' ድርቅ በሚሆንበት ሰዓት ግብፅ ትጎዳለች ' ነው ፤ ድርቅ የሚባለው ኢትዮጵያ ነው ኢትዮጵያ ከደረቀች ውሃዋ የለም ማለት ነው እዛ አይደለም ድርቅ የሚባለው፤ ኢትዮጵያ ደግሞ እንዳትደርቅ Green Legacy (አረንጓዴ አሻራ) እየሰራን ነው እኛ አንደርቅም ማለት ነው እኛ ዝናብ ካገኘን እኛም ግብፅም ሱዳንም ሌሎቹም ይጠቀማሉ። በቅንነት አይተን በጋራ ለልማት እንድንሰራ አደራ እላለሁ። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#GERD
" መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! "
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን።
ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው ነገ ክረምቱ ሲያልቅ።
ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ያለኝ መልዕክት ህዳሴ ለሱዳን ህዳሴ ለግብፅ በረከት ነው። በፍጹም ጉዳት አያመጣባቸውም። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ልማት ልማታቸው ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ኢነርጂ ለሁሉም ጎረቤቶች የሚዳረስ ነው።
የኛ ግድብ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ ቱርካና አጀንዳ አይሆንም ነበር። ታስታውሳላችሁ ግቤ 3 ሲሰራ 'ቱርካና ይደርቃል የሚል ከፍተኛ ችግር ነበር። እንኳን ሊደርው ከግድቡ በኋላ ይኸው ሞልቶ እያስቸገረ ነው ያለው።
አሁንም ግብፅ ብትሄዱ የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም። ወደፊትም ኢትዮጵያ እስከበለጸገች ድረስ እስካለች ድረስ የግብፅ ወንድሞቻችንን ጉዳት እኛ አናይም ተባብረን ከወንድሞቻች ጋር ማደግ እንፈልጋለን።
ግብፅ እንድትጎዳ ፣ ሱዳን እንድትጎዳ አንፈልግም። ኢነርጂውን በጋራ እንጠቀማለን ውሃውን በጋራ እንጠቀማለን ልማት በጋራ ይመጣል። ንግግር ካስፈለገ እንነጋገራለን ችግር የለም።
እኛ ለረጅም ጊዜ ስናነሳ የነበረው ' አትስሩ ' አትበሉን ነው ያልነው እንጂ በኛ ገንዘብ በኛ ምድር የሚሰራውም ስራ አታግዱ ነው ያልነው እንጂ ያን እስካልከለከሉ ድረስ አሁንም ከግብፆች ጋር ለመነጋገር፣ ለመደራደር ፣ ለመስራት ኢትዮጵያ ዝግጁ ናት፤ምንም ችግር የለብንም።
በእርግጠኝነት የምናገረው ህዳሴ ለግብፅም ለሱዳንም ጉዳት አያመጣም።
በዚሁ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የስልጣን ባለቤት ይህ የተከበረው ምክር ቤት ስለሆነ ለግብፅ መንግሥት ፣ ለሱዳን መንግሥት እንዲሁም ለተፋሰሱ ሀገራት መንግሥታት በሙሉ መስከረም ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን ስናስመርቅ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ግብዣ አቀርብላቸዋለሁ።
የጋራ ሃብታችን ነው ፤ በጋራ እናስመርቀዋለን በጋራ እናየዋለን፣ የሚታዩ ጉዳዮች ካሉ በጋራ እናያለን።
ከድርቅ ጋር ተያይዞ ግብፅ የሚነሳው ነገር ' ድርቅ በሚሆንበት ሰዓት ግብፅ ትጎዳለች ' ነው ፤ ድርቅ የሚባለው ኢትዮጵያ ነው ኢትዮጵያ ከደረቀች ውሃዋ የለም ማለት ነው እዛ አይደለም ድርቅ የሚባለው፤ ኢትዮጵያ ደግሞ እንዳትደርቅ Green Legacy (አረንጓዴ አሻራ) እየሰራን ነው እኛ አንደርቅም ማለት ነው እኛ ዝናብ ካገኘን እኛም ግብፅም ሱዳንም ሌሎቹም ይጠቀማሉ። በቅንነት አይተን በጋራ ለልማት እንድንሰራ አደራ እላለሁ። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የፌዴራል መንግሥት በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ፀደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 42ኛ መደበኛ ጉባኤ የ2018 ዓ/ም የፌዴራል መንግስት በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር አድርጎ አፅድቋል።
@tikvahethiopia
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 42ኛ መደበኛ ጉባኤ የ2018 ዓ/ም የፌዴራል መንግስት በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር አድርጎ አፅድቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia 🇪🇹 #GERD 🇪🇹 " መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! " የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ? " ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን። ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው…
" በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው ተጣርቶ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ "- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል።
ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አንድ አባት መገደላቸውን እና ሟቹ አባት ባህታዊ አባ ኃይለሚካኤል እንደሚባሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከገዳሙ ባገኘው መረጃ መዘገቡ ይታወሳል።
በተደጋጋሚ በገዳሙ እያጋጠመው ስላለው የመነኮሳት ግድያ መንግስት ለምን ማስቆም ተሳነው ሲሉ በዛሬው እለት የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል።
የአብን አባሉ አቶ አበባው " በዝቋላ ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው " ሲሉ ጥያቄያቸውን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በዝቋላ አንድ መናኝ መገደላቸውን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዝርዝር በሰጡት ምላሽ ምን አሉ ?
" ' መሻቴን ፍላጎቴን በሃይል ማስፈጸም እችላለሁ ' የሚሉ ሃይል በብቸኝነት የመጠቀም ስልጣን የመንግስት ብቻ መሆኑን የማይቀበሉ ሰዎች ናቸዉ።
እንዳሉት በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው ተጣርቶ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ።
የሃይማኖት ተቋማት የታጠቁ ሽፍቶች መሸሸጊያ ከሆኑ እንደዚህ አይነት አደጋ ሊፈጠር ይችላል የሃይማኖት ቦታ የሃይማኖት ብቻ መሆን አለበት ሲሸሹ የሚደበቁበት ከሆነ ሲከፋቸው ገድለው ሊሄዱ ስለሚችሉ።
የዝቋላው ምን ይገርማል 12 አመት ተምሮ ፈተና ሊፈተን የሚሄድ ሰው ላይ የሚተኩሱ ሰዎች ዝቋላ ላይ አንድ አባት ላይ ቢገድሉ ምን ይገርማል።
የግድያው እሳቤ ነው ችግር ያለው ፈተና አትፈተን፣ ማዳበሪያ አትውሰድ ፣ትምህርት አትማር ብሎ የሚገድል ሰዉ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ የትም ሞት አለ ማለት ነው።
'ልብ ሲያቅ ገንፎ ያንቅ ይባላል' ልባችን ያውቀዋል እነማን እንደሆኑ፤ ድብብቆሽ አይደለም። እነማን ገዳይ እንደሆኑ ግልጽ ነው። 'ልብ ሲያቅ ገንፎ ያንቅ' የመባለው እያወቅነው የምናግበሰብሰው ጉዳይ ሲሆን ነው።
ግድያ ሽንፈት ብቻ ነው የሚያመጣው በመግደል አይሳካልኝም ብሎ ማመን ያስፈልጋል። ... በሃይል ፍላጎትን ማስፈጸም ማለቂያ የለውም መቆም አለበት። " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል።
ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አንድ አባት መገደላቸውን እና ሟቹ አባት ባህታዊ አባ ኃይለሚካኤል እንደሚባሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከገዳሙ ባገኘው መረጃ መዘገቡ ይታወሳል።
በተደጋጋሚ በገዳሙ እያጋጠመው ስላለው የመነኮሳት ግድያ መንግስት ለምን ማስቆም ተሳነው ሲሉ በዛሬው እለት የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል።
የአብን አባሉ አቶ አበባው " በዝቋላ ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው " ሲሉ ጥያቄያቸውን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በዝቋላ አንድ መናኝ መገደላቸውን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዝርዝር በሰጡት ምላሽ ምን አሉ ?
" ' መሻቴን ፍላጎቴን በሃይል ማስፈጸም እችላለሁ ' የሚሉ ሃይል በብቸኝነት የመጠቀም ስልጣን የመንግስት ብቻ መሆኑን የማይቀበሉ ሰዎች ናቸዉ።
እንዳሉት በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው ተጣርቶ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ።
የሃይማኖት ተቋማት የታጠቁ ሽፍቶች መሸሸጊያ ከሆኑ እንደዚህ አይነት አደጋ ሊፈጠር ይችላል የሃይማኖት ቦታ የሃይማኖት ብቻ መሆን አለበት ሲሸሹ የሚደበቁበት ከሆነ ሲከፋቸው ገድለው ሊሄዱ ስለሚችሉ።
የዝቋላው ምን ይገርማል 12 አመት ተምሮ ፈተና ሊፈተን የሚሄድ ሰው ላይ የሚተኩሱ ሰዎች ዝቋላ ላይ አንድ አባት ላይ ቢገድሉ ምን ይገርማል።
የግድያው እሳቤ ነው ችግር ያለው ፈተና አትፈተን፣ ማዳበሪያ አትውሰድ ፣ትምህርት አትማር ብሎ የሚገድል ሰዉ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ የትም ሞት አለ ማለት ነው።
'ልብ ሲያቅ ገንፎ ያንቅ ይባላል' ልባችን ያውቀዋል እነማን እንደሆኑ፤ ድብብቆሽ አይደለም። እነማን ገዳይ እንደሆኑ ግልጽ ነው። 'ልብ ሲያቅ ገንፎ ያንቅ' የመባለው እያወቅነው የምናግበሰብሰው ጉዳይ ሲሆን ነው።
ግድያ ሽንፈት ብቻ ነው የሚያመጣው በመግደል አይሳካልኝም ብሎ ማመን ያስፈልጋል። ... በሃይል ፍላጎትን ማስፈጸም ማለቂያ የለውም መቆም አለበት። " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው ተጣርቶ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ "- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል። ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አንድ አባት መገደላቸውን…
" ጦርነት ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል !! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ዛሬ በነበረው የህ/ተ/ም/ቤት ጉባኤን አንድ አባል " በትግራይ ክልል ዳግም ጦርንት እንዳይነሳ ስጋት አለ " በማለት በክልሉ ስላለው አሁናዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራርያ እና ምላሽ ጠይቀዋል።
" ህወሓት ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ እያደረገ ነው " በማለት " ከሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ፤ ምሁራን እና ወጣቶች ምን ይጠበቃል ? " ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን መለሱ ?
" የሁሉም እምነት አባቶች እዚህ ተወካይዎች አላችሁ፣ ሌላ ምንም ስራ የላችሁም በፍጥነት ትግራይ ወደ ግጭት፣ ወደ ጦርነት እንዳይገባ ስራችሁን አሁን ጀምሩ፣ ከተጀመረ ወዲያ ብትናገሩ ዋጋ የለውም።
ባለሃብቶች፣ ምሁራን፣ ኤምባሲዎች ውጊያ እንዳይጀመር አሁን ሚናችሁን ተወጡ ምክንያቱም ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ይበላሻል ነገር።
በእኛ በኩል በትግራይ ምድር እንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለንም፣ ከቻልን ማልማት ነው የምንፈልገው።
ትግራይ ላሉ ሃይሎች ለትግራይ ህዝብም፣ ለኢትዮጵያ ህዝብም መታወቅ ያለበት ጦርነት አያስፈልገንም በሰላም እና በውይይት ጉዳያችንን መፍታት ይቻላል " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዛሬ በነበረው የህ/ተ/ም/ቤት ጉባኤን አንድ አባል " በትግራይ ክልል ዳግም ጦርንት እንዳይነሳ ስጋት አለ " በማለት በክልሉ ስላለው አሁናዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራርያ እና ምላሽ ጠይቀዋል።
" ህወሓት ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ እያደረገ ነው " በማለት " ከሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ፤ ምሁራን እና ወጣቶች ምን ይጠበቃል ? " ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን መለሱ ?
" የሁሉም እምነት አባቶች እዚህ ተወካይዎች አላችሁ፣ ሌላ ምንም ስራ የላችሁም በፍጥነት ትግራይ ወደ ግጭት፣ ወደ ጦርነት እንዳይገባ ስራችሁን አሁን ጀምሩ፣ ከተጀመረ ወዲያ ብትናገሩ ዋጋ የለውም።
ባለሃብቶች፣ ምሁራን፣ ኤምባሲዎች ውጊያ እንዳይጀመር አሁን ሚናችሁን ተወጡ ምክንያቱም ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ይበላሻል ነገር።
በእኛ በኩል በትግራይ ምድር እንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለንም፣ ከቻልን ማልማት ነው የምንፈልገው።
ትግራይ ላሉ ሃይሎች ለትግራይ ህዝብም፣ ለኢትዮጵያ ህዝብም መታወቅ ያለበት ጦርነት አያስፈልገንም በሰላም እና በውይይት ጉዳያችንን መፍታት ይቻላል " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ጦርነት ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል !! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በነበረው የህ/ተ/ም/ቤት ጉባኤን አንድ አባል " በትግራይ ክልል ዳግም ጦርንት እንዳይነሳ ስጋት አለ " በማለት በክልሉ ስላለው አሁናዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራርያ እና ምላሽ ጠይቀዋል። " ህወሓት ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ እያደረገ ነው " በማለት " ከሰላም…
" እነዚህ ሀገራት እንኳንስ እናተን እራሳቸውንም ማገዝ አይችሉም ! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ጉዳይ ያነሷቸው ነጥቦች ምንድናቸው ?
- ፕሪቶሪያ ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል።
- ትግራይ ቴሌኮሚኒኬሽን ፣ መብራት ፣ ባንክ ፣ የአየር ትራንስፖርት፣ ምርት አልነበረም ፣ ፋብሪካዎችም ስራ አቁመው ነበር ይሄ ሁሉ ጀምሯል።
- ትግራይ ክልል መንግሥት አልነበረም መንግሥት ተቋቁሟል።
- የተፈናቀሉ ሰዎች ራያ ፣ ፀለምት ተመልሰዋል።
- ወልቃይት የተፈናቀሉ አልተመለሱም DDR አልተፈጸመም።
- የወልቃይት ተፈናቃዮች መመለስ አለባቸው መንግሥት የፀና አቋም አለው። DDR መፈጸም አለበት። በነዚህ ጉዳዮች የፌዴራል ችግር አስመስሎ ለመሳል ይሞከራል ስህተት ነው። የፌዴራል መንግሥት በትግራይ ያለውን ጉዳይ በሰላም የመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለው።
- ለአንዳንዶች ውጊያ ጨዋታ ሊሆን ይችላል ለህዝባችን ፃረሞት ነው።
- ለአንዳንዶች ስለውጊያ እያነሱ መናገር ምንም ላይመስል ይችላል ስለማይሞቱ ለወጣት ግን ጉዳት ነው።
- የትግራይ ህዝብ 100% ጦርነት አይደልግም አይቶታል ትርፍ የለውም።
- ዓለም ትግራይ እና ምናምን ቢዋጉ ደንታው አይደለም ብዙ ውግያ እያስተናገደ ስለሆነ፤ ጆሮም የለውም ጊዜም የለውም። ዓለም ጊዜ ቢኖረው ኖሮ ሱዳንን ያዳምጥ ነበር።
- የዘመኑን የውጊያ ስልት መገንዘብ ይገባል ፤ አሁን እንደ ድሮ ተራራ መያዝ ተራራ መልቀቅ ብቻ ማሰብ ትክክል አይደለም። ኢራንን እና እስራኤልን ያዋጋው ተራራ አይደለም። ዘመን ተቀይሯል።
- አንዳንዶች " መንግሥት ተወጥሯል በፋኖ ፣ በሸኔ ወታደሩ ተበታትኗል አሁን ነው ጊዜው " የሚሉ ሰዎች አሉ እነዚህ ሰዎች ታሪክን መለስ ብለው ማየት አለባቸው። ሶማሊያ ኢትዮጵያን ስትወር ኢትዮጵያ ወታደር አልነበራትም ፤ ጣልያን ኢትዮጵያን ስትወር ወታደር አልነበራትም። ስለዚህ ኢትዮጵያ ራሷን ለመከላከል የግድ ሰልፍ የያዘ ወታደር አያስፈልጋትም።
- " የሚያግዙን ሰዎች አሉ ፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ " ብሎ ማሰብ በጣም የሚያሳዝነው ሌላው ጉዳይ ነው። እነዚህ ሀገራት እንኳንስ እናተን እራሳቸውንም ማገዝ አይችሉም። ሞራል ቲፎዞነትና ማገዝ ለየብቻ ነው። በትላልቅ ውጊያ እንኳን መደጋገፍ ችግር ሆኗል፤ እንኳንስ በሰፈር ውጊያ። የዓለም ኢኮኖሚ ከራስ ተርፎ ሰው ለማገዝ የሚያስችል ነገር ብዙ የለም ካለም ጥቂት ብቻ ነው።
- ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም ነው በንግግርና ውይይት ችግር መፍታት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ጉዳይ ያነሷቸው ነጥቦች ምንድናቸው ?
- ፕሪቶሪያ ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል።
- ትግራይ ቴሌኮሚኒኬሽን ፣ መብራት ፣ ባንክ ፣ የአየር ትራንስፖርት፣ ምርት አልነበረም ፣ ፋብሪካዎችም ስራ አቁመው ነበር ይሄ ሁሉ ጀምሯል።
- ትግራይ ክልል መንግሥት አልነበረም መንግሥት ተቋቁሟል።
- የተፈናቀሉ ሰዎች ራያ ፣ ፀለምት ተመልሰዋል።
- ወልቃይት የተፈናቀሉ አልተመለሱም DDR አልተፈጸመም።
- የወልቃይት ተፈናቃዮች መመለስ አለባቸው መንግሥት የፀና አቋም አለው። DDR መፈጸም አለበት። በነዚህ ጉዳዮች የፌዴራል ችግር አስመስሎ ለመሳል ይሞከራል ስህተት ነው። የፌዴራል መንግሥት በትግራይ ያለውን ጉዳይ በሰላም የመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለው።
- ለአንዳንዶች ውጊያ ጨዋታ ሊሆን ይችላል ለህዝባችን ፃረሞት ነው።
- ለአንዳንዶች ስለውጊያ እያነሱ መናገር ምንም ላይመስል ይችላል ስለማይሞቱ ለወጣት ግን ጉዳት ነው።
- የትግራይ ህዝብ 100% ጦርነት አይደልግም አይቶታል ትርፍ የለውም።
- ዓለም ትግራይ እና ምናምን ቢዋጉ ደንታው አይደለም ብዙ ውግያ እያስተናገደ ስለሆነ፤ ጆሮም የለውም ጊዜም የለውም። ዓለም ጊዜ ቢኖረው ኖሮ ሱዳንን ያዳምጥ ነበር።
- የዘመኑን የውጊያ ስልት መገንዘብ ይገባል ፤ አሁን እንደ ድሮ ተራራ መያዝ ተራራ መልቀቅ ብቻ ማሰብ ትክክል አይደለም። ኢራንን እና እስራኤልን ያዋጋው ተራራ አይደለም። ዘመን ተቀይሯል።
- አንዳንዶች " መንግሥት ተወጥሯል በፋኖ ፣ በሸኔ ወታደሩ ተበታትኗል አሁን ነው ጊዜው " የሚሉ ሰዎች አሉ እነዚህ ሰዎች ታሪክን መለስ ብለው ማየት አለባቸው። ሶማሊያ ኢትዮጵያን ስትወር ኢትዮጵያ ወታደር አልነበራትም ፤ ጣልያን ኢትዮጵያን ስትወር ወታደር አልነበራትም። ስለዚህ ኢትዮጵያ ራሷን ለመከላከል የግድ ሰልፍ የያዘ ወታደር አያስፈልጋትም።
- " የሚያግዙን ሰዎች አሉ ፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ " ብሎ ማሰብ በጣም የሚያሳዝነው ሌላው ጉዳይ ነው። እነዚህ ሀገራት እንኳንስ እናተን እራሳቸውንም ማገዝ አይችሉም። ሞራል ቲፎዞነትና ማገዝ ለየብቻ ነው። በትላልቅ ውጊያ እንኳን መደጋገፍ ችግር ሆኗል፤ እንኳንስ በሰፈር ውጊያ። የዓለም ኢኮኖሚ ከራስ ተርፎ ሰው ለማገዝ የሚያስችል ነገር ብዙ የለም ካለም ጥቂት ብቻ ነው።
- ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም ነው በንግግርና ውይይት ችግር መፍታት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NationalExam🇪🇹
ፆታዊ ትንኮሳ የፈፀሙ ሦስት ተማሪዎች ከሀገር አቀፍ ፈተና ታገዱ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ባለው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን ወደ መቱ ዩንቨርስቲ ከገቡት ተማሪዎች ውስጥ ሦስት ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ዕፆታዊ ትንኮሳ በመፈፀማቸው ከፈተናው መታገዳቸውን የመቱ ዩንቨርስቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " በርካታ ተማሪዎች ወደ ግቢ ከገቡ በኃላ ወጣ ያለ ፀባይ እያሳዩ ነበር " ብለዋል።
ዩኒቨርስቲውም ለፈተናው ከተቋቋመ ኮማንድፖስት ጋር በመሆን የመቆጣጠር ሥራ ሲሰራ እንደነበር በማንሳት፤ ሦስቱ ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም አደባባይ ላይ ትንኮሳ መፈፀማቸውን ተበድለናል ብለው በመጡ ሴቶች ቅሬታ እና ዩንቨርስቲውም ባደረገው ማጣራትብ ድርጊቱን መፈፀማቸውን አረጋግጧል።
" ትንኮሳ አድራጊዎቹ በአደባባይ ሴቶችን በግድ መሳም፤ ልብሳቸውን መገለብ እና መንካት የማይፈቀድ የአካላቸውን ክፍል በመንካታቸው ሴቶቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብለዋል።
በዚህ የተነሳ የትንኮሳ ወንጀል በፈፀሙ ወንዶች ላይ ከዘንድሮው አመት ፈተና እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ አንዱ ከኢሉ አባቦር ዞን በቾ ወረዳ ሁለቱ ደግሞ ከምስራቅ ወለጋ የመጡ መሆናቸውን ፕረዝዳንቱ አክለዋል።
እርምጃ ከተወሰደ በኃላ በግቢው ሲስተዋል የነበረው የተማሪዎች ሥነ ምግባር መሻሻሉንም ተናግረዋል።
ወደፊትን ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠር ትምህርት ቤቶች የፈተና ሥነ ምግባር ላይ ለተማሪዎች ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው የገለፁት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ሴት ተማሪዎችም ራሳቸውን እንዲጠብቁና ለትንኮሳ ራሳቸውን እንዳይጋብዙም ጠይቀዋል።
የመቱ ዩንቨርስቲ በዘንድሮው ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ14,000 በላይ ተማሪዎችን ለመፈተን መቀበሉንም ዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አለሙ ድሳሳ አክለው ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte
@tikvahethiopia
ፆታዊ ትንኮሳ የፈፀሙ ሦስት ተማሪዎች ከሀገር አቀፍ ፈተና ታገዱ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ባለው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን ወደ መቱ ዩንቨርስቲ ከገቡት ተማሪዎች ውስጥ ሦስት ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ዕፆታዊ ትንኮሳ በመፈፀማቸው ከፈተናው መታገዳቸውን የመቱ ዩንቨርስቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " በርካታ ተማሪዎች ወደ ግቢ ከገቡ በኃላ ወጣ ያለ ፀባይ እያሳዩ ነበር " ብለዋል።
ዩኒቨርስቲውም ለፈተናው ከተቋቋመ ኮማንድፖስት ጋር በመሆን የመቆጣጠር ሥራ ሲሰራ እንደነበር በማንሳት፤ ሦስቱ ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም አደባባይ ላይ ትንኮሳ መፈፀማቸውን ተበድለናል ብለው በመጡ ሴቶች ቅሬታ እና ዩንቨርስቲውም ባደረገው ማጣራትብ ድርጊቱን መፈፀማቸውን አረጋግጧል።
" ትንኮሳ አድራጊዎቹ በአደባባይ ሴቶችን በግድ መሳም፤ ልብሳቸውን መገለብ እና መንካት የማይፈቀድ የአካላቸውን ክፍል በመንካታቸው ሴቶቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብለዋል።
በዚህ የተነሳ የትንኮሳ ወንጀል በፈፀሙ ወንዶች ላይ ከዘንድሮው አመት ፈተና እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ አንዱ ከኢሉ አባቦር ዞን በቾ ወረዳ ሁለቱ ደግሞ ከምስራቅ ወለጋ የመጡ መሆናቸውን ፕረዝዳንቱ አክለዋል።
እርምጃ ከተወሰደ በኃላ በግቢው ሲስተዋል የነበረው የተማሪዎች ሥነ ምግባር መሻሻሉንም ተናግረዋል።
ወደፊትን ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠር ትምህርት ቤቶች የፈተና ሥነ ምግባር ላይ ለተማሪዎች ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው የገለፁት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ሴት ተማሪዎችም ራሳቸውን እንዲጠብቁና ለትንኮሳ ራሳቸውን እንዳይጋብዙም ጠይቀዋል።
የመቱ ዩንቨርስቲ በዘንድሮው ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ14,000 በላይ ተማሪዎችን ለመፈተን መቀበሉንም ዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አለሙ ድሳሳ አክለው ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM