መገጭ መቼ ነው የሚጠናቀቀው ?
የመገጭ የመስኖ ግድብ በሚቀጥለው በጀት ዓመት ይጠናቀቃል ተባለ።
በጎንደር ዙሪያ እየተገነባ ያለውና ከ16 ዓመታት በላይ የፈጀው የመገጭ የመስኖ ግድብ በቀጣይ በጀት አመት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
በ2001 ፕሮጀክቱ ሲጀመር፥ ለአከባቢው የመስኖ ፕሮጀክት እንዲሁም በጎንደርና አከባቢው በስፋት ለሚስተዋለው የመጠጥ ውኃ ችግር መፍትሔ ይሆናል ተብሎ እምነት ተጥሎበት ነበር።
ሥራው ሲጀመር ፕሮጀክቱ በ2.4 ቢሊዮን በጀት ቢሆንም በተባለው በጀትና ጊዜ መጠናቀቅ ባለመቻሉ የበርካቶች የዓመታት ጥናቄ ሆኖ ቆይቷል።
ፕሮጀክቱ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ከዚህ ቀደም ሥራ ላይ የነበረውን ተቋራጭ ውል በመሰረዝ ' ባይካ ' ከተባለ አዲስ ተቋራጭ ጋር በ14 ቢሊዮን ብር ካፒታል ውል ተገብቷል።
በዚህ ተቋራጭ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ጌታቸው አረጋ፥ የመገጭ የመስኖ የግድብ ፕሮጀክት የስትራክቸር ሥራ በዚህ ዓመት ነሐሴ ወር ላይ እንደሚጠናቀቅ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ሥራ አስኪያጁ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የመገጭ ግድብ 185 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውኃ የይዛል፤ ግድቡ ሲጠናቀቅ እስከ 5 ኪ.ሜ ወደ ኋላ ውኃ የሚተኛ ይሆናል።
የውኃ መቆጣጠሪያው (Intake Tower) አጠቃላይ 64 ሜትር (16 ፎቅ ርዝመት) ሲኖረው ከዚህ ውስጥ አሁን ላይ ቀሪ 14 ሜትር ግንባታ ይቀራል።
እንደዚህ አይነቱ ግንባታ በኢትዮጵያውያን ተቋራጭ ሲሰራ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፤ አብዛኛው ጊዜ ለቻይኖች ነበር የሚሰጠው።
ከዚህ በተጨማሪም ከፍተኛ ውኃ ቢመጣ በግድቡ ሳይሆን ማስተንፈሻ (Spillway) አለው። አጠቃላይ የስትራክቸር ሥራው በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል።
ፕሮጀክቱ አሁን ላይ 73.5 ከመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን በሚቀጥለው ዓመት ሙሉ ለሙሉ ትኩረታችንን ግድቡ ላይ አድርገን እንሰራለን።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከ17 ሺ አስከ 20ሺ ሄክታር መሬት በመስኖ የማልማት አቅም ሲኖረው ከአጠቃላይ የውኃ መጠኑ ደግሞ 32 ሜትር ኪዩቢክ የሚሆነው ለጎንደርና አከባቢው ንጹሕ መጠጥ ውኃ ለማቅረብ ግብዓት የሚውል ነው " ብለዋል።
የፕሮጀክቱ አማካሪ የሆነው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ተጠሪ መሐንዲስ የሆኑት ወርቅነህ አሰፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱን በመጪው ዓመት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን ገልጸውልናል።
ተጠሪ መሐንዲሱ በዝርዝር ምን አሉ ?
" ይህ ፕሮጀክት ቀድሞ ከነበረው ተቋራጭ ስንረከብ 60.3 በመቶ ሥራው ተጠናቆ ነበር። ይሄ አሰሪው በሚያውቀው ነው። ወደኋላ ተመልሶ የተሰሩ ሥራዎች አሉ ይህ ወደፊት ይስተካከላል።
ዲዛይኑ አጠቃላይ 50 የደለል ዓመት አለው። ከዚህም በላይ ከዚህም በታች የአገልግሎት እድሜ እንዲኖረው የሚያስችለው የተፋሰሱ አከባቢዎች ላይ የሚሰሩ የተፈጥሮ ጥበቃ ሥራዎች ናቸው። እኛ ሥጋታችን እሱ ነው በዚህ ዙሪያ ሰፊ የአከባቢ ጥበቃ ሥራ ይጠይቃል።
ለመጠጥ ውኃው 1.5 ኪሜ ከግድቡ እስከ ማጣሪያው እናወጣለን። የውኃ ማጣሪያው እና የስርጭት መስመሩ ሌላ ፕሮጀክት ነው" ብለዋል።
በተደጋጋሚ ለሚጠየቀው የጎንደር የመጠጥ ውኃ ችግር መፍትሄ ምን እየተሰራ ነው ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ደብሬ የኋላን አነጋግሯል።
ም/ከንቲባዋ ምን አሉ ?
" የጎንደር የንጹህ መጠጥ ውኃ ችግር የቆየ ችግር ነው። ይህንን ለመፍታት ልዩ ልዩ አማራጮችን አቅርበናል አንዱ የመገጭ የውኃ ፕሮጀከት ነው።
አማራጮቹ በፌደራል መንግስት ሥር ያሉ አማራጮች ናቸው። አብሮ ከግድቡ ጋር እንዲመረቅ ካስፈለገ አብሮ በትይዩ መቀጠል አለበት።
ልዩ ልዩ የዲዛይን ሥራዎች አልቀዋል። አሁን ይጀመራል ብለን እናምናለን፤ የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ውሳኔ ነው የሚጠበቀው " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የመገጭ የመስኖ ግድብ በሚቀጥለው በጀት ዓመት ይጠናቀቃል ተባለ።
በጎንደር ዙሪያ እየተገነባ ያለውና ከ16 ዓመታት በላይ የፈጀው የመገጭ የመስኖ ግድብ በቀጣይ በጀት አመት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
በ2001 ፕሮጀክቱ ሲጀመር፥ ለአከባቢው የመስኖ ፕሮጀክት እንዲሁም በጎንደርና አከባቢው በስፋት ለሚስተዋለው የመጠጥ ውኃ ችግር መፍትሔ ይሆናል ተብሎ እምነት ተጥሎበት ነበር።
ሥራው ሲጀመር ፕሮጀክቱ በ2.4 ቢሊዮን በጀት ቢሆንም በተባለው በጀትና ጊዜ መጠናቀቅ ባለመቻሉ የበርካቶች የዓመታት ጥናቄ ሆኖ ቆይቷል።
ፕሮጀክቱ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ከዚህ ቀደም ሥራ ላይ የነበረውን ተቋራጭ ውል በመሰረዝ ' ባይካ ' ከተባለ አዲስ ተቋራጭ ጋር በ14 ቢሊዮን ብር ካፒታል ውል ተገብቷል።
በዚህ ተቋራጭ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ጌታቸው አረጋ፥ የመገጭ የመስኖ የግድብ ፕሮጀክት የስትራክቸር ሥራ በዚህ ዓመት ነሐሴ ወር ላይ እንደሚጠናቀቅ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ሥራ አስኪያጁ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የመገጭ ግድብ 185 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውኃ የይዛል፤ ግድቡ ሲጠናቀቅ እስከ 5 ኪ.ሜ ወደ ኋላ ውኃ የሚተኛ ይሆናል።
የውኃ መቆጣጠሪያው (Intake Tower) አጠቃላይ 64 ሜትር (16 ፎቅ ርዝመት) ሲኖረው ከዚህ ውስጥ አሁን ላይ ቀሪ 14 ሜትር ግንባታ ይቀራል።
እንደዚህ አይነቱ ግንባታ በኢትዮጵያውያን ተቋራጭ ሲሰራ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፤ አብዛኛው ጊዜ ለቻይኖች ነበር የሚሰጠው።
ከዚህ በተጨማሪም ከፍተኛ ውኃ ቢመጣ በግድቡ ሳይሆን ማስተንፈሻ (Spillway) አለው። አጠቃላይ የስትራክቸር ሥራው በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል።
ፕሮጀክቱ አሁን ላይ 73.5 ከመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን በሚቀጥለው ዓመት ሙሉ ለሙሉ ትኩረታችንን ግድቡ ላይ አድርገን እንሰራለን።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከ17 ሺ አስከ 20ሺ ሄክታር መሬት በመስኖ የማልማት አቅም ሲኖረው ከአጠቃላይ የውኃ መጠኑ ደግሞ 32 ሜትር ኪዩቢክ የሚሆነው ለጎንደርና አከባቢው ንጹሕ መጠጥ ውኃ ለማቅረብ ግብዓት የሚውል ነው " ብለዋል።
የፕሮጀክቱ አማካሪ የሆነው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ተጠሪ መሐንዲስ የሆኑት ወርቅነህ አሰፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱን በመጪው ዓመት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን ገልጸውልናል።
ተጠሪ መሐንዲሱ በዝርዝር ምን አሉ ?
" ይህ ፕሮጀክት ቀድሞ ከነበረው ተቋራጭ ስንረከብ 60.3 በመቶ ሥራው ተጠናቆ ነበር። ይሄ አሰሪው በሚያውቀው ነው። ወደኋላ ተመልሶ የተሰሩ ሥራዎች አሉ ይህ ወደፊት ይስተካከላል።
ዲዛይኑ አጠቃላይ 50 የደለል ዓመት አለው። ከዚህም በላይ ከዚህም በታች የአገልግሎት እድሜ እንዲኖረው የሚያስችለው የተፋሰሱ አከባቢዎች ላይ የሚሰሩ የተፈጥሮ ጥበቃ ሥራዎች ናቸው። እኛ ሥጋታችን እሱ ነው በዚህ ዙሪያ ሰፊ የአከባቢ ጥበቃ ሥራ ይጠይቃል።
ለመጠጥ ውኃው 1.5 ኪሜ ከግድቡ እስከ ማጣሪያው እናወጣለን። የውኃ ማጣሪያው እና የስርጭት መስመሩ ሌላ ፕሮጀክት ነው" ብለዋል።
በተደጋጋሚ ለሚጠየቀው የጎንደር የመጠጥ ውኃ ችግር መፍትሄ ምን እየተሰራ ነው ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ደብሬ የኋላን አነጋግሯል።
ም/ከንቲባዋ ምን አሉ ?
" የጎንደር የንጹህ መጠጥ ውኃ ችግር የቆየ ችግር ነው። ይህንን ለመፍታት ልዩ ልዩ አማራጮችን አቅርበናል አንዱ የመገጭ የውኃ ፕሮጀከት ነው።
አማራጮቹ በፌደራል መንግስት ሥር ያሉ አማራጮች ናቸው። አብሮ ከግድቡ ጋር እንዲመረቅ ካስፈለገ አብሮ በትይዩ መቀጠል አለበት።
ልዩ ልዩ የዲዛይን ሥራዎች አልቀዋል። አሁን ይጀመራል ብለን እናምናለን፤ የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ውሳኔ ነው የሚጠበቀው " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ሳምንት ባልሞላ ጊዜ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል። ከ2009 ዓ/ም ጀምሮ ከ400 በላይ ሰዎች ተገድለዋል፤ ከ500 በላይ ደግሞ ቆስለዋል " - ኮሬ ዞን
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ሰሞኑን የታጠቁ አካላት አደረሱት በተባለ ጥቃት ሁለት ንጹሐን መገደላቸውን ፤ ባለፉት ዓመታትም ከ 400 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ተናግሯል።
በዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን የኮሚዩኒኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ አማረ አክሊሉ በሰጡን ቃል፣ " ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሁለት ሰዎች ህይወት በኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ በጸረ ሰላም ኃይሎች ምክንያት አልፏል " ብለዋል።
በወረዳው ዳኖ ቀበሌ ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ/ም አቶ ዮናስ ዱንአ፤ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ/ም አቶ ፊቴ ፊጋ የተባሉ አርሶ አደሮች በግብርና ሥራ ላይ እያሉ በታጣቂዎች ተኩስ ተከፍቶባቸው ሕይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።
ሰሞንኛውን ጥቃት የፈጸሙት፣ " የምዕራብ ጉጂ ዞን የጋላና ታጣቂዎች ናቸው። ማሳ ላይ ያሉ አርሶ አደሮችን ነው የሚያጠፉት። ፍላጎታቸው መሬቱን ማስለቀቅ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" አካባቢው ዘራፊ ቡድኖች የሚፈነጩበት ነው፤ አደብ የሚያስገዛ መንግስት አልተገኘም። ችግሮቹ የሚባባሱት በስርቆት ምክንያት ነው " ያሉት አቶ አክሊሉ፣ " ዳኖ ቀበሌ በአንድ ቀን ብቻ ከ70 በላይ ከብቶች ተነድተዋል/ተወስደዋል የዛሬ ሁለት ወራት ገደማ " በማለት አስታውሰዋል።
በጥቃቱ እስካሁን በአጠቃላይ ስንት ሰዎች ተገድለዋል ? በሚል ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ሁለት ሰዎች እንደተገደሉ ገልጸው፣ " ከ2009 ዓ/ም ጀምሮ ከ400 በላይ ሰዎች ሞተዋል፤ ከ500 በላይ ቆስለዋል " ሲሉ መልሰዋል።
ከግድያው ባሻገር፣ " ከ700 ሚሊዮን በላይ ንብረት ነው የወደመው። መንግስት ችግሩን አልፈታም። ሁለት ችግሮች አሉ፤ እነርሱም የወሰን ጥያቄና ጫካ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች ናቸው " ብለዋል።
ግድያውና ውድመቱ የተፈጸመው ከነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ/ም ጀምሮ እስከትላንት ድረስ መሆኑን አስረድተው፣ " ከነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ/ም ጀምሮ ለሦስት ጊዜያቶች እርቀ ሰላምም ተደርጓል፤ ግን እርቀ ሰላሞቹ ውጤታማ አልሆኑም። በተለያዩ አካባቢዎችም ስብሰባዎች ይካሄዳሉ የተወሰነ ሰላምም ያመጣሉ ግን ዘላቂ አይደለም" ሲሉ አስረድተዋል።
" ፎሌ " የሚባሉ መደበኛ ያልሆኑ ሚሊሻዎች በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱና ጎርካ ወረዳ ላይ "የወሰን ይገባኛል" ጥያቄም። እንዳላቸው፣ "የሸኔ" ታጣቂዎችም በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ በተደጋጋሚ እርቅ ቢፈጸምም መፍትሄ ስለማይቀመጥለት ጥቃቱ ለአመታት እያገረሸ እንደቀጠለ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ሰሞኑን የታጠቁ አካላት አደረሱት በተባለ ጥቃት ሁለት ንጹሐን መገደላቸውን ፤ ባለፉት ዓመታትም ከ 400 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ተናግሯል።
በዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን የኮሚዩኒኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ አማረ አክሊሉ በሰጡን ቃል፣ " ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሁለት ሰዎች ህይወት በኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ በጸረ ሰላም ኃይሎች ምክንያት አልፏል " ብለዋል።
በወረዳው ዳኖ ቀበሌ ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ/ም አቶ ዮናስ ዱንአ፤ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ/ም አቶ ፊቴ ፊጋ የተባሉ አርሶ አደሮች በግብርና ሥራ ላይ እያሉ በታጣቂዎች ተኩስ ተከፍቶባቸው ሕይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።
ሰሞንኛውን ጥቃት የፈጸሙት፣ " የምዕራብ ጉጂ ዞን የጋላና ታጣቂዎች ናቸው። ማሳ ላይ ያሉ አርሶ አደሮችን ነው የሚያጠፉት። ፍላጎታቸው መሬቱን ማስለቀቅ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" አካባቢው ዘራፊ ቡድኖች የሚፈነጩበት ነው፤ አደብ የሚያስገዛ መንግስት አልተገኘም። ችግሮቹ የሚባባሱት በስርቆት ምክንያት ነው " ያሉት አቶ አክሊሉ፣ " ዳኖ ቀበሌ በአንድ ቀን ብቻ ከ70 በላይ ከብቶች ተነድተዋል/ተወስደዋል የዛሬ ሁለት ወራት ገደማ " በማለት አስታውሰዋል።
በጥቃቱ እስካሁን በአጠቃላይ ስንት ሰዎች ተገድለዋል ? በሚል ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ሁለት ሰዎች እንደተገደሉ ገልጸው፣ " ከ2009 ዓ/ም ጀምሮ ከ400 በላይ ሰዎች ሞተዋል፤ ከ500 በላይ ቆስለዋል " ሲሉ መልሰዋል።
ከግድያው ባሻገር፣ " ከ700 ሚሊዮን በላይ ንብረት ነው የወደመው። መንግስት ችግሩን አልፈታም። ሁለት ችግሮች አሉ፤ እነርሱም የወሰን ጥያቄና ጫካ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች ናቸው " ብለዋል።
ግድያውና ውድመቱ የተፈጸመው ከነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ/ም ጀምሮ እስከትላንት ድረስ መሆኑን አስረድተው፣ " ከነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ/ም ጀምሮ ለሦስት ጊዜያቶች እርቀ ሰላምም ተደርጓል፤ ግን እርቀ ሰላሞቹ ውጤታማ አልሆኑም። በተለያዩ አካባቢዎችም ስብሰባዎች ይካሄዳሉ የተወሰነ ሰላምም ያመጣሉ ግን ዘላቂ አይደለም" ሲሉ አስረድተዋል።
" ፎሌ " የሚባሉ መደበኛ ያልሆኑ ሚሊሻዎች በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱና ጎርካ ወረዳ ላይ "የወሰን ይገባኛል" ጥያቄም። እንዳላቸው፣ "የሸኔ" ታጣቂዎችም በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ በተደጋጋሚ እርቅ ቢፈጸምም መፍትሄ ስለማይቀመጥለት ጥቃቱ ለአመታት እያገረሸ እንደቀጠለ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" አባት ተገድሏል ፤ እናት ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባታል " - ነዋሪዎች
አንድ የኤርትራ ወታደር ሁለት ሲቪሎች ላይ ተኩሶ አንድ ሰው ሲገድል ፤ ሌላ ሰው ማቁሰሉን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
የግድያና የማቁሰል ደርጊቱ የተፈጸመው በድንበር ከተማዋ ዛላኣንበሳ ሲሆን በአከባቢው የሚገኘውን ህዝብ ክፉኛ አሰቆጥተዋል።
ከትላንት በስቲያ አርብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ/ም በኤርትራ ወታደር በሲቪል የዛላንበሳ ነዋሪ ባልና ሚስት የተፈፀመውን ግፍ የሚመለከት መረጃ ለድህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈቀዱ የከተማዋ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ አጋርተውታል።
እንደ ነዋሪዎቹ ቃል ፥ በከተማዋ ሲቪል ለብሰው የአልኮል መጠጥ ሲቀማምሱ የዋሉ ሁለት የኤርትራ ወታደሮች ከሰዓት በኋላ ወደ መኖሪያ ካምፓቸው እያመሩ ሳለ ሁለት ህፃናት በቤታቸው አጠገብ ሲጫወቱ ያገኛሉ።
አንደኛው ወታደር ሰክሮ ስለነበር ህፃናቱን ከመስደብ አልፎ ይመታቸዋል።
ይህንን ተግባር በቅርብ ርቀት ሲመለከት የነበረው የህፃናቱ ወላጅ አባት ቀረብ ብሎ " ለምን መታሃቸው ? " ብሎ ጠይቆ ሳይጨርስ የሰከረው ወታደር የታጠቀው ሽጉጥ አውጥቶ ይተኩስበታል። አባትም ይወድቃል።
ተግባሩ ያስደነገጣት እናት እየጮኸች ባልዋ ወደ ወደቀበት ስትጠጋ ወታደሩ እሷም ላይ እንደተኮሰባት ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
አባት ትዳሩንና ልጆቹ ትቶ በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ተቀጥፏል።
እናት በተተኮሰው ጥይት ቀላል ጉዳት ደርሶባታል።
" ሌላኛው አብሮ የነበረው ወታደር ጉዳዩን ወታደር ከአረመኔያዊ ተግባሩ ባያስጥለው ኖሮ የጉዳቱ መጠን ካጋጠመው በላይ ይሆን ነበር " ሲሉ በቅርብ ርቀት ክስተቱን ያዩ የአይን እማኞች ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
አንድ የኤርትራ ወታደር ሁለት ሲቪሎች ላይ ተኩሶ አንድ ሰው ሲገድል ፤ ሌላ ሰው ማቁሰሉን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
የግድያና የማቁሰል ደርጊቱ የተፈጸመው በድንበር ከተማዋ ዛላኣንበሳ ሲሆን በአከባቢው የሚገኘውን ህዝብ ክፉኛ አሰቆጥተዋል።
ከትላንት በስቲያ አርብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ/ም በኤርትራ ወታደር በሲቪል የዛላንበሳ ነዋሪ ባልና ሚስት የተፈፀመውን ግፍ የሚመለከት መረጃ ለድህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈቀዱ የከተማዋ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ አጋርተውታል።
እንደ ነዋሪዎቹ ቃል ፥ በከተማዋ ሲቪል ለብሰው የአልኮል መጠጥ ሲቀማምሱ የዋሉ ሁለት የኤርትራ ወታደሮች ከሰዓት በኋላ ወደ መኖሪያ ካምፓቸው እያመሩ ሳለ ሁለት ህፃናት በቤታቸው አጠገብ ሲጫወቱ ያገኛሉ።
አንደኛው ወታደር ሰክሮ ስለነበር ህፃናቱን ከመስደብ አልፎ ይመታቸዋል።
ይህንን ተግባር በቅርብ ርቀት ሲመለከት የነበረው የህፃናቱ ወላጅ አባት ቀረብ ብሎ " ለምን መታሃቸው ? " ብሎ ጠይቆ ሳይጨርስ የሰከረው ወታደር የታጠቀው ሽጉጥ አውጥቶ ይተኩስበታል። አባትም ይወድቃል።
ተግባሩ ያስደነገጣት እናት እየጮኸች ባልዋ ወደ ወደቀበት ስትጠጋ ወታደሩ እሷም ላይ እንደተኮሰባት ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
አባት ትዳሩንና ልጆቹ ትቶ በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ተቀጥፏል።
እናት በተተኮሰው ጥይት ቀላል ጉዳት ደርሶባታል።
" ሌላኛው አብሮ የነበረው ወታደር ጉዳዩን ወታደር ከአረመኔያዊ ተግባሩ ባያስጥለው ኖሮ የጉዳቱ መጠን ካጋጠመው በላይ ይሆን ነበር " ሲሉ በቅርብ ርቀት ክስተቱን ያዩ የአይን እማኞች ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍትህ እንዲረጋገጥ እሻለሁ " - ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ ትላንት አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የተገደለበት 4ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 3ኛው ዓመት " የሃጫሉ አዋርድ " የሽልማት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች እውቅና አግኝተዋል፡፡ በዚሁ መድረክ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ባለቤት እና…
ፎቶ ፦ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ 5ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 4ኛው ዓመት " የሃጫሉ አዋርድ " የሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች በመርሃግብሩ እውቅና አግኝተዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ፎቶ ክሬዲት ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን እና ኦኤምኤን
@tikvahethiopia
በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች በመርሃግብሩ እውቅና አግኝተዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ፎቶ ክሬዲት ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን እና ኦኤምኤን
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam ዩኒቨርሲቲዎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞችን ዛሬ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም መቀበል ጀምረዋል፡፡ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። በወጣው መርሐግብር መሰረት ሰኞ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ይጀምራል፡፡ ፈተናውን…
#NationalExam🇪🇹
ነገ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መሠጠት ይጀምራል።
ፈተናውን ለመውሰድ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ለገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችም ዛሬ የግንዛቤ ማስጨበጫ (Orientation) ሲሰጥ ውሏል።
ተፈታኞቹ በዩኒቨርሲቲዎቹ በሚኖራቸው ቆይታ ስለሚያገኙት አገልግሎቶች (ምግብ፣ መኝታ፣ ጤና...) እና ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጓል።
በተጨማሪም በፈተና ወቅት ስለሚከተሏቸው ህግና ደንቦች እንዲሁም ተያያዥ ስለሆኑ የፈተና ሂደቶችና አተገባበሮችን በሚመለከት ገለጻ ተሰጥቷቸዋል።
ነገ የሚጀመረው የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሚወስዱት ፈተና ይጀምራል።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
ነገ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መሠጠት ይጀምራል።
ፈተናውን ለመውሰድ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ለገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችም ዛሬ የግንዛቤ ማስጨበጫ (Orientation) ሲሰጥ ውሏል።
ተፈታኞቹ በዩኒቨርሲቲዎቹ በሚኖራቸው ቆይታ ስለሚያገኙት አገልግሎቶች (ምግብ፣ መኝታ፣ ጤና...) እና ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጓል።
በተጨማሪም በፈተና ወቅት ስለሚከተሏቸው ህግና ደንቦች እንዲሁም ተያያዥ ስለሆኑ የፈተና ሂደቶችና አተገባበሮችን በሚመለከት ገለጻ ተሰጥቷቸዋል።
ነገ የሚጀመረው የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሚወስዱት ፈተና ይጀምራል።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM