Telegram Web
በዓለ ደብሚ ቁስቋም
እንኳን አደሹሰን

ደብሚ ቁስቋም በደቡብ ግብፅ ዹሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ደብሚ ቁስቋም እመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስን እንዲሁም ቅዱስ ዮሎፍንና ቅድስት ሰሎሜን ይዛ ኚስደት ሲመለሱ ያሚፉበት ቊታ ነው፡፡

ይህም በቅዱስ ወንጌል እንደተጻፈ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ ዚእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኀል ለአሹጋዊው ዮሎፍ በሕልሙ ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሜሜ›› ባለው መሠሚት ዹተፈጾመ ነው፡፡ (ማቮ. ፪፥፲፫-፲፭)

ዚክርስቶስ ስደቱ ቀድሞ በነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹. . . እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተቀምጩ ወደ ግብፅ ይመጣል፡፡ ዚግብፅም ጣዖታት በፊቱ ይዋሚዳሉ›› ተብሎ በተነገሹው መሠሚት ዹተፈጾመ ነው፡፡ ነቢዩ ፈጣን ደመና ያለው ጌታቜን በእመቀታቜን በቅድስት ድንግል ጀርባ ላይ ሆኖ ወደ ግብፅ መውሚዱን ለመግለጜ ነው፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩) በስደቱም ጣዖታተ ግብፅ እዚተሰባበሩ ሲወድቁፀ በእነርሱም አድሚው ሰውን ሲያስቱ ዚነበሩ አጋንንትም ሲሞሹ ታይተዋል፡፡

ደግሞም ጌታቜን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክሹ ኚይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ ዹነበሹው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደፀ በዚህም አጋንንትን ኹሰው ልቩና አውጥቶ አሳደደ፡፡

እመቀታቜንም ልጇን ይዛ ኚስደት ስትመለስ ያሚፈቜበትን ተራራ ደብሚ ቁስቋምን ባሚኚቜው ቀደሰቜውምፀ ይህ ተራራ ዹተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ ዚእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኊፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም እንዲህ አለፀ ‹‹ይህም ኚሀገሮቹ ሁሉ ተራሮቜ ዚሚበልጥ (ዹተለዹ) ኹፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ ዚእግዚአብሔር ልጅ ወዶታልፀ አክብሮታልምናፀ ኹዓለም ሀገሮቜ ሁሉ ኚተቀደሰቜ እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ኚመላእክት ቀት ያድር ዘንድ አልወደደምፀ ቢታንያንም አልመሚጠም፡፡
ኚተራራው ላይ ባለቜ ገዳም ቀት ውስጥ አደሹ እንጂፀ ነቢዩ ዳዊትፀ ዚጜዮንን ተራራ ወደደፀ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡››
‹‹አንተ ተራራ ሆይ ዚእግዚአብሔር ማደሪያ በሆንህ ጊዜ በኪሩቀልና በሱራፌል መካኚል ፍጹም ደስታ ተደሚገ፡፡ ዚመላእክት ሠራዊት ቅዱስ ዹሆነ ፈጣሪያ቞ውንና ጌታ቞ውን ይታዘዙ (ያገለግሉ) ነበር፡፡

አንተ ተራራ ሆይ ያደሚብህ ጌታቜን ስለሆነ ኚተራሮቜ ሁሉ ኚደብሚ ሲናም ይልቅ ኹፍ ኹፍ አልህፀ ጌታቜን በደብሚ ሲና ባሚፈ ጊዜ ፍጹም ደስታ፣ ታላቅ ብርሃንም በሆነ ጊዜ መቅሚብና መመልኚት ኹሙሮ በቀር ዚቻለ ዚለም፡፡

እርሱም ቢሆን ፊቱን ማዚት አልቻለም፡፡ ሥጋ ለባሜ ሁሉ እርሱን ዐይቶ በሕይወት መኖር ዚሚቻለው ዚለምና፡፡ እኛ ግን አዚንፀ ኹዚህ ማደሩንም ተሚዳንፀ ዳግመኛም ንጜሕት በሆነቜ በማርያም ዘንድ አዚነው፡፡ ቅድስት ኚሆነቜ ኚእመቀታቜን ማርያም ዘንድ በቀተልሔም ስለ እኛ በተዋሐደው ሥጋ በጹለማና በሞት ጥላ ሥር ያለን እኛን ኚ቞ርነቱና ሰውን ኚመውደዱ ዚተነሣ መጥቶ አዳነንፀ ኹዓለም ሁሉ ይልቅ ጣዖትን በማምለክ ሲበድሉም ወደ ግብፅ  ሀገር ወርዶ በእነርሱ ላይ ዚመለኮትነት ብርሃኑን በማብራት ታላቅ ዹሆነ ክብሩን ገለጠ››፡፡ (ድርሳነ ማርያም)
ኅዳር ፮ ቀንን ዹሚነበበው ዚመጜሐፈ ስንክሳር ክፍል ጌታቜን መድኀኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዳግመኛም በኋላ ዘመን ሐዋርያትን በደብሚ ቁስቋም ሰብስቊፀ ታቊትንና ቀተ ክርስቲያኑን አክብሮ ዚቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙን እንደ ሰጣ቞ውፀ እኛንም ለዚህ ክብር ዹበቃን እንሆን ዘንድ ዚእግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልንፀ አሜን፡፡

ምንጭፀ ድርሳነ ማርያም መጜሐፍ ትርጉም
https://www.tgoop.com/DIYAKONAE
ኅዳር ጜዮን
"ጜዮን" ማለት "ጾወን አምባ፣ መጠጊያ" ማለት ነው:: ጜዮን ዹሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጜላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቀተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል፡፡

ኅዳር ፳፩ ቀን በታቊተ ጜዮን ዹተፈጾሙ ታላላቅ ተአምራት ዚሚታሰቡበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ቀን ቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ዚታቊተ ጜዮንን ተአምራት እግዚአብሔር ቃል ቅድስት ድንግል ማርያምን ታቊቱ አድርጎ ኹፈጾማቾው ታላላቅ ዚድኅነት ሥራዎቜ ጋር በማነጻጞር እመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም በነገሹ ድኅነት ውስጥ ያላትን ድርሻ በስፋት ታስተምራለቜ፡፡

ነቢዩ ሙሮ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጞልዮና ጹሞ ዐሥርቱ ቃላት ዚተጻፈበትን ጜላት ኚእግዚአብሔር ዹቃል ኪዳኑን ታቊት ‹ታቊተ ጜዮንን› እንደተቀበለ መጜሐፍ ቅዱስ ይገልጻል፡፡

ታቊተ ጜዮን ኹማይነቅዝ እንጚት ዚተቀሚጞቜበት ምክንያት ዚእመቀታቜን ድንግል ማርያምን ንጜሕና ለማመልኚት ነው፡፡ በውስጥም በውጪም በጥሩ ወርቅ ዚተለበጠቜ መሆኗ ደግሞ ዚእመቀታቜን ድንግል ማርያም ቅድስናዋንና በሁለት ወገን ድንግል ዹመሆኗ ምሳሌ ነው፡፡

ንጉሥ ዳዊት ዚእግዚአብሔርን ዹቃል ኪዳን ታቊት ኚአቢዳራ ቀት ወደ ጜዮን ኹተማ ባስመጣበት ወቅት በታቊቷ ፊት በሙሉ ኃይሉ በደስታ እዚዘለለ ለእግዚአብሔር በዝማሬ ምስጋና አቅርቧል፡፡ ‹‹ለንጉሥ ዳዊትም “እግዚአብሔር ዚአቢዳራ ቀት ዹነበሹውን ሁሉ ስለ እግዚአብሔር ታቊት ባሚኚ” ብለው ነገሩት፡፡

ዳዊትም ሄዶ ዚእግዚአብሔርን ታቊት ኚአቢዳራ ቀት ወደ ራሱ ኹተማ በደስታ አመጣት፡፡ ኚእርሱም ጋር ዚእግዚአብሔርን ታቊት ዹተሾኹሙ ሰባት መሰንቆ ዚሚመቱ መዘምራን ነበሩፀ በሬዎቜንና በጎቜን ይሠዉ ነበር፡፡ ዳዊትም በእግዚአብሔር ፊት በገና ይደሚድር ነበር›› እንዲልፀ ነቢዩ ዳዊት በቃል ኪዳኑ ታቊት ፊት ዹተቀኘው ለሰው ልጆቜ ሁሉ ዚመዳናቜን ምክንያት ዚሆነቜውን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስን ሲያመስገን ነው፡፡ (፪ሳሙ.፮፥፲፪-፲፬)

ታቊተ ጜዮን እስራኀል ዚዮርዳኖስን ባሕር ለመሻገር በተ቞ገሩ ጊዜ ነቢዩ ኢያሱ እግዚአብሔር አምላክ በነገሹው መሠሚት ካህናቱ ዹቃል ኪዳኑን ታቊት ይዘው በሕዝቡ ፊት ወደ ዮርዳኖስ እንዲሄዱ ነገራ቞ውፀ እነርሱም እንደታዘዙት አደሚጉፀ ታቊቱን ዚተሞኚሙት ዚካህናቱ እግሮቜ በውኃው ዳር ሲጠልቁ ኹላይ ዹሚወርደው ውኃ ቆመፀ ዚእግዚአብሔርን ዹቃል ኪዳን ታቊት ዹተሾኹሙ ካህናት በዮርዳኖስ መካኚል በደሹቅ መሬት ጾንተው ቆመው ነበርፀ ሕዝቡም ሁሉ ዮርዳኖስን ፈጜመው እስኪሻገሩ ድሚስ እስራኀል ሁሉ በደሹቅ መሬት ተሻገሩ፡፡ (ኢያ. ፫፥፩-፲፯)

እስራኀላውያን በመካኚላ቞ው ዹቃል ኪዳኑ ታቊት በያዙ ቁጥር በጊርነታ቞ው ሁል ጊዜ ያሞንፉ ነበሩ፡፡ ነገር ግን ልዑል እግዚአብሔር ሕዝበ እስራኀል ስለበደሉት እንዲሁም ዚኀሊ ልጆቜ አፍኒንና ፊንሐስ በደላቾውና ክፋታ቞ው ስለበዛ ታቊተ ጜዮን ተማርካ ወደ ፍልስጥኀም ሄደቜ፡፡ በዚያ በአሕዛብ ምድርም ልዩ ልዩ ተአምራትን እያደሚገቜ ፍልስጥኀማውያንን ስለአስጚነቀቻ቞ው ዚፍልስጥኀማውያን አለቆቜ ዚቃልኪዳኑን ታቊት ልዩ ልዩ ገጾ በሚኚቶቜን አስይዘው ወደመጣቜበት በሠሹገላ አድርገው በክብር ሞኝተዋታል፡፡ (፩ኛ.ሳሙ. ፭፥፩-፲፭)
ሀገራቜን ኢትዮጵያም በንግሥተ ሳባ አማካኝነት ለታቊተ ጜዮን መቀመጫ እንድትሆን ዚእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኗል፡፡ ይህም እንዲህ ነበርፀ ንግሥተ ሳባ ዚንጉሥ ሰሎሞንን ጥበብ ለማድነቅ ምድሚ እስራኀል ድሚስ መጓዟን ተኚትሎ ኚንጉሡ ቀዳማዊ ምኒልክን ፀነሰቜ፡፡

ቀዳማዊ ምኒልክ ኹአደገ በኋላ አባቱን ሊጠይቅ ሂዶ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ አብሚውት አንድ ሺህ ሁለት መቶ እስራኀላውያን ዚበኩር ልጆቜ፣ ሊስት መቶ ዐሥራ ስምንት በአዛርያስ ዚሚመሩ ሌዋውያን ካህናትም አብሚውት ለጉዞ ተነሡ፡፡ ዚብሉይ ኪዳን መጻሕፍትንና ሌሎቜ በርካታ ቁሳቁሶቜን ይዘውም ነበር።

ነገር ግን ታቊተ ጜዮንን አዛርያስና ካህናቱ ተማክሹው ቀዳማዊ ምኒልክ እንኳን ሳይሰማ በምሥጢር ይዘዋት ሊመጡ ተስማሙ፡፡ ዕቅዳ቞ውን ለማሳካት በታቊተ ጜዮን አምሳያ ሌላ ታቊት አዘጋጅተው ለመሄድ በሚነሡበት ዕለት ሌሊትም ወደ ቀተ መቅደስ ይዘውት ሄዱ፡፡

ኚቀተ መቅደስ ሲደርሱም ዚእግዚአብሔር ፈቃድ ነበርና ዚቀተ መቅደሱ በር ተኚፍቶ እና ውስጡም በብርሃን ተሞልቶ ታቊተ ጜዮንም ኚመንበሯ በመነሣት ኹፍ ብላ አገኟት። በዚህም ዹአምላክን ፈቃድ ተሚድተውና እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በፍጥነት ይዘዋት ወጡ፡፡ በአምሳያዋ ዚሠሩትንም ቅርፅ በመንበሩ ላይ አስቀምጠው ሄዱ።

ዚንጉሡ ወታደሮቜ በፍጥነት ቢጓዙም ቀዳማዊ ምኒልክ እና አዛርያስ ታቊተ ጜዮንን ይዘው ሲጓዙ እጅግ ፍጣን ስለበር ሊደርሱባ቞ው አልቻሉም። መጜሐፈ ክብሚ ነገሥት ይህንን ሲጠቅስ ‹‹ኚመሬት አንድ ክንድ ያህል ኹፍ ብለው ይሄዱ ነበር›› በማለት ይገልጞዋል። ባሕሚ ኀርትራን ኚተሻገሩና ግብፅ ኚደሚሱ በኋላ ዕሚፍትን ባደሚጉ ጊዜ አዛርያስ ለቀዳማዊ ምኒልክ ታቊተ ጜዮንን ይዘዋት እንደመጡ ነገሚው፡፡

አያይዞም ‹‹አንተም ብትሻ ታቊቷንም ወደ ሀገሯ ልመልሳት ብትል አትቜልምፀ አባትህ ሰሎሞንም ሊወስዳት ቢመጣ አይሆንለትም›› አለው። ኚቊታ ቊታ ይዣት እንቀሳቀሳለው ቢልም ያለ ፈቃዷ ምንም እንደማያደርግና ሁሉ ነገር በአምላክ መልካም ፈቃድ እንደሚፈጞም ነገሚው። ቀዳማዊው ምኒልክም ይህን ሲሰማ ተደሰተፀ ሕዝቡና ሠራዊቱ በሙሉ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑፀ ኚግብፅ ምድር ወጥተው እስኚ ኢትዮጵያ በታላቅ እልልታና ሆታ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መጡ።

ኅዳር ፳፩ ቀን አክሱም በደሚሱ ጊዜም እናቱ ንግሥተ ሳባ ተቀበለቜውፀ ደስታና እልልታውን ተመልክታ ያገኙት ነገር እንዳለ ብትጠይቀው ታቊተ ጜዮንን እንዳመጧት ነገራት፡፡ ዚእርሷም ደስታ እጥፍ ድርብ ሆነ። ታቊቷንም በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጜዮን ማርያም ቀተ ክርስቲያን አስቀመጡአት፡፡

ኚዚያም ዘመን ጀምሮ በዚዓመቱ ኅዳር ፳፩ ቀን ብዙ ምክንያቶቜ ቢኖሩም በታቊተ ጜዮን ዹተፈጾሙ ታላላቅ ተአምራትን በማሰብ ቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ታኚብራለቜ፡፡
         ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
ምንጭፀ
ክብሚ ነገሥት ተርጓሚ ሥርግው ገላው (1994 ዓ.ም)
መዝገበ ታሪክ ቊጥር 1 (መምህር ኅሩይ ኀርምያስ)
❗#ትውፊት_ማለት_ምን_ማለት_ነው?❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔎👉 እንደ ቀተ ክርስቲያናቜን አስተምሮ ቀተ ክርስቲያናቜን ዚምትመራበት 3 ህግጋቶቜ አሏት። እነርሱም ፊ
                        👉(1) ፊ ዶግማ
                        👉(2) ፊ ቀኖና
                        👉(3) ፊ ትውፊት ና቞ው።

🔵👉 እግዚአብሔር ቢፈቅድ ዛሬ ክፍል (3) ትውፊት ማለት ምን እንደሆነ በአጭሩ እንመለኚታለን።

           🔎👉
#ትውፊት_ማለት_ምን_ማለት_ነው?

🔎👉 ትውፊት ማለት አወፈዹ ኹሚለው ዚግእዝ ግሥ ዚመጣ ሲሆን ውርስ፣ ቅብብል ተብሎ ይተሚጎማል፡፡ ትውፊት ቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ትምህርቶቿን ጠንቅቃ ኚያዘቜበት እና ልጆቿንም ኚምትመራባ቞ው ሊስቱ ዹመሠሹተ እምነት ምንጮቜ ውስጥ አንደኛው ነው፡፡

🔷👉 ዚቀተ ክርስቲያን መሠሹተ እምነት ተብለው ዚሚጠቀሱት፡- ዶግማ፣ ቀኖና እና ትውፊት ሲሆኑ እነዚህ መሠሚቶቜ ቅድስት ቀተ ክርስቲያንን ሳትለወጥና ሳትበሚዝ እንደ ደመቀቜ ኚትውልድ ወደ ትውልድ እንድትተላለፍ አድርገዋታል፡፡ ለቀት መቆም ብቻ ሳይሆን ቀቱ ዕድሜ እንዲኖሚውም ዚሚያደርገው ዚመሠሚቱ ጥንካሬ ነው፡፡

🔷👉 በዚህም መሠሚት ትውፊት አንድ ሰው ኚእርሱ በፊት ኹነበሹው ማኅበሚሰብ ዹሚቀበለውና ዹሚወርሰው እምነት፣ ባህል፣ ዹአኗኗር ዘይቀ፣ 
ወዘተ ሲሆን ሒደቱም በዚህ ሳያበቃ እርሱም በተራው ለተተኪው ዚሚያስተላልፈው ነው፡፡

🔎👉 ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኀል አልታዬ ስለ ትውፊት እንዲህ በማለት ማብራሪያ ይሰጣሉ፡-“ትውፊት በቃል ወይም በጜሑፍ ወይም በተግባር እንቅስቃሎ ኚአንዱ ወደ ሌላው ዹሚተላለፍ ታሪክ፣ ትምህርት፣ ባህል፣ ወግና ሥርዓት ነው፡፡ ትውፊት በተጚባጭ በትክክል ዹተፈጾመ እንጂ ተሚት አይደለም፡፡ ኹሕገ ልቡና ወደ ሕገ ኊሪት፣ ኹሕገ ኊሪት ወደ ሕገ ወንጌል፣ በቅብብሎሜ ዚመጣ ዹተወሹሰና ለተኚታዩ ትውልድ ዹተላለፈ ነው፡፡

🔵👉 ትውፊት ልማደ ሀገርን ሕገ እግዚአብሔርን ባህለ ሃይማኖትን ሁሉ ዚሚያጠቃልልና እንደ መንፈሳዊ ሕግ ሆኖ ሊያዝ ዚሚቜል ነው፡፡” ይላሉ (ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኀል አልታዬፀ ፈለገ ጥበብ መጜሔት ፪ኛ ዓመት ቁጥር ፲፭/፲፱፻፺፪ ዓ.ም. ገጜ ፲፭)

🔎👉 ትውፊት ኚትውልድ ወደ ትውልድ በሊስት መንገዶቜ ዹሚተላለፍ ሲሆንፀ እነርሱም፡- ዚሚዳሰስ፣ ዚማይዳሰስ እና በቃል ይተላለፋሉ፡፡

🔷👉 አንድን ትውፊት ክርስቲያናዊ ነው ይምንለው፩

👉 1) ቅዱሳን አበው በኑሮአ቞ው ዚገለጡት ማለትም ዚተናገሩት ዚሰሩትና ያስተማሩት ሲሆን
👉 2) በቀተ ክርስቲያን ተጠብቆ ዚሚሰራበት ሲሆን
👉 3) እኛን ኹቀደሙ አበው ጋር አንድ ዚሚያደገንፀ አሰሹ ፍኖታ቞ውን እንድንኚተል ዚሚያበቃን ሲሆን ነው።

🔎👉 "እግዚአብሔርፊ ሕዝቡን ወደ እኔ ሰብስብ፥ በምድርም በሕይወት በሚኖሩበት ዘመን ሁሉ እኔን መፍራት ይማሩ ዘንድ፥
ልጆቻ቞ውንም ያስተምሩ ዘንድ ቃሌን አሰማቾዋለሁ ብሎ
በተናገሹኝ ጊዜ በአምላክህ በእግዚአብሔር ፊት በኮሬብ
በቆምህበት ቀን ዓይኖቜህ ያዩትን ነገር እንዳትሚሳ፥ በሕይወትህም
ዘመን ሁሉ ኚልብህ እንዳይወድቅ ተጠንቀቅ፥ ነፍስህንም በትጋት
ጠብቅ ለልጆቜህም ለልጅ ልጆቜህም አስታውቀው"። ዘዳ.4:9-
10

🔎👉 በአጭሩ ይሔን ይመስላል አነሳስቶ ያስጀመሚን አስጀምሮም ያስፈፀመን ዚአባቶቻቜን አምላክ ይክበር ይመስገንልን።

       ❗ለሁሉም እንዲደርስ ላይክ ሌር አድርጉ❗

።።።።
#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
    ።።።።።
#ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
     ።።።።።
#ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

 

ፔጁን
#Like_Follow_Share በማድሚግ ትክክለኛ ኊርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መሹጃ ያግኙ
https://www.tgoop.com/tmhrteorthodo
❗#ሥግደት_ዚማይሰግባ቞ው_ቀናቶቜ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔎👉 ኊርቶዶክሳዊት ቀተ ክርስቲያን በሃይማኖት ይዘትም ሆነ በሃይማኖት ሥርዐት ፍጜምት ነቜ፡፡ ዚሃይማኖት ይዘቷ (ዶግማዋ) ይህ ይቀሹዋል ተብሎ ዚማይጚመርበት በእግዚአብሔር አንድ ጊዜ ፍጹም ሆኖ ለቅዱሳን ዹተሰጠ ነው፡፡

🔵👉 (ይሁዳ 3) እግዚአብሔርን ዚምታመልክበት ሥርዐትም እንዲሁ መንፈስ ቅዱስ በመራ቞ው ቅዱሳን ሰዎቜ ዹተቀነነ ቅዱስ ሥርዐት ነው፡፡ ጊዜንና ቊታን በመዋጀትም (ግንዛቀ ውስጥ በማስገባትም) እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ሥርዐትን እንድትሠራ ቀኖና አለ፡፡ ኹዚህ አንጻር ስግደትንም በተመለኹተ መቜ ሊሰገድ እንደሚገባና መቜ እንደማይሰገድ ሥርዐትን ሠርታልናለቜ እንጂ እንዲሁ በዘፈቀደ እንዲተገበር ቾል አላለቜም፡፡

🔎👉 ኹሁሉ አስቀድሞ ግን እንደ ቀተ ክርስቲያናቜን አስተምህሮ መሠሚት ያሉትን ዚአሰጋገድ አይነቶቜ ማወቅ ያስፈልጋል በመሆኑም
#ሊስት አይነት #ዚስግደት_አሰጋገድ_አይነት_አሉ ። እነሱም ፊ

(1ኛ)፩
#አድንኖ ስግደት ይባላል።ይህም ማለት እራስን ዝቅ አድርጎ ወገብን ጎበስ በማለት ጉልበትና ግንባር ምድር ሳይነካ ዹምንቃናው ማለት ነው።

(2ኛ)፩
#አስተብርኮ ይባላል ይህም አሰጋገድ በጉልበት ወድቆ ግንባር መሬት ሳይነካ ዚምንነሳው ዚስግደት አይነት ነው።

(3ኛ)፩
#ሠጊድ ይባልላ። ይህ አግጋገድ ሙሉ በሙሉ በጉልበት መሬት ላይ በመውደቅ ግባርን መሬት በማስነካት ዹምንሰግደው ዚስግደት አይነት ነው።

🔵👉 ታዲያ ኚእነዚህ ዚአሰጋገድ አይነቶቜ በአምስቱ (5) ዚግዝት በዓላት ዹማይሰገደው ዚትኛው ዚአሰጋገድ አይነት ነው ስንል አባቶቻቜን በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው እስኚዛሬ ያስተማሩን ያስቀመጡልን ሠጊድ ዹምንለውን ስግደት ነው።

🔎👉 ስለዚህ ዚአሰጋገድ አይነቶቹን ኚተመለኚትን ዘንዳ ይህንን ሠጊድ ዹምንለውን ዚአሰጋገድ አይነት ዚማንሰግድባ቞ውን አምስቱን ዚግዝት ዓላት ደግሞ እንመልኚት !

     🔎👉 ሥግደት ዚሚሰገድባ቞ው ጊዜያት እንዳሉት ሁሉ ዚማይሰገድባ቞ው ጊዜያት አሉት ዚግዝት በዓላት አምስት ሲሆኑ
እነርሱም :- 1 👉ወር በገባ በ29 
#ዚወልድ_በዓል፣
              🔎 ዚነጻነት ቀን ጌታ ዚተወለደበት ቀን ስለሆነ።

          2 👉ወር በገባ በ 21
#ዚእመቀታቜን_በዓል፣
        🔎ዚነፍሳቜን ዕሚፍት፥ ነጻ ዚወጣንባት ስለሆነ።

           3 👉ወር በገባ በ 12
#ዚቅዱስ_ሚካኀል በዓል፣
          🔎ራዕ᎐፲፪ ሰይጣን ዚወደቀበት ቀን ስለሆነ።

          4 👉
#ቀዳሚት_ሰንበት (ቅዳሜ)
             🔎ጌታ ኚስራው ያሚፈበት ቀን ስለሆነ

          5 👉እሑድ_ሰንበት (ሰንበተ ክርስቲያን ና቞ው።
           🔎ጌታ ኚሙታን መካኚል ተለይቶ ዚተነሳበት ቀን ዚዕሚፍት ቀን ስለሆነ ።
❗በእነዚህ ቀናቶቜም ሠጊድ ዹምንለው ስግደት አይሰገድም❗

🔎👉 ኹነዚህ በተጚማሪም ሥግደት ዚማይሰገድባ቞ው ጊዜያት ዚሚኚተሉት ናቾው !

❗1ኛ.
#በዕለተ_እሑድ❗

🔵👉ኚአልቊ ነገር ወይም ኹምንም ዹተፈጠሹ ፍጥሚት ሁሉ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ጠፍቶ ወደ ምንምነት ሲቀዚር ኹማይጠፉ ኚአምስቱ ፍጥሚታት አንዷ ሰንበት ናት፡፡ ጌታ ዚተነሣባት ፣ ዳግምም ዚሚመጣባት ዕለት ናት፡፡ በዚህና በሌሎቜ ምክንያቶቜም ሰንበተ ክርስቲያን እሑድ በዓል ነቜ፡፡

🔎👉 ስለዚህ በዕለተ እሑድ መስገድ ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ይህንን ፍትሐ ነገሥቱ እንዲህ በማለት ይገልፀዋል፡- “ኚአድንኖና ኚአስተብርኮ በቀር እስኚ ምድር መስገድን ዚሚተዉባ቞ው ዚታወቁ ጊዜያቶቜ እነዚህ ና቞ው፡፡ ኒቅያ 20፣ በዕለተ እሑድና በበዓለ ሃምሳ ወራት፣ ” ፍት.መን. አን. 14 ቁ. 537 ይህንን ይበልጥ ሲያጞናው በሰንበታትና በበዓላት አንቀጹ እንዲህ ሲል ደግሞታል፡- “በእሑድና በተኚበሩት በዓላት ቀን ስግደት አይገባምፀ እነዚህ ዚደስታ ቀኖቜ ናቾውና” ፍት. መን. አን. 19 ቁ. 715።

❗2ኛ.
#በበዓለ_ሃምሳ_ወራት❗

🔎👉 በዓለ ሃምሳ ዚፍስሐና ዹሰላም ጊዜ ነው፡፡ ስሙ እንደሚጠቁመው ሃምሳውም ቀን በሙሉ በዓል ነው፡፡ በዓል ስለሆነም እንደ ፋሲካና እንደ ልደት እንበላበታለን እንጂ ሚቡዕና አርብ ቢሆን እንኳን አንጟምበትም፡፡ በበዓልነቱ ጟም እንደተሻሚበት ስግደትም እንዲሁ ይሻርበታል፡፡ ኹላይ እንዳዚነው ፍትሐ ነገሥቱም በፍት.መን. አን. 14 ቁ. 537 በእሑድ መስገድን ሲኚለክል በበዓለ ሃምሳም እንዲሁ ኚልክሏል፡፡

❗ 3ኛ.
#በጌታቜን_በዓላት❗

🔵👉 ፍትሐ ነገሥቱ “በእሑድና በተኚበሩት በዓላት ቀን ስግደት አይገባምፀ እነዚህ ዚደስታ ቀኖቜ ናቾውና” (ፍት.መን.
አን. 19 ቁ. 715) ካለ በኋላ “ዚተኚበሩት በዓላት” ያላ቞ው ዚትኞቹን እንደሆነ ሲዘሚዝር ትስብእት/ጜንሰት ፣ ልደት ፣ ጥምቀት ፣ ሆሣዕና ፣ ትንሣኀ ፣ ዕርገት ፣ በዓለ ሃምሳ ፣ ደብሚ ታቊር በማለት ኚጌታ ዘጠኝ ዐበይት በዓላት 8ቱን ይገልፃል፡፡ ሳይገለፅ ዹቀሹው ስቅለት ነውፀ ያልተገለፀበትም ምክንያት በስቅለት ስግደት ስለማይኚለኚል ነው፡፡

🔎👉 ስለዚህ ኚስቅለት በቀር በጌታ ዐበይት በዓላት (በተቀሩት በ8ቱ) ስግደት ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ፍትሐ ነገሥቱ ይህንን ሲያጞና በአንቀጜ 14 እንዲህ ብሏል፡- “መስገድን ዚሚተዉባ቞ው ዚታወቁ በዓላት እነዚህ ናቾው.... ኒቅያ 32፣ በጌታቜን በዓላትና በእመቀታቜን በዓላት” ፍት.መን. አን. 14 ቁ. 536-537፡፡

❗4ኛ.
#ዚእመቀታቜን_በዓላት❗

🔎👉 ኹላይ ያዚነው ዚፍትሐ ነገሥት ንባብ በፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536-537 ድሚስ በጌታ በዓላት መስገድ እንደተኚለኚለው ሁሉ በእመቀታቜን በዓላትም መኹልኹሉን ይጠቁመናል፡፡

❗5ኛ
#ሥጋውንና_ደሙን_ኹተቀበሉ_በኋላ❗

🔎👉 ዚሥርዐት ምንጫቜን ዹሆነው ፍትሐ ነገሥት አሁንም በዚህ ዙሪያ እንዲህ ብሏል፡- “መስገድን ዚሚተዉባ቞ው ዚታወቁ በዓላት እነዚህ ናቾው... ሥጋውንና ደሙን ኹተቀበሉ በኋላ” ይላል፡፡ ፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536-537፡፡ ሥጋውንና ደሙን ኹተቀበልን በኋላ ኚሚሰገድለት እንጂ ኹማይሰግደው ጋር አንድ መሆናቜንን ለማጠዹቅና ለቅዱስ ሥጋውና ለክቡር ደሙ ክብር ስንል ዝቅ ብለን አንሰግድም።

    🔵👉ለሌቜም እንዲደርስ በቅንነት
                 ሌር አድርጉ !
።።።
#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
       ።።።።።
#ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
       ።።።።።
#ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
       ህዳር 28/2017 ዓ.ም
             

ፔጁን
#Like_Follow_Share በማድሚግ ትክክለኛ ኊርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መሹጃ ያግኙ

🔎👉 በ቎ሌግራም | Telegram
       👇👇👇👇👇👇
https://www.tgoop.com/sratebetkrstyane
ዹተቀደደ ልብስ መልበስ
።።።.።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
መጜሐፍ ቅዱስ እንደሚነግሚን " ዚለምጜ ደዌ
ያለበት ሰው ልብሱ ዹተቀደደ ይሁን፥.....ርኩስ
ርኩስ ነኝ ይበል።"(ኊሪ ዘሌ.13፥45) እንደሚል
ዹተቀደደ ልብስ ያለበሰ ሰው ዹተዋሹደና
በኃጢአት እንደሚኚሰ እርኩስ ነኝ እያለን ነው
ማለት ነው ። ለዚህም ሌላ ማስሚጃ ዚቅዱስ
ዳዊት ልጅ ትእማር በወንድማ በተደፈሚቜ ጊዜ "
ትዕማርም በራስዋ ላይ አመድ ነስንሳ፥ ብዙ
ኅብርም ያለውን ልብስዋን ተርትራ፥ እጅዋንም
በራስዋ ላይ ጭና እዚጮኞቜ ሄደቜ። ነው
እሚለን (1ኛሳ.13፥19)
ኚእስራኀል ወገን በሆነው በአካን ምክንያት
እሥራኀል በደሚሰባ቞ው መኚራ ምክንያት "
ኢያሱም ልብሱን ቀደደ፥ ......"እንዲል መጜሐፍ
ቅዱስ። ( ኢያሱ 7፥6) እኛም ዚተቀዳደደ ልብስ
ስንለብስ እንደሚኚስንና በኃጢአታቜን መኚራ
እዚደሚሰብን እዚገለጜን ነው። እንዲያም ቢሆን
ደግሞ ማቅ ለብሰን አመድ ነስንሰን በንስሃና
በጞሎት ልንበሚታ እንጂ ደሚታቜንን ነፍተን
ባልዘነጥንበት ነበር።
ሌላው መጜሐፍ ቅዱስ በሐዘን ምክንያት
ልብሳ቞ውን ዚቀደዱና ያዘኑ እንዳሉ" ያዕቆብም
ልብሱን ቀደደ፥ በወገቡም ማቅ ታጥቆ ለልጁ
ብዙ ቀን አለቀሰ።" ሲል አባታቜን ያዕቆብ
በዮሎፍ ምክንያት ያለቀሰውን ለቅሶ ጜፎልናል
(ኊሪ.ዘፍ 37÷34) እንዲህ አይነቱን ሐዘን
እዮብም አድርጎታል። " ኢዮብም ተነሣ
መጐናጞፊያውንም ቀደደ፥ ....."(ኢዮ.1÷20)
ሰለዚህ ክርስቲያን ዹተቀደደን ልብስ ሊለብስ
አይገባም በተለይ በቀተክርስቲያን ቅጥር ግቢ
ውስጥ ስንገባ እንዲህ አይነት አለባበሶቜን
መልበስ ነውር ነው። ገላን እያሳዩ ወደ
ቀተክርስቲያን መግባት ለቀተክርስቲያን ያለንን
ንቀት ኚማሳዚት ያለፈ ሌላ ትርጉም ዚለውም።
ምክንያቱም ቀተክርስቲያን ዚራሷ ዹሆነ ዚአለባበስ
ሥርዓት አላትና።
❗ታህሣሥ 3 በዓታ ለማርያም ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔎👉 ታህሣሥ 3 በዚህቜ ቀን አምላክን ዚወለደቜ እመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም ሊስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቀተ መቅደስ ዚገባቜበት ዕለት ነው ምክንያቱም እርሷ ለእግዚአብሔር ዚስዕለት ልጅ ነበሚቜና።

🔷👉 ታዲያ ቀተ መቅደስ ዚገባቜበት ዕለት ነው ብለን ብቻ ማለፍ ሳይሆን እንዎት እንደገባቜ ማወቅ ያስፈልጋልና አጠር አድርገን እንመለኚታለን።

🔎👉 ዚእናታቜን ዚቅድስት ድንግል ማርያም ወላጅ እናት ቅድስት ሐና ትባላለቜ። እናታቜን ቅድስት ሐናም አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ኚቀተ መንግሥት ወገን ኚነቅዱስ ዳዊት ወገን ኹሆነው ኚቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት።

🔎👉 እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡፀ ኚእለታት አንድ ቀን ወደ ቀተ እግዚአብሔር ሂደው ሲጞልዩ ሲያዝኑ ዋሉ። ሀዘናቾው እንዎትስ ነው ቢሉ፡- ኢያቄም፡- "አቀቱ ጌታዬ ያባቶቌ ዚእስራኀል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ጾሎቮን ስማኝ ፈቃዮን ፈጜምልኝፀ ለዐይኔ ማሚፊያ ለልቀ ተስፋ ዹሚሆን ዚተባሚኚ/ቜ ወንድ ወይም ሎት ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ። ሐናም በበኩሏ "አቀቱ ጌታዬ ዚአባቶቌ ዚእስራኀል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁፀ ስማኝ ለዐይኔ ማሚፊያ ለልቀ ተስፋ ዚምትሆነኝ ዚተባሚኚቜ ሎት ልጅ ዹማኅጾኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለቜ።

🔷👉 እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጞልዩ ውለው ርግብ ኚልጆቿ ጋር ስትጫወት ዐይታ አቀቱ ጌታዬ ለዚቜ ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ ዹሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኞኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰቜ። ኹሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ሄደው አቀቱ ጌታቜን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ፣ ቀተ እግዚአብሄርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለንፀ ሎት ልጅም ብንወልድ ማይ (ውሃ) ቀድታ፣ መሶብ ወርቅ ሰፍታ፣ መጋሹጃ ፈትላ፣ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ። ዘካርያስም እግዚአብሔር ጞሎታቜሁን ይስማቜሁ ስእለታቜሁን ይቀበልላቜሁ ጻህቀ ልቊናቜሁን ይፈጜምላቜሁ ብሎ አሳሚገላ቞ው።

🔷👉 ኚዚያም በኋላ ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱኑ ራዕይ ዐይተው ነገር አግኝተው አደሩ። ራዕዩም ኢያቄም “ርኢኩ በህልምዹ እንዘ ይትሚኀው ሰባቱ ሰማያት - ፯ቱ ሰማያት እንደ መጋሹጃ ተገልጠው ኹላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሎ ላይ ሲቀመጥ አዹሁ” አላት ፀ ወፍ ዚተባለው ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ነው። ነጭነቱ ንጜሐ ባሕሪው ነውፀ ኹላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሎ ላይ ሲቀመጥ ዐዹሁ ማለቱፀ አምላክ ዚኢያቄምን ( ዹሰውን) ባሕርይ ባሕርይ እንዳደሚገው ሲያጠይቅ ነውፀ ፯ቱ ሰማያት ዚተባሉ ዚጌታቜን ልዩ ልዩ ባሕርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩ መንግሥቱ ና቞ው።

🔎👉 ሐናም እኔም አዹሁ አለቜውፀ ምን አዚሜ ቢላትፀ “ዖፍ ጞዓዳ መጜአት ኀቀዚ ወነበሚት ዲበ ርዕስዚ ወቊአት ውስተ ዕዝንዹ ወኀደሚት ውስተ ኚርስዚ - ነጭ ርግብ መጥታ በራሎ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጾኔ ስትተኛ አዹሁ” አለቜው። ርግብ ዚተባለቜ እመቀታቜን ድንግል ማርያም ናት። ነጭ መሆንዋ ንጜህናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ድንግልናዋ ነው። ነጭ ርግብ መጥታ በራሎ ላይ ተቀምጣ ኚራሎ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕጾኔ ስትተኛ አዹሁ ማለቷ ብሥራተ ገብርኀልን በጆሮዋ ሰምታ እመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታቜንን መጜነሷን ነው። ይህንኑም ራዕይ ያዩት ሐምሌ ፎ (ሠላሳ) ዕለት ነው።

🔷👉 እነሱም እንዲህ ያለ ራዕይ ካዚን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቀ ሥጋ አልተገናኙምፀ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት ብሎ ያበሰሚ አምላክ ለኛስ ይልክልን ዹለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስኚ ፯ ቀን ድሚስ ለዚብቻ቞ው ሰነበቱ። በነሐሮ በሰባተኛው ቀን ኹሰው ዚበለጠቜ ኚመላእክት ዚኚበሚቜ ደግ ፍጥሚት ትወልዳላቜሁና ዛሬ በሩካቀ ሥጋ ተገናኙ ብሏቜኋል ጌታ ብሎ መልአኩ ለሐና ነገራት። በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቀታቜን እግዝእትነ ማርያም ነሐሮ ፯(7) ቀን ተፀነሰቜ።

🔎👉 እመቀታቜን ኚተፀነሰቜ በኋላ አይሁድ ቀንተው ተነሱባ቞ው። ኚቅናትም ዚተነሳ ሊገድሏ቞ው ይፈልጉ ነበርና በመልአኩ ትዕዛዝ ሞሜተው በሊባኖስ ተራራ ላይ እመቀታቜን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰቜ በ፱(9) ወር ኚአምስት ቀን ዚግንቊት መባቻ ዕለት ግንቊት ፩(1) ተወለደቜ።

🔎👉 ዚእመቀታቜን እድሜ ሊስት ዓመት ሲሞላው ጠቢቡ ሰሎሞን “ሰነፎቜ ደስ አያሰኙትምና ለእግዚአብሔር ስእለት በተሳልኜ ጊዜትፈጜመው ዘንድ አትዘግይ ዚተሳልኞውን ፈጜመው ተስለህ ዚማትፈጜም ብትኟን ባትሳል ይሻላል” መክ 5፡4-5 ብሎ ዹተናገሹውን በማሰብ ባሏ ኢያቄምን ይኜቺ ብላ቎ና ዚብጜአት ገንዘብ እንደኟነቜ ታውቃለኜ ወስደን ለቀተ እግዚአብሔር እንስጣት አለቜው፡፡

🔷👉 እርሱም ፍቅርሜ ይለቅልሜ ብዬ ነው እንጂ እኔማፈቃዎ ነው አለፀ ኢያቄም ይኜነን ማለቱ ሐና እመቀታቜንን በመካንነት ኑራ ያገኘቻት አንድያ ልጇ ናትና ኚፍቅሯ ጜናት ዚተነሣ ተለይታት አታውቅም ነበርና ነው፡፡ ኹዚህም በኋላ ቅድስት ሐና ኚቅዱስ ኢያቄም ጋር በመሆን ካህኑ ዘካርያስ ወደሚገኝበት ቀተመቅደስ ልጃቾውን ወሰዷት፡፡ ኢያቄምና ሐና እግዚአብሔርን በማመስገን ካህኑ ዘካርያስን ‹‹ይህቺ ብላ቎ና ስዕለት ተስለን አምላካቜን በ቞ርነቱ ዹሰጠን ናትና ተቀበለን›› አሉት፡፡ እርሱም ቢያያት እንደ ፀሓይ ዚምታበራ እንደመብሚቅ ግርማዋ ዚሚያስፈራ ዚምታበራ ዕንቈ ባሕርይ መስላታዚቜው፡፡

🔎👉 ወደ ቀተመቅደስ በወሰዷት ወቅትም እርሱም በአድናቆት ይህቺን ዚመሰለቜ ፍጥሚት ምን እናደርጋታለን፣ ምን እናበላታለን፣ ምንስ እናጠጣታለን፣ ምን እናነጥፍላታለን፣ ምን እንጋርድላታለን ብሎ ሕዝቡን ሰብስቊ ሲጚነቁ ሳለ ለእስራኀል ደመና ጋርዶ መናን አውርዶ ዚመገበፀ ለኀልያስም በመልአኩ እጅ በመሶበ ወርቅ ኅብሥት ዚመገበፀ ለዕዝራ ሱቱኀልም በመልአኩ በቅዱስ ዑራኀል እጅ መልኩ እሳት ዚሚመስል ጜዋዐ ልቡና ያጠጣው ልዑል እግዚአብሔር ለእናትነት ወደ መሚጣት ወደ እናቱ መልአኩ ቅዱስ ፋኑኀልን ላኚላት (ዘፀ 16፡ 31ፀ 1ኛነገ 19፡6ፀ ዕዝ. ሱቱ. 13፥38-41)::

🔷👉 በዚያን ጊዜ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኀል ኅብስት ሰማያዊ በብርሃን ጜዋዕ ስ቎ ሕይወት ይዞ ሹቩ ወሚደፀ ዘካርያስ ለእርሱ ዚመጣ ሀብት መስሎት ሊቀበል ቢነሣ ወደ ላይ ሰቀቀበትፀ ያን ጊዜ ጥበበ እግዚአብሔር አይመሹመርምና ለዚህቜ ብላ቎ና ዚመጣ ሀብት ይኟናል እስኪ እልፍ አድርጋቜኊ አኑሯት አለፀ እልፍ አድርገው ቢያኖሯት እመቀታቜን እናቷን ስትኚተል መልአኩ አንድ ክንፉን አንጜፎ አንዱን ክንፉን አጐናጜፎ ኚመሬት ዹሰው ቁመት ያህል ኹፍ ብሎ ኅብስቱን መግቧት ጜዋውን አጠጥቷት ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡

❗ዚእናታቜን ዚቅድስት በዓታ ለማርያም ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን❗

❗ለሁሉም እንዲደርስ ላይክ ሌር አድርጉ❗

    ።።።።
#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
     ።።።።።
#ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
     ።።።።።
#ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
[ታኅሣሥ 22 ዹአምላክ እናት ተአምሯን ለጻፈላት ለቅዱስ ደቅስዮስ በሚኚቷን ዚሰጠቜበት]
✍ ኚመጋቀ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ደቅስዮስ ዹተወለደው በ607 ዓ.ም. ሲኟን ኹጊዜ በኋላ ዚቶሌዶ ጳጳስ ዹሆነው አጎቱ ዩጄኒዚስ በወጣትነቱ ቃለ እግዚአብሔርን ያስተምሚው ነበሚ። ኚዚያም በ632 ዓ.ም አካባቢ ዚቶሌዶ ኀጲስ ቆጶስ ኀላዲዎስ ዲያቆን አድርጎ ሟሞታል። ኹፍ ካለ በኋላ በቶሌዶ አቅራቢያ ወደሚገኘው ዚአጋሊያ ገዳም በመግባት ዚገዳሙ አበምኔት ኟነ። ኚዚያም በ657 ዚቶሌዶ ሊቀ ጳጳስ ኟኖ ተመሚጠ።

💥 ደቅስዮስ እመቀታቜንን በፍጹም ልቡ ኚመውደዱ ዚተነሣ በተቻለዉም ኹሉ ያገለግላት ነበር “ወእምንደተ ፍቅሩ አስተጋብአ መጜሐፈ ተአምሪሃ” ይላል ኚፍቅሩም ጜናት ዚተነሣ ክብሯን፣ ንጜሕናዋን፣ ቅድስናዋን፣ ዘላለማዊ ድንግልናዋን፣ ወላዲተ አምላክነቷን፣ ተአምሯን ዹሚናገር መጜሐፍን ሰበሰበ።

💥 ደቅስዮስ መሰብሰብ ብቻ ሳይኟን ድርሰትም ደራሲ ነበሚ። ኚጻፋ቞ው ኚደብዳቀዎቹ ሁለቱ እና አራቱ ጜሑፎቹ አሁንም ድሚስ አሉ። በተለይ ዚመዠመሪያው እና ዋናው ክፍል ስድስት ድርሰቶቜን ያቀፈና ልክ እንደ ጀሮም ርሱም ሄልቪደስን ተቃውሞ ስለ እመቀታቜን ዘላለማዊ ድንግልና ዚጻፈው "De virginitate perpetuâ sanctae Mariae adversus tres infideles" (On the Perpetual Virginity of Holy Mary) በመባል ዚሚታወቅ ሥራው ነው። ይኜ ዚደቅስዮስ መጜሐፍ ለ3 ዹተኹፈለ ሲኟን "ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅሚ ወሊድ" ዘላለማዊት ድንግል መኟኗን ይተነትናል።

💥 ቅዱስ ደቅስዮስ ዚእመቀታቜን ዘላለማዊ ድንግልናዋ ዹልጇ ዚክርስቶስን ዚባሕርይ አምላክነት ዚሚገልጜ ምልክት እንደኟነ ሲገልጜ ልጇ እግዚአብሔር ነውና ብቻውን በድንግልና ተፀንሶ በድንግልና ሊወለድ ቜሏል ብሏል።

💥 ደቅስዮስ እመቀታቜንን በጜሑፉ ማርያም ብቻ ብሎ በስሟ አይጠራትም። ይልቁኑ ድንግሊቱ፣ ዚእኛ ድንግል ይላታል።

💥 ያን ጊዜ እመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻለት “ይኜን መጜሐፍ ስለ ጻፍኜልኝ ደስ ብሎኛል” ብላው ባርካው ተሰወሚቜ፡፡

💥 በተጚማሪም በ304 ዓ.ም. በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነትን በተቀበለቜው በቅድስት ሊዮካዲያ (Saint Leocadia) ዹኹበሹ ዐፅም ፊት ሲጞልይ በተአምራት ተነሥታ ዹአምላክን እናት ስላኚበራት አመስግናዋለቜ።

💥 ቅዱስ ደቅስዮስም ይኜነን ኹሉ ካዚ በኋላ እጅጉን በመደሰት ለእመቀታቜን ክብር ምን መሥራት እንዳለበት በማሰብ ቅዱስ ገብርኀል እመቀታቜንን ያበሠሚበት መጋቢት 29 ቀን ዚዐቢይ ጟም በመኟኑ ምክንያት ሰዎቜ ማክበር ያልተቻላ቞ውን በዓለ ብሥራትን ኚልደት በዓል ስምንት ቀናት ቀደም በማድሚግ ታኅሣሥ 22 ዕለት እንዲኚበር ሥርዐትን ሠራ። በቶሌዶ በተደሹገ ጉባኀ ለአምላክ እናት ክብር ዹተለዹ ዚበዓላቷን ቀን ተደነገገ።

💥 ምእመናንም እጅጉን በመደሰት በቅዱስ ገብርኀል ብሥራት ወልደ እግዚአብሔር በማሕፀነ ማርያም ዚተፀነሰበትን በዓል ለውጥ በማሰብ በዓሉን በድምቀት አኚበሩ፡፡ ያን ጊዜ በወርኃ ታኅሣሥ በ665 ዓ.ም. በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ዚጞናቜ እመቀታቜን ለደቅስዮስ ለብቻው ተገልጻለት “ወዳጄ ደቅስዮስ ባንተ ደስ አለኝፀ ሥራኜንም ወደድኊፀ በዓሌን አክብሚኜ ስለ እኔ ሰውን ኹሉ ደስ አሰኝተኻልና እኔም ዋጋኜን ልሰጥኜ እወዳለኊ ትቀመጥበትም ዘንድ ይኜነን ወንበር አመጣኹልኜ” በማለት በወንበሩም ላይ ማንም ሊቀመጥባት ዚሚቻለው እንደሌለ ነግራው ኚርሱ ተሰወሚቜ፡፡

💥 በሌላ ጊዜ ኀጲስ ቆጶሱ ደቅስዮስ ኚምእመናን ጋር ዚእመቀታቜንን መዝሙር ሲዘምሩ ኹፍተኛ ብርሃን ወርዶ ቀተ ክርስቲያኒቱን ሲኚብባት አብዛኞቹ ምእመናን ፈርተው ሲሞሹ ደቅስዮስ ኚጥቂት ዲያቆናት ጋር ብቻ ቀሚ። ያንጊዜ ቅድስት ድንግል ማርያም ደናግልን አስኚትላ ወርዳ በኀጲስ ቆጶስ ዙፋን ላይ ተቀምጣ አዚ። እመቀታቜንም ደቅስዮስን ለታማኝነቱ አመስግናው እጅግ ዹተለዹ ልብሰ ተክህኖ በበዓላቷ ላይ ብቻ እንዲለብስ ሰጥታው በእመቀታቜን በዓላት ይለብሰው ነበር።

💥 ቅዱስ ደቅስዮስም በ667 ዓ.ም. ኚዚኜ ዓለም በሕይወተ ሥጋ በተለዹ ጊዜ እመቀታቜን ዚባሚኚቜውን ልብስ በቀተ ክርስቲያን ዕቃ ቀት በክብር አኖሯትፀ ኚርሱ በኋላ ዚተሟመው ኀጲስ ቆጶስ ግን ያቜን ልብስ ሊለብሳትና በደቅስዮስም ወንበር ሊቀመጥ ወደደ።

💥 ቀሳውስትና መምህራን ግን ዚልብሷን ክብር በመንገር ይኜነን እንዳያደርግ ቢለምኑት ርሱ ግን ልክ እንደ ዖዝያን በድፍሚት ልብሷን ለብሶ በወንበሩ በተቀመጠ ጊዜ ሐናንያና ሰጲራ በቅዱስ ጎጥሮስ ፊት ተቀሥፈው እንደሞቱፀ ርሱም “ወድቀ በጊዜሁ እምላዕለ ውእቱ መንበር በቅድመ ኲሎሙ ሰብእ እለ ሀለዉ ውስተ ቀተ ክርስቲያን ወሞተ በእኩይ ሞት ወሕሡም ፈድፋደ” ይላል በዚኜ ዚድፍሚት ኀጢአቱ ኚዚያ ወንበር ላይ በቀተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰዎቜ ኹሉ ፊት ወድቆ ክፉ አሟሟትን ሞቷልፀ በቀተ ክርስቲያን ውስጥ በተደሹገው ተአምር ሕዝቡ በመደነቅ ምስጉን እግዚአብሔርን በማመስገን አምላክን ዚወለደቜ ክብርት እመቀታቜንን ስለ አደሚገቜው ተአምር እጅጉን አክብሚዋታል፡፡ በግእዝ በብራና በተጻፉት ተአምሹ ማርያም ላይ ይኜ ዚቅዱስ ደቅስዮስ ታሪክ ተሥሎ ማዚት ዹተለመደ ነው።

💥 ኚዚያ በኋላ ዚሰጠቜው ልብስ ቢሰወርም ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ለደቅስዮስ ስትገለጥለት እግሯን ያሳሚፈቜበት ድንጋይ ግን በቶሌዶ ካ቎ድራል ጞሎት ቀት ውስጥ ይኚበራል።

💥 ንጉሥ ዳዊትም እንደነ ደቅስዮስ ላሉ እመቀታቜንን ለሚወዷት ኹሉ በምልጃዋ ኹልጇ ስለምታሰጣ቞ው ታላቅ መንፈሳዊ በሚኚት መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ ገልጊለት “ህዹንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ” (በአባቶቜሜ ፈንታ ልጆቜ ተወለዱልሜ) በማለት ኹገለጠ በኋላ “ወትሠይሚዮሙ መላእክተ ለኲሉ ምድር” (በምድርም ኹሉ ላይ ገዢዎቜ አድርገሜ ትሟሚያ቞ዋለሜ) በማለት ዚሠያሜ ነገሥት፣ ዚሠያሜ ካህናት ዚክርስቶስ እናት መኟኗንናፀ ይኜነንም ዹአምላክ እናትነቷን ለመሰኚሩ ለነ ደቅስዮስ ወንበርፀ ለነ ኒቆላዎስ ዐጜፍ፣ ለነ ቅዱስ ኀፍሬም “አኀዝ እግዚኊ መዋግደ ጾጋኹ” (አቀቱ ዚጞጋኜን ማዕበል ግታውፀ ወስነው) እስኪሉ ድሚስ በቃል ኪዳኗና በአማላጅነቷ ያሰጠቻ቞ው ታላቅ በሚኚት መንፈሳዊ ሹመትና ብቃት መኟኑን አሳይቷል፡፡

💥 “ወይዘክሩ ስመኪ በኲሉ ትውልደ ትውልድ” (ለልጅ ልጅ ኹሉ ስምሜን ያሳስባሉ) በማለት በክርስቶስ ዚባሕርይ አምላክነት በርሷ ወላዲተ አምላክነት በማመን ዹጾና ያለፈውና ዚሚመጣው ትውልድ ኹሉ “ሰአሊ ለነ ቅድስት” (ቅድስት ሆይ ለምኝልን) እያለ ዹተቀደሰ ስሟን ሳይጠራ ዹሚውል ማንም እንደማይኖር ቅዱስ ዳዊት በመንፈሰ እግዚአብሔር ገላጭነት ተናግሯል (መዝ ፵፬፥፱-፲፯)፡፡

💥 ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በሕማማት ሰላምታው ላይ፩
“ማርያም ሀብኒ ልብሰ ትፍሥሕት ወተድላ
ኹመ ወሀብኪዮሙ ቅድመ ምስለ መሐላ
ለደቅስዮስ ወለኒቆላ ሰላም ለኪ"
(ለኒቆላና ለደቅስዮስ ኹቃል ኪዳን ጋራ አስቀድመሜ እንደሰጠሻ቞ው ሰላምታ ዚተገባሜ ማርያም ዚፍጹም ደስታና ተድላ ልብስን ስጪኝ) በማለት ተማፅኗታል፡፡

💥 ዹነገሹ ማርያም ሊቃውንት ዚነበሩት አባ ጜጌ ድንግልና አባ ገብሚ ማርያም ዘደብሚ ሐንታም በማሕሌተ ጜጌ መጜሐፋ቞ው ላይ እመቀታቜን ተአምሯን ሰብስቊ ላዘጋጀላት ለደቅስዮስ ታላቅ ጾጋን በቃል ኪዳኗ እንዳሰጠቜ ሲገልጹፊ
“ሶበ ጾሐፈ ደቅስዮስ ተአምሚኪ ቅዱሰ
መንበሹ ወዐጜፈ ዕሀተ ጻማሁ ወሹሰ
ማርያም ድንግል ዘታብእሊ ፅኑሰ
ዐስበ ማሕሌትዚ ዐቅመ ልብዚ ኀሠሠ
ጾግውኒ አትሮንሰ ወጜጉዚ ልብሰ”

(ደቅስዮስ ልዩ ዚኟነ ተአምርሜን በጻፈ ጊዜ ዚድካሙን ዋጋ ልብስንና ወንበርን አገኘፀ ድኻውን ባለጠጋ ዚምታደርጊ (ነዳዚ አእምሮውን በቃል ኪዳንሜ ባለ አእምሮ ዚምታደርጊ) ድንግል ማርያም ልቡናዬ በፈለገ መጠን ዚምስጋናዬን ደሞዝ ወንበርንና ዚክብር ልብስን ስጪኝ) በማለት ዚሿሚ ዚክርስቶስ እናት ዚቅድስት ድንግልን በሚኚት ልክ እንደ አባ ጊዮርጊስ ሜተዋል፡፡
❀በቀተ ክርስቲያን 5 አይነት አክሊላት አሉ❀

1 አክሊለ ሰማዕት
ይህ አክሊል ሰማእታት በተጋድሎ ዚሚያገኙት አክሊል ነው  ቅዱስ
ጳውሎስም ስለዚህ አክሊል ሲናገር ሃይማኖቮን ጠብቄለው ሩጫዬን ጚርሻለው ወደፊት ዚጜድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ብሎ ጠቅሶታል
2 ጢሞ 4+6-7
በተመሳሳይ ባለራዕዩ ቅዱስ ዮሐንስም እስኚሞት ድሚስ ዚታመንክ ሁን ዚሕይወት አክሊል እሰጥሃለው ብሎ ዹተናገሹው ስለ ሰማእታት አክሊል ነው ራዕ 2+10 ክርስቶስም አክላሎሙ ለሰማእት ተብሏል እመቀታቜንም አክሊለ ሰማእት ትባላለቜ

2 አክሊለ ሶክ (አስኬማ መላእክት)
ይሄ አክሊል ዚአባ እንጊንዮስ አክሊል ሲሆን መነኮሳት ዚሚያደርኩት አክሊል ነው ይሄ አክሊል በምንኩስና ዓለምን ኹናቁ በኋላ ዹሚገኝ ነው ክርስቶስ በዕለተ አርብ ዹተቀበለው አክሊለ ሶክ ዚሚታሰብበት ሲሆኔ ይሄን አክሊል ያደሚጉ መነኮሳት እንደ መላእክት በንጜሕና በቅድስና ስለሚኖሩ አስኬማ መላእክት ተብሏል

3 ተክሊል (ዹተክሊል አክሊል)
ይህ አክሊል በድንግልና ኑሹው ለሚጋቡ ኊርቶዶክሳውያን ዹሚደሹግ ዚድንግልና ምልክት ዹሆነ አክሊለ ኚብካብ ነው ደናግል ላልሆኑ ፈጜሞ ዹማይደሹግ ነው 

4 አክሊለ ነገሥት ይህ አክሊል ለነገሥታት ብቻ ዹሚደሹግ ነው ሰሎሞን ሲነግሥ ሲቀባ ዚተደሚገለት አክሊል ነው አባ ሕርያቆስ በቅዳሎው  ወአክሊሉ ለሰሎሞን ዹሰሎሞን አክሊል ነሜ ብሎ ዹተናገሹው  ዚነገሥታት አክሊል እመቀታቜን እንደሆነቜና ነገሥታት ሲነግሢ ተቀብተው አክሊል እንደሚያደርጉ ለመግለጜ ነው

5 አክሊለ ካህናት
ይህ አክሊል በክህነት ዚሚያገለግሉ ካህናትና ዲያቆናት ዚሚያደርርጉት አክሊል ነው
ክህነት ለሌለው ፈጜሞ ዹማይደሹግ ሲሆን ዚካህናት አክሊል አሰራሩ ኹላይ 4 ማዕዘን ሲሆን ዚዲያቆናት አክሊለም በአሰራር ኚካህናት ዹተለዹ ክብ ነው ዲያቆን ዚቄሱን አክሊል ፈጜሞ ማድሚግ አይቜልም  አምስቱ አክሊላት እነዚህ ናቾው
አሁን አሁን ግን ዚካህኑን እና ዚዲያቆኑን አክሊል ሎቶቜ ሳይቀር አድርገውት እዚታዚ ስለሆነ እጅግ ዚሚያሳዝን ነው 
ሥርዓተ ቀተ ክርስቲያን እዚተጣሰ  ቾል ተብሎ እዚታዚ ነው ስለዚህ  ዚሊቃውንት ጉባኀ ይሄን ጉዳይ እልባት ሊሰጥበት ይገባል ።
#ድንግል_ሎት_ትፈልጋለህ?
ምንም እንኳን ሰዎቜ ሁሉም ባይሆኑም ብዙ ሰዎቜ ግን ዚሚያገቧት ሎት ድንግል እንድትሆን ይፈልጋሉ አንዳንዶቜ ደግሞ መፈለግ ብቻ ሳይሆን ዚመጀመሪያ መስፈርታ቞ው ያደርጉታል ይህ እጅግ ደስ ዚሚያሰኝ አቋም ነው ምክንያቱም ዚኹሉም ሰው አቋም እንዲህ ቢሆን ኖሮ ሎቶቜ ኹሉ በንጜሕና መኖርን ለወደፊት ትዳራ቞ው መቃናት ሲሉ ስለሚለማመዱት ነው።

ታዲያ ሚስቱ ድንግላዊት ሆና ቢያገኛት ዹሚመኝ ሰው እርሱም ድንግልናውን ዹጠበቀ ሆኖ መገኘት እንዳለበት ለአፍታም እንኳን ቢሆን መዘንጋት ዚለበትም ስለዚህ ይህን ዹሚመኝ ራሱን ይጠብቅ ካላገባኻት ሎት ጋር አንሶላ መጋፈፍን አትሻ ልታገባ አንድ ቀን ዹቀሹህ ቢሆን እንኳን ሳታገባት ይኜን መሞኹር ዚለብኜም በሰዓታትና በቅጜበት ውስጥ በእቅፍኜ ያለቜ እጮኛህ ያንተ ሚስት መሆን ዚማትቜልበት ሁኔታ ይፈጠር እንደሆነ አታውቅምና አንተ ራስህ ኚነድንግልናህ ዚምትፈለግበት ጋብቻ ኹፊተህ ይጠብቅሀል ።

#እርሷም_በምትሄድበት_ቊታ_ባሏ ኹነ ሙሉ ክብሯ ይሻታል ታዲያ ካላገባሃት ሎት ጋር ለምን ትተኛለህ? ካላገቧት ሎት ጋር ምንጣፍ መጋራት በሰው ቀት መግባትና ኚባለ ትዳር ሎት ጋር እንደ ማመንዘር ነው ያላገባቜ መሆኗ ልዩነቱ ባሏን መቅደምህ ብቻ ነው አንተ በሰው ትዳር እንዲህ ዚምተገባ ኹሆነ ሌሎቜ ደግሞ አንተ ዚምታገባትን ሎት ኚክብር አስንሰው ንጜሕነዋን ገፈው ያቆዪሀል አንተ ድንግል ሳትሆንና ዚብዙዎቜን ሕግ አፍርሰህ ድንግል ሎት መፈለግህ አያስገርምም ?

ሰው ዚራሱን ድንግልና ቢጠብቅ እግዚአብሔር ደግሞ በድንግልና ዚተጠበቀቜ ሚስት እንደ ፍላጎቱ ሊሰጠው ተስፋ ሰጥቷል ሰው ዚራሱን ዕቃ ቢጠብቅ ለእርሱ ዚሚገባውን ዕቃ እግዚአብሔር በክብር ይጠብቅለታል። በመጜሐፍ ቅዱስ ዕቃ ዚሚባለው አባለ ዘርዕ (ኀፍሹተ አካል )ነው።ቅዱስ ዳዊት በእውነት ኚመጣን ጀምሹን እኛ ሰውነታቜንን ኚሎቶቜ ሶስት ቀን ጠብቀናል ዚብላ቎ኖቜም ዕቃ ዚተቀደሰቜ ናት ስለዚህ ዛሬ ዕቃቾው ዚተቀደሰቜ በመሆኗ እንጀራው እንደሚበላ እንጀራ ይሆናል 1ኛሳሙ 21:5 በማለት ዹተናገሹው ቃል ኀፍሹተ አካል ዕቃ እንደሚባል ያስሚዳል።

#ዚራሱን ንጜሕና ዹጠበቀ ሰው ለእርሱ ዚምትሆነው ሚስቱ ኚነቅድስነዋ ኚነንጜሕነዋና ኹነሙሉ ክብሯ(ድንግልነዋ)እንደሚያገኛት ማወቅ አለበት ሲል ሐዋሪያው"ኚእናንተ እያንዳንዱ ዚራሱን እቃ(ሚስቱ ዚምትሆነውን ) በቅድስናና በክብር (ኚነድንግልነዋ) ያገኝ ዘንድ እንዲያውቅ"በማለት ይናገራል።
#ዕቃ ዹሚለው ኀፍሹተ አካል መሆኑ ኹላይ በማያሻማ መልኩ ተገልጿል።ስለዚህ ድንግልን ማግባት ዹሚፈልግ ሰው ዚራሱን ክብር መጠበቅ ይኖርበታል።
#1ኛ_ተሰሎንቄ 4÷5🙏
https://www.tgoop.com/tmhrteorthodox
​​ጟመ ሰብአ ነነዌ

ጟመ ነነዌ ኚሰባቱ ዹአዋጅ አጜዋማት አንዷ ስትኟን ዚምትጟመውም ለሊስት ቀናት ነው፡፡ ይህቺ ጟም ዚምትጀመርበት ዕለትም ልክ እንደ ዐቢይ ጟም ሰኞን አይለቅም፡፡ ጟሟ ዚምትጀመርበት ቀን ሲወርድ ወይም ወደ ኋላ ሲመጣ እስኚ ጥር ፲፯ ቀን ድሚስ ነው፡፡

ቀኑ ሲወጣ ወይም ወደ ፊት ሲገፋ ደግሞ እስኚ ዚካቲት ፳፩ ቀን ይሚዝማል፡፡ ጟመ ነነዌ በእነዚህ ፎ፭ ቀናት ውስጥ ስትመላለስ (ኹፍ እና ዝቅ ስትል) ትኖራለቜፀ ኚተጠቀሱት ዕለታት አትወርድምፀ አትወጣም፡፡ በዚህ ዓመትም ዚካቲት ፫ ቀን ትጀመራለቜ፡፡

‹‹ጟመ ሰብአ ነነዌፀ ዹነነዌ ሰዎቜ ጟም›› á‹šáˆšáˆˆá‹ ዚጜሑፋቜን ርእስ እንደሚያስሚዳው ይህቺን ዚሊስት ቀን ጟም ዚጟሟት በነነዌ ይኖሩ ዚነበሩ ሰዎቜ ና቞ው፡፡ ኹተማዋም (ነነዌ) በጀግሮስ ወንዝ ዳርቻ ዚምትገኝ ስትኟን መሥራቿም ናምሩድ ነው  ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪/ ፡፡ ጥንታዊቷ ዹነነዌ ኹተማ ለአሩር መነሻ ዚኟነቜፀ እጅግ ሰፊና ያማሚቜፀ ዚቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር ዹሚሾፈን ነበር። በኹተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎቜን ገንብቶባት ነበር /ዮናስ ፬፥፲፩/፡፡

በዚያ ዘመን ዚነበሩ ዹነነዌ ሰዎቜ ኀጢአታ቞ው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋ቞ው ሲል ቞ርነትና ምሕሚቱ ዚማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳ቞ውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላኹው /ሉቃ.፲፩፥ፎ/፡፡

ዮናስ ዚስሙ ትርጕም ‹ርግብ› ማለት ነው፡፡ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት ዹነበሹ ነቢይ ነው፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ኹተማ ነበሚ፡፡ አባቱም አማቮ ይባላል፡፡ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ ዚእስራኀልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናግሯል /፪ኛነገ.፲፬፥፳፭ፀ ዮናስ ፩፥፩/፡፡

ነቢዩ ኀልያስ ያስነሣው ዚሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ኟነ ዚቀተ ክርስቲያን ታሪክ ያስሚዳል /፩ኛ ነገ.፲፯፥፲፱/፡፡ መድኀኔታቜን ክርስቶስም ዚዮናስን ኚዓሣ ኟድ መውጣት ዚራሱ ትንሣኀ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል /ማቮ.፲፪፥፲፱-፵፪ፀ ሉቃ.፲፩፥ፎ-ፎ፪/፡፡

እግዚአብሔር ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ መሐሪ ነህ ፀ áˆá‰µáŒ á‰ ነው á‰¥á‹¬ á‰°áŠ“áŒáˆ¬ ብትምራ቞ው ሐሰተኛ áŠá‰¢á‹­ እባላለሁ›› á‰¥áˆŽ ላለመታዘዝ እስራኀልን ለቆ በመርኚብ ወደ ተርሎስ ሞሞ፡፡

እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርኹቧ በማዕበል እንድትመታ አደሚገ፡፡ ኚዮናስ ጋር በመርኹቧ ተሳፍሚው ዚነበሩ ነጋድያንም ያላ቞ውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቩ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት ዚመጣ ስለ ኟነ ንብሚታቜሁን ሳይኟን áŠ¥áŠ”áŠ•  ወደ á‰£áˆ•ር áŒ£áˆ‰áŠâ€ºâ€º á‰¥áˆŽ ተማጞና቞ው፡፡

እነርሱም â€¹â€¹áˆµáˆˆá‹šáˆ… ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደሚግብን አይኟንም›› áŠ áˆ‰á¡á¡

ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ኚእግዚአብሔር ዘንድ ዚታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሊስት ቀንና ሊስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደሚሰው፡፡

እግዚአብሔር ዹቅል ተክልን ምሳሌ በማድሚግ ቅጠሉ በመድሚቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደኚምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ኹተማ ያሉ ኚአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ ዚእጄ ፍጥሚቶቜ ስለ ኟኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሞታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መኟኑን አስሚድቶታል፡፡

ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድሚሱን ባወቀ ጊዜ ኚእግዚአብሔር መሞሜ አለመቻሉን ተሚዳፀ ዹነነዌ ሰዎቜንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› áŠ¥á‹«áˆˆ መስበክ ጀመሚ፡፡ ዹነነዌ ሰዎቜም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ኚጥፋት አድኗ቞ዋል። ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ኟኖ ኹላይ ታይቶአል፡፡

ዚታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድሚስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷ቞ዋል፡፡ ንስሐ቞ው በኚንቱ እንዳልቀሚ አስሚድቷ቞ዋል /ትንቢተ ዮናስን በሙሉ ይመልኚቱ/። ታኅሣሥ ፭ ቀን ዹሚነበበው ዚመጜሐፈ ስንክሳር ክፍል ‹‹ወበልዐ አሐደ áŠ€áˆáˆˆâ€ºâ€º á‰ áˆ›áˆˆá‰µ ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎቜ በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግሚናል፡፡

ጟመ ነነዌ ዚሊስት ቀን ሱባኀ ናትፀ በሊስት ቀናት ጟምና ጞሎት ንስሐ ዚገቡ ዹነነዌ ሰዎቜ ኚጥፋት እንደ ዳኑ ዅሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስ቎ር ሊስት ቀን ጟማ፣ ጞልያ በእስራኀል ላይ ዚመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለቜ /አስ.፬፥፲፭-፲፮/፡፡ እመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያምም ኹበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢዚሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ኚሊስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቀተ መቅደስ አግኝታዋለቜ /ሉቃ.፪፥፵፮/፡፡ ጌታቜን መድኀኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሜ መልስ ሊስት ቀን ዚሱባኀ ፍጻሜ መኟኑን ገልጿል /ሉቃ.፲፫፥ፎ፪/፡፡

ጟመ ነነዌ ዚእግዚአብሔርን ቞ርነትና መሐሪነት ዚምናስታውስበት ጟም ነው። ይኾውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጜሞ ኚማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብኚት ፈቃደኛ ባይኟን እንኳን እግዚአብሔር በተለዹ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡

በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ ዹሚልኹው ነቢይ አጥቶም አይደለምፀ እርሱንም ጭምር ሊያስተምሚው ስለ ፈለገ እንጂ። ዹነነዌ ሰዎቜ ዚተነሳ ሕያን ምሳሌ ና቞ው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ኚገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን ‹‹አንተ ላልደኚምክበት እና á‰ áŠ áŠ•á‹µ  á‰€áŠ• á‰ á‰…ሎ  áˆ‹á‹°áŒˆ á‰…ል  ስታዝን እነሆ በታላቂቱ  ነነዌ áŠšá‰°áˆ› ያሉ ኚአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ áˆ•ዝብና እንስሳቱ á‹šáŠ¥áŒ„ ፍጥሚቶቜ ስለ ኟኑ ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡

ቀደምት ዚቀተ ክርስቲያን አባቶቻቜን ይህን እና ሌሎቜ አጜዋማትን እንድንጟም ዹወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ ዹተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎቜ እኛም ጟመን፣ ጾልዹን ኚኀጢአታቜን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማቜን በኀጢአት ማዕበል እዚተናወጠቜ ባለቜበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎቜ ኚበደላቜን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቞ሩ ፈጣሪያቜን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕሚት ዚባሕርይ ገንዘቡ ስለ ኟነ â€¹â€¹á‹ˆá‹° እኔ  ተመለሱፀ እኔም á‹­á‰…ር  እላቜኋለሁፀ›› ይለናል፡፡

ስለኟነም በነቢዩ ዮናስ ላይ ዹተደሹጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ ዚሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመኟኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎቜ ዹወሹደውን ምሕሚት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ኟነ ለሃይማኖት አባቶቜ እና ለወላጆቻቜን መታዘዝ ይገባናል፡፡

ስንጟምም እግዚአብሔር አምላካቜን መዓቱን በምሕሚት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኀጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጟማቜን ራሳቜን ኚመዓትና ኚመቅሠፍት ኚመዳናቜን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት አገራቜን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ኚድርቅና ኹቾነፈር ይተርፋሉና፡፡

✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
ለተዋሕዶ ልጆቜ👇
                •➢ ሌር // SHARE
   
https://www.tgoop.com/tmhrteorthodox
♊⛪ዚኢኊተቀክ አስተምህሮ ና ስርአትን ዹጠበቁ ዚትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉

👏 ዚ቞ብ቞ቊ መዝሙራት
          📖▓⇚→vido    ⇚ግጥም
🎻 ዹበገና መዝሙራት  
         📖▓⇚→vido     ⇚ግጥም
👑 ዚቅዱሳን መዝሙራት
          📖▓⇚→vido    ⇚ግጥም
⛪ ዚንግስ መዝሙራት
          📖▓⇚→vido    ⇚ግጥም
🀲 ዚምስጋና  መዝሙራት
          📖▓⇚→vido    ⇚ግጥም
🙏 ዚንስሐ  መዝሙራት
         📖▓⇚→vido   ⇚ግጥም
💍 ዹሠርግ መዝሙራት
          📖▓⇚→avido   ⇚ግጥም
🌊 ወቅታዊ መዝሙራት
          📖▓⇚→vido    ⇚ግጥም
🇪🇹 ለአገር ዚተዘመሩ
          📖▓⇚→vido   ⇚ግጥም
          👇👇

https://www.tgoop.com/+lVXHSARuil5kZDU0

          👇🏜ኚእስልምና ወደ ክርስትና በእውነተኛ ታሪክ ላይ ዹተመሰሹተ በYOUTUBE👇🏜

         👇🏜🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏜
   https://www.tgoop.com/+lVXHSARuil5kZDU0
#ዐብይ_ጟም

#ዐብይ_ጟም ፊማለት ምን ማለት ነው በመጀመሪያ ‹‹ዐቢይ›› ዹሚለው ቃል ‹‹አበዚ›› ኹሚለው ዹግዕዝ ግስ ዹተገኘ ነው፡፡ ትርጓሜውም ‹‹ኚፍ አለ›› ማለት ነው፡፡

ዚዐብይ ጟም ዚተለያዚ ስያሜዎቜ ዐብይ ጟም ኹቀኑ ርዝማኔ በተጚማሪ ጟሙ ዚተለያዩ ስያሜዎቜ አሉት፡፡

#ጟመ_ሁዳዎ፡- ሁዳድ ማለት ሠፊ (ትልቅ) ዚእርሻ ቊታ ማለት ነው፡፡ ይህም ጟም ደግሞ በቀኑ ብዛት ትልቅ (ሠፊ) በመሆኑ ዚሁዳዎ ጟም ይባላል፡፡

#ዚካሳ_ጟም፡- እንዲህ ዚተባለበት ምክንያቱ ደግሞ አዳምና ሔዋን በዲያቢሎስ ግዞት እያሉ ክርስቶስ ደሙን በመክፈል (በመካስ) ነጻ ስላውጣ቞ው ዚካሳ ጟም ተብሎሏል

#ዚድል_ጟም ፡-ይህም ደግሞ ጌታቜን አምላካቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ በዚህ ጟም ሰይጣንን ድል ያደሚገበት በመሆኑ ዚድል ጟም ተብሏል፡፡

#ዚመሞጋገሪያ_ጟም ፊጌታቜን ኹሕገ ኊሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሊያሞጋግሚን ዚጟመው ጟም በመሆኑ ዚመሞጋገሪያ ጟም ተብሏል።

#ጟም_አስተምህሮ፡- ይህ ጟም ‹‹ጟም አስተምህሮ›› ዚተባለበት ምክንያት ደግሞ ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ እኛን ለማስተማር ዚጟመው በመሆኑ ነው፡፡ ኹዚህም በተጚማሪ ደግሞ ዚተለያዪ ስያሜዎቜ አሉት
‹‹ዚመሞጋገሪያ ጟም ››
‹‹ዚስራ መጀመሪያ ጟም ››

ይህ ፆም ታላቅ መባሉም ለ55 ቀናት ያህል መፆሙና ኚሌሎቹ አፅዋማት ጋር ሲነፃፀር በቁጥር
መብለጡ ብቻ ሳይሆን ጌታቜን አምላካቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ በገዳመ
ቆሮንቶስ መፆም ሳይገባው ለእኛ አርአያና ትልቅ ምሳሌ ለመሆን ዹፆመው ፆምም
በመሆኑ ነው።

ታላላቅ ዚሰይጣን ፈተናዎቜ እንዲሁም ደግሞ ሶስቱ ርዕሰ ኃጢአት ዚሚባሉት
#ትዕቢት፣
#ስስት
#ፍቅሹ_ነዋይ
በጌታቜን በኢዚሱስ ክርስቶስ ድል ዚተመቱበት ስለሆነ ይህ ጟም አብይ (ታላቅ) ተብሏል፡፡

ዚአብይ ጟም ሳምንታት 8 ና቞ውፀ
1. 
#ዘወሹደ
2. 
#ቅድስት
3. 
#ምኩራብ
4. 
#መጻጉዕ
5. 
#ደብሚዘይት
6. 
#ገብርሔር
7. 
#ኒቆዲሞስ
8. 
#ሆሣዕና

አቢይ ጟም ሊስቱ ክፍሎቜ
1.     ዘወሹደ (ጟመ ሕርቃል)ፀ ይህም ጟሙ ኚሚገባበት ሰኞ ጀምሮ እስኚ እሑድ ያሚስ ያለው 7 ቀን ነው።
2.    ዚጌታ ጟምፀ ይህም ኚቅድስት ሰኞ እስኚ ሆሣዕና ዋዜማ ዓርብ ድሚስ ያለው 40 ቀን ነው።
3.    ሕማማትፀ ይህም ጌታቜን በአልዓዛር ቀት ለማዕድ ኚተቀመጠበት ዚሆሳዕና ቅዳሜ ጀምሮ እስኚ ሥዑር ቅዳሜ ያለው መኚራን ዚተቀበለበት 8 ቀን ሕማማት ነው።

ይህም 7+40+8 = 55 ቀን ማለት ነው።

ዚዲያብሎስን ሥራ ሊያፈርስዚተገለጠው ዚእግዚአብሔር ልጅም በፆም ድል ማድሚግን ለእኛ አስተምሮናል። እኛምበዚህ በአብይ ፆም ዹለመነውና ዹጠዹቅነው ነገር ሁሉ ኚኃጢአት በስተቀርእንዲኚናወንልን ፆምን ገንዘባቜን እናድርግ። በፆም ዹተጠቀሙ ቅዱሳን አባቶቜና ቅዱሳንእናቶቜ እንዳሉን እናስተውል።

ጟም ጞሎታቜን ዚቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይቀበልልን አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ደብሚ á‹˜á‹­á‰µ
ዚዐብይ ጟም አምስተኛ እሑድ(ሳምንት)
(ዚዐብይ ጟም እኩሌታ)
ደብሚ á‹˜á‹­á‰µ áˆ›áˆˆá‰µ á‹šá‹ˆá‹­áˆ« á‹›á á‹«áˆˆá‰ á‰µ á‰°áˆ«áˆ« áˆ›áˆˆá‰µ áŠá‹á¡á¡á‰Šá‰³á‹ áŠšáŠ¢á‹šáˆ©áˆ³áˆŒáˆ á‰ áˆµá‰°áˆáˆ¥áˆ«á‰… á‹šáˆšáŒˆáŠ á‹šá‹ˆá‹­áˆ« á‹›á á‹šá‰ á‹›á‰ á‰µ á‰°áˆ«áˆ« áˆ²áˆ†áŠ• áˆµáˆ™áˆ áŠšá‹ˆá‹­áˆ« á‹›á‰:- á‹°á‰¥áˆš á‹˜á‹­á‰µ (ዚወይራ á‹›á á‰°áˆ«áˆ«) á‰ áˆ˜áˆ°áŠ˜á‰µ ተገኝቷል። á‰ á‰…ድስት á‰€á‰° áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ“á‰œáŠ• á‹°á‰¥áˆš ዘይት á‰ á‹“ል ሆኖ á‹šáˆšáŠšá‰ áˆ­á‰ á‰µ áˆáŠ­áŠ•á‹«á‰µ áŒŒá‰³á‰œáŠ• áˆ˜á‹µáŠƒáŠ’á‰³á‰œáŠ• áŠ¢á‹šáˆ±áˆµ áŠ­áˆ­áˆµá‰¶áˆµ á‰ á‹°á‰¥áˆšá‹˜á‹­á‰µ á‰°áˆ«áˆ« áˆ‹á‹­ áˆ³áˆˆ áˆˆá‰…ዱሳን á‹°á‰€áˆ˜á‹›áˆ™áˆ­á‰± áˆµáˆˆ á‹“ለም ááŒ»áˆœ áŠ¥áŠ“ áˆµáˆˆ á‹³áŒáˆ áˆáŒœáŠ á‰± áˆµáˆ‹áˆµá‰°áˆ›áˆ«á‰žá‹‰ á‰ áŒŒá‰³á‰œáŠ• á‰µáˆáˆ…ርት áˆ˜áˆ áˆšá‰µ áŠáŒˆáˆš áˆáŒœáŠ á‰±áŠ• áŠ¥áŠ•á‹µáŠ“áˆµá‰³á‹áˆµ á‹ˆá‹­áˆ áŠ¥á‹«áˆ°á‰¥áŠ• áŠ¥áŠ•á‹µáŠ•á‹˜áŒ‹áŒ… áˆˆáˆ›á‹µáˆšáŒ áŠá‹á¢

ስለ ዓለም መጚሚሻና ስለ ዳግም ምጜአቱ ምልክቶቜ ምን እንደሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ማ቎ዎስ ወንጌል ላይ በሊስት መሠሚታዊ ክፍሎቜ ኹፍሎ ጜፎልናል፡፡

፩. ሃይማኖታዊ áˆáˆáŠ­á‰¶á‰œ

"እኔ áŠ­áˆ­áˆµá‰¶áˆµ áŠáŠ áŠ¥á‹«áˆ‰ á‰ áˆµáˆœ á‹­áˆ˜áŒ£áˆ‰á€ á‰¥á‹™á‹Žá‰œáŠ•áˆ á‹«áˆµá‰³áˆ‰" /ማቮ 24፥5/፡፡

፪. ፖለቲካዊ áˆáˆáŠ­á‰¶á‰œ

“ጩርንም á‹šáŒŠáˆ­áŠ•áˆ á‹ˆáˆ¬ á‰µáˆ°áˆ™ á‹˜áŠ•á‹µ áŠ áˆ‹á‰œáˆá€ á‹­áˆ… áˆŠáˆ†áŠ• áŒá‹µ áŠá‹áŠ“ á‰°áŒ á‰ á‰â€ /ማቮ 24፥6/ “ሕዝብ á‰ áˆ•ዝብ áˆ‹á‹­ áˆ˜áŠ•áŒáˆ¥á‰µáˆ á‰ áˆ˜áŠ•áŒáˆ¥á‰µ áˆ‹á‹­ á‹­áŠáˆ£áˆáŠ“â€ /ማቮ 24፥7/

፫. ተፈጥሯዊ áˆáˆáŠ­á‰¶á‰œ

“ሚሐብም á‰žáŠáˆáˆ­áˆ á‹šáˆá‹µáˆ­ áˆ˜áŠ“á‹ˆáŒ¥ á‰ áˆá‹© áˆá‹© áˆµááˆ« á‹­áˆ†áŠ“áˆâ€ /ማቮ.24፥7/

ኹላይ ያዚና቞ውን ምልክቶቜ በዓለማቜን ላይ ዕለት ዕለት ዹምናዹው ዹምንሰማው ዚአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ ጌታቜን ለደቀመዛሙርቱ ዚነገራ቞ውን ምልክቶቜ ዚቀተ ክርስቲያናቜን አራት
ዐይና ሊቃውንት ዹወንጌሉን ገጾ ንባብ እንዲህ ብለው ያመሰጥሩታል፡፡

“እነዚህ áˆáˆ‰ á‹šáˆáŒ¥ áŒ£áˆ­ áˆ˜áŒ€áˆ˜áˆªá‹«á‹Žá‰œ áŠ“á‰žá‹â€ /ማቮ.24፥8/

ምጥ ሲመጣ አስቀድሞ ዚምጡ መጀመሪያ ሕመም (ጣር) እንዳለ ሁሉ ዹዓለምም ፍጻሜ በጣር ነው ዚሚጀምሚው። ይህንንም ጌታቜን በግልጜ አስሚድቶናልፊ ጩርና ዹጩር ወሬ መሰማት፣ ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ መነሳት፣ ርሃብም ቾነፈርም ዚምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ መታዚት ለዓለም ፍጻሜ ዚምጥ ጣር መጀመሪያዎቜ ና቞ዉ። እነዚህ ነገሮቜ በሁሉም ቊታ በአንድ ጊዜ ላይኚሰቱ ይቜላሉፀ ነገር ግን በልዩ ልዩ ቊታዎቜ ለብዙ ዘመናት ታይተዋልፀ እዚታዩም ና቞ው።

“ስለ áˆµáˆœ á‰ áŠ áˆ•á‹›á‰¥ áˆáˆ‰ á‹šá‰°áŒ áˆ‹á‰œáˆ á‰µáˆ†áŠ“áˆ‹á‰œáˆâ€ /ማቮ.24፥9/

ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ "ስለ ስሜ ክርስቲያኖቜ በመሆናቜሁ በዓለም ዘንድ ትጠላላቜሁ" ብሎናል። ዓለም ክፉ ስለሚሠራ ዚጥሩ ነገር ተቃራኒ ሆኖ ለብዙ ዘመናት ቆይቷል። ጌታቜን â€œá‰¥áˆ­áˆƒáŠ•áˆ á‹ˆá‹° á‹“ለም áˆµáˆˆáˆ˜áŒ£ áˆ°á‹Žá‰œáˆ áˆ¥áˆ«á‰žá‹ áŠ­á‰ áŠá‰ áˆ­áŠ“ áŠšá‰¥áˆ­áˆƒáŠ• á‹­áˆá‰… áŒšáˆˆáˆ›áŠ• áˆµáˆˆá‹ˆá‹°á‹± ááˆ­á‹± á‹­áˆ… áŠá‹á¢ áŠ­á‰ á‹šáˆšá‹«á‹°áˆ­áŒ áˆáˆ‰ á‰¥áˆ­áˆƒáŠ•áŠ• á‹­áŒ áˆ‹áˆáŠ“á£áˆ¥áˆ«á‹‰áˆ áŠ¥áŠ•á‹³á‹­áŒˆáˆˆáŒ¥ á‹ˆá‹° á‰¥áˆ­áˆƒáŠ• áŠ á‹­áˆ˜áŒ£áˆá€ áŠ¥á‹áŠá‰µáŠ• á‹šáˆšá‹«á‹°áˆ­áŒ áŒáŠ• áˆ¥áˆ«á‹ á‰ áŠ¥áŒá‹šáŠ á‰¥áˆ”áˆ­ á‰°á‹°áˆ­áŒŽ áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ á‹­áŒˆáˆˆáŒ¥ á‹˜áŠ•á‹µ á‹ˆá‹° á‰¥áˆ­áˆƒáŠ• á‹­áˆ˜áŒ£áˆâ€ /ዮሐ. 3፥19-21/ እንዳለን በክፉ ሥራ ውስጥ ያለው ይህ ዓለም በጎ ሥራ ዚሚሠሩትን ዚክርስቶስን ተኚታዮቜ ይጠላል። ጹለማ ብርሃንን ብርሃንም ጹለማን እንደሚጠላፀ ይህ ዓለም እኛን እንዲጠላን፣ እኛ ክርስቲያኖቜ ደግሞ ይህንን ዓለም ልንጠላው ይገባል።
አሁን ባለንበት ዘመን ክርስትና እዚተጠላ፣ እዚተናቀ ነው ያለው። â€œá‰£á‹°áŒ‰á‰µâ€ á‹“ለማት ባዶ አብያተ መቅደሶቜ ቀርተው እነሆ እንመለኚታ቞ዋለንፀ ትውልዱ በዓለም ስሜትና በሥጋ ፈቃድ ብቻ እዚሔደ ነው። ክርስቲያን ነን በሚሉትም አውሮፓውያን ዘንድ ዚአንገት በላይ ዚማስመሰል ክርስትና እንጂ እንደ ቅዱስ ቃሉ ዹሚጓዝ አማኝ ማግኘት አይቻልም። እውነተኞቜ አይወደዱምፀ ይገፋሉፀ ይናቃሉ። ሁኔታው ዹዘመኑ ፍጻሜ እጅግ እዚቀሚበ መምጣቱን በእርግጥ ያስሚዳል።
ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ኹዚህም በላይ “ስለ ስሜ ለመኚራ አሳልፈው ይሰጧቜኋልፀ ይገድሏቜሁማል” ብሏል። ክርስቲያን በመሆናቾው ብቻ ማንንም ሳይበድሉ ኹዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ በልዩ ልዩ ሀገራት ክርስቲያኖቜ ሰማዕትነትን እስኚ አሁን ድሚስ እዚተቀበሉ ነው፡፡ቅዱስ ጳዉሎስ  â€œáˆµáˆˆ áŠ áŠ•á‰° á‰€áŠ‘áŠ• áˆáˆ‰ áŠ¥áŠ•áŒˆá‹°áˆ‹áˆˆáŠ•á€ áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‰³áˆšá‹± á‰ áŒŽá‰œ á‰°á‰†áŒ áˆ­áŠ•â€ /ሮሜ 8፥36/ እንዳለው። ይህ በቅዱሱ በክርስቶስ ስም መጠላትና መኚራ መቀበል ኹዓለም ዹሚጠበቅ ዚፍጻሜዉ ዘመን ምልክት መሆኑን አውቀን መዘጋጀትና ኚሐዋርያው ጋር â€œá‰ á‹šáˆ… áˆáˆ‰ áŒáŠ• á‰ á‹ˆá‹°á‹°áŠ• á‰ áŠ¥áˆ­áˆ± áŠšáŠ áˆžáŠ“áŠá‹Žá‰œ áŠ¥áŠ•á‰ áˆáŒ£áˆˆáŠ•â€ /ሮሜ 8፥37/ እያልን በእምነታቜን ጾንተን መጋደል ይገባናል።

ዚክርስቲያኖቜ ቁጥር እያነሰ መምጣት፣ ዚአብያተ ክርስቲያናት መዘጋት፣ ሰው ሰው ዚሚያሰኘውን ክብርና ሞገስ ትቶ በግብሩ እንስሳትን ሲመስል ዚቅድስና ሕይወት ሲጠላና ሲናቅፀ በአንጻሩ ደግሞ ዹሰው ልጅ ለሹኹሰው ለዚህ ዓለም ምኞትና ፈቃድ ሲገዛ ስናይ ዹዚህ ዓለም ፍጻሜ ጊዜው እዚደሚሰ መሆኑን አውቀንፀ ኖኅ በብዙ ኃጢአተኞቜ መካኚል ቢኖርም ራሱን በቅድስና ጠብቆ እንደኖሚ /ዘፍ.6-8/ፀ ሎጥም እንዲሁ በብዙ ኃጢአተኞቜ መካኚል ሲኖር በነርሱ ኃጢአት እንዳልተባበሚ /ዘፍ. 19/ ኹዚህ ዓለም ክፉ ሥራ ተለይተን ራሳቜንን በቅድስና በመጠበቅ እንጋደል። ዓለሙ ስለ እምነታቜን ቢጠላንም እኛም ስለ ክፉ ሥራው ንቀነው መኖር ዚግድ መሆኑን እንወቅ እንጂ ስለ እምነት፣ ስለ ቅድስናም ኹዓለም በጎ ነገር አንጠብቅ። በተለያዩ ሁኔታዎቜ ዚሚደርሱብንን ፈተናዎቜ ሁሉ በትዕግስት እንቀበላ቞ው እንጂ በማማሹር አንዘንፀ ምክንያቱም ስለ ስሜ በዓለም ዘንድ ዚተጠላቜሁ ትሆናላቜሁ ተብለናልና።

“ዚጥፋትን áˆ­áŠ©áˆ°á‰µ á‰ á‰°á‰€á‹°áˆ°á‰œá‹ áˆµááˆ« á‰†áˆž áˆµá‰³á‹© áŠ áŠ•á‰£á‰¢á‹ á‹«áˆµá‰°á‹áˆ!” áˆ›á‰Ž.24፥15/

ዓለም ራሱን በማርኚስ ብቻ ሳይወሰን በፍጻሜ ዘመን በተቀደሰው ስፍራ እንኳን ሳይቀር ዚጥፋትን ርኩሰት ያቆማል። ዹተቀደሰው ስፍራ ዚተባለው በተቀደሰ ሃይማኖት ዚሚኖሩትን ሀገራት፣ ሕዝቊቜ ዚሚመለኚት ነው። እንደ ኢትዮጵያ ዚመሳሰሉትን ሀገራት ዲያብሎስ በመልእክተኞቹ ላይ አድሮ በብዙ ርኩሰት ተፈታትኗ቞ዋልፀ እዚተፈታተና቞ውም ነው። ዚዚሀገራቱን እምነትና ታሪክ ለማጥፋት ጥሯልፀ ብዙውንም ዚቅድስና ሥርዓት በርዟልፀ ዚቻለውንም ኚነጭራሹ አጥፍቶታል። አሁን እንኳ አምልኮተ እግዚአብሔር በሚፈጞምባ቞ዉ ቅዱሳት መካናትና ገዳማት ሳይቀር በልዩ ልዩ ምክንያት ዚጥፋት ርኩሰት አዉጇል። ይህም ዚፍጻሜ ዘመኑ አንዱ ምልክት ስለሆነ አንባቢዉ  እንደተባለ ዹዘመኑን መፍጠን ዹጊዜውን መድሚስ በመሚዳት መዘጋጀት ይገባናል።

“ብዙ áˆáˆ°á‰°áŠ›á‹Žá‰œ áŠá‰¢á‹«á‰µáˆ á‹­áŠáˆ£áˆ‰ á‰¥á‹™á‹Žá‰œáŠ•áˆ á‹«áˆµá‰³áˆ‰â€ /ማቮ.24፥11/፡፡

ብዙ ሐሰተኞቜ ነቢያት በዹዘመኑ ተነስተው እውነተኛይቱን  ታግለዋታልፀ ሊያጠፏት ባይቜሉም እንኳን ብዙ ልጆቿን ነጥቀው ወስደውባታል። ዹነዚህን  ሠራተኞቜ አመጣጥ ኚባድ ዚሚያደርገው በተአምራትና በድንቅ ምልክቶቜ መምጣታ቞ው ነው። ጌታቜን እንደተናገሚ â€œá‰¢á‰»áˆ‹á‰žá‹áˆµ á‹šá‰°áˆ˜áˆšáŒ¡á‰µáŠ• áŠ¥áŠ•áŠ³áŠ• áŠ¥áˆµáŠªá‹«áˆµá‰± á‹µáˆšáˆµ á‰³áˆ‹áˆ‹á‰… áˆáˆáŠ­á‰µáŠ“ á‹µáŠ•á‰… á‹«áˆ³á‹«áˆ‰â€ /ማቮ.24፥24/ ስለዚህ በምትሐታዊ ምልክቶቻ቞ው ዚብዙ ዹዋሃንን ልብ በማታለል ኹተቀደሰ እምነታ቞ው እያስኮበለሉ አጥፍተዋ቞ዋልፀ በማጥፋትም ላይ ይገኛሉ። ስለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ  â€œá‹ˆá‹³áŒ†á‰œ áˆ†á‹­ áˆ˜áŠ•áˆáˆµáŠ• áˆáˆ‰ áŠ á‰µáˆ˜áŠ‘ áŠáŒˆáˆ­ áŒáŠ• áˆ˜áŠ“ááˆµá‰µ áŠšáŠ¥áŒá‹šáŠ á‰¥áˆ”áˆ­ áˆ†áŠá‹‰ áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ áˆ˜áˆ­áˆáˆ©â€/1ዮሐ 4፥1-3/ አለን።
ቅዱስ ጳዉሎስም “ዚክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳ቞ዉን እዚለወጡ ውሞተኞቜ ሐዋርያትና ተንኮለኞ ሠራተኞቜ ና቞ው። ይህም ድንቅ አይደለም ሰይጣን ራሱ ዚብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለዉጣልና” ብሏል /2ቆሮ.11፥13-15/። ሐዋርያት ሁሉ በዚመልእክቶቻ቞ው ኚሐሰተኞቜ አስተማሪዎቜ እንድንጠበቅ ደጋግመው አሳስበዋል። ብዙ ሰው ግን በዚዋሕነት ስለሚጓዝ ዹነዚህ ተኩላዎቜ ሰለባ ሆኗል።
ጊዜው ክፉ ነውና ዚሐሰተኞቜ ነቢያት መሚብ ጠልፎ ወደ ሐሰተኞቜ ክርስቶሶቜ እንዳይወስደን
#በጥንቃቄ መጓዝ ይጠበቅብናል። ሐዋርያዉ ቅዱስ ይሁዳም በመልእክቱ ቁ.3  â€œáˆˆá‰…ዱሳን áŠ áŠ•á‹µ áŒŠá‹œ áˆáŒœáˆž áˆµáˆˆá‰°áˆ°áŒ  áˆƒá‹­áˆ›áŠ–á‰µ áŠ¥áŠ•á‹µá‰µáŒ‹á‹°áˆ‰ áŠ¥á‹šáˆ˜áŠšáˆ­áŠ³á‰œáˆ áŠ¥áŒœááˆ‹á‰œáˆ á‹˜áŠ•á‹µ áŒá‹µ áˆ†áŠá‰¥áŠâ€ áˆ²áˆ እንደመኚሚን በተቀደሰ እምነታቜን እስኚመጚሚሻ ጾንተን እንጋደል።

#በቅዳሎ #ጊዜ# ዚሚነበቡ #ጥቅሶቜፊ
-፩ኛ ተሰ ፬፥፲፫ እስኚ ፍጻሜ
-፪ኛ ጎጥ ፫፥፯-፲፭
-ዹሐዋ ሥራ ፳፬፥፩-፳፪

#ምስባኩምፊ መዝ ፵፱፥፫
"እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጜእ ወአምላክነሂ ኢያሚምም #
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ"
"እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካቜን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል"

#ወንጌል፩ ማቮ ፳፬፥፩-ፎ፮
#መጋቢት_27

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
         አሐዱ አምላክ አሜን።

🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
እንኳን ለአባታቜንና ለአምላካቜን ለመድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብሚ በዓል በሰላም አደሹሰን አደሚሳቜሁ!!!
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺


✞ መ ድ ኃ ኔ ዓ ለ ም -  ክ ር ስ ቶ ስ ✞

ጌታቜን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈፀመው ዚማዳን ስራ ክፉዎቜ አይሁድ ኚምሜቱ ሊስት ሰዓት ጌቮሮማኒ ውስጥ ያዙት።

ሙሉውን ሌሊት ኚቀያፋ ወደ ሐናፀ ኹሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት አስሚው ሲደበድቡት አድሚዋል።

ዝም ቢላ቞ው ዓይኑን ሾፍነው በጥፊ መቱት።

ምራቃ቞ውን ተፉበትፀ ዘበቱበት።

ራሱንም በዘንግ መቱት።

እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ። በጧት ኚገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈሚድበት አቀሚቡት። በሠለስት (ሊስት ሰዓት ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እዚተዘባበቱ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ገሚፉት።

ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሾክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት። ስድስት ሰዓት ላይ በሚዣዥም ብሚቶቜ አምስት ቊታ ላይ ቾንክሹው ሰቀሉት። ሰባት ታላላቅ ታአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ። ዓለም በጹለማ ሳለቜ ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገሚ። ኹቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አኚባቢ በባሕርይ ስልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ኚቅዱስ ሥጋው ለዚ።

በዚያቜ ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ ዚታሠሩትን ሁሉ ፈታ። አስራ አንድ ሰዓት ላይ ደጋጉ ዮሎፍና ኒቆዲሞስ ኚታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት።

በዚያቜ ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ። ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍጹም ለቅሶን አለቀሰ። ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ።

ለእኛ ለኃጥአን ፍጡሮቹ ሲል ይህንን ሁሉ መኚራ ዚታገሰ አምላክ ስለ አሥራ ሊስቱ ኀማማቱፀ አምስቱ ቅንዋቱፀ ስለ ቅዱስ መስቀሉፀ ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶና ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማሚን።

-------------------------------------------
"በእውነት ደዌአቜንን ተቀበለ። ሕማማቜንንም ተሞክሟል። እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቾገሹም ቆጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋቜን ቆሰለ። ስለ በደላቜንም ደቀቀ። ዚደኅንነታቜንም ተግሣጜ በእርሱ ላይ ነበሚ። በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን።"  (ኢሳ ፶፫፥፬-፭)

     <<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>>

#ስንክሳር_ዘወርሃ_መጋቢት

ይቀላቀሉ ሌሎቜንም ይጋብዙ!
https://www.tgoop.com/tmhrteorthodox
ኒቆዲሞስ፡ዚዐቢይ ጟም ሰባተኛ ሳምንት

በመ/ር ጌታ቞ው በቀለ

በኊርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ዚበዓላት ቀኖና መሠሚት ሰባተኛው ዚዐቢይ ጟም ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል፡፡ በዚህ ሰባተኛው ሳምንት ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ኒቆዲሞስ ለተባለ ዚአይሁድ አለቃ ያስተማሚው ትምህርት ይነበባል፣ ይተሚጎማል፣ ይዜማል /ዮሐ ፫፥፩-፳፩/፡፡

ኒቆዲሞስ ማን ነዉ?

ኒቆዲሞስ ቃሉ ዚግሪክ ሲሆን ድል ማድሚግን ወይም አሞናፊነትን ያመለክታል፡: ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፥ ኚአይሁድ አለቆቜና መምህራና አንዱ ነው። በወንጌለ ዮሐንስ ምዕራፍ ሊስት ኚፈሪሳውያን ወገን ዚአይሁድ አለቃ ዹሆነ ኒቆዲሞስ ዚተባለ አንድ ሰው እንደነበሚና እርሱም በሌሊት ወደ ጌታቜን መጥቶ እንደተማሚ ተጠቅሷል /ዮሐ ፩-፪/፡፡ በአይሁድ አለቆቜ ፊትም “ሕጋቜን አስቀድሞ ሳይሰማ ዚሠራውንም ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?” በማለት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ዹተናገሹ እሱ ነው። እነርሱ ግን በክርስቶስ እግዚአብሔርነት ያመኑበት ኊሪትን ዚማያዉቁ ስሑታን እንደሆኑ ያስቡ ስለ ነበር “አንተም ደግሞ ኹገሊላ ነህን? ኹገሊላ ነቢይ እንደማይነሣ መርምርና እይ” አሉት እንጂ አልተቀበሉትም /ዮሐ ፯፥፵፰-፶፪/። ኒቆዲሞስ ዚአርማትያስ ሰው ኹሚሆን ኚዮሎፍ ጋር በመሆን ዚጌታቜንን ቅዱስ ሥጋ በንጹሕ በፍታ ገንዞ በአዲስ መቃብር ቀብሯል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “ቀድሞ በሌሊት ወደ ጌታቜን ኢዚሱስ ሄዶ ዹነበሹዉ ኒቆዲሞስም መጣፀ ቀብተውም ዚሚቀበርበትን መቶ ወቄት ዚኚርቀና ዚሬት ቅልቅል ሜቶ አመጣ።” እንዳለ /ዮሐ ፲፱፥ፎ፱/። በዚህም ኒቆዲሞስ ኹምክሹ አይሁድ ያልተቀላቀለ መሆኑ ይታወቃል።

ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ብቻ ሳይሆን ዚፈሪሳውያን አለቃ፣ ዚኊሪት መምህር ብቻ ሳይሆን ዚኊሪት ምሁርም ነበር፡፡ በእርሱ ደሹጃ ዚነበሩ ታላላቅ ዚአይሁድ ምሁራን መንፈሳዊ ሥልጣና቞ውና ሹመታ቞ው ዚእግዚአብሔር ስጊታ መሆኑን ሚስተው በሕዝቡ ላይ ዚሚመጻደቁ ነበሩ፡፡ በዘመናቾው ዕውቀትን ዚሚገልጥ እውነተኛ አምላክ፣ ዚካህናት አለቃ ኢዚሱስ ክርስቶስ ለቀዛ ዓለም ሲገለጥ ዚአይሁድ ምሁራን ዚጌታን መገለጥ አልወደዱትም፡፡ ዚእርሱ ትሕትና ዚእነርሱን ትዕቢት ዚሚያጋልጥ ነበርና ወደ ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚሚሄዱትን ሁሉ ይነቅፉ ይኚስሱ ነበር፡፡ ጌታቜንም ዚፈሪሳውያን ሐሳባ቞ው በግብዝነት ዹተሞላና ኚንቱም እንደሆነ ነግሯ቞ዋል፡፡ ለደቀመዛሙርቱም ኚጻፎቜና ኚፈሪሳውያን ጜድቅ ዚሚበልጥ ሥራን እንዲሰሩ አስጠንቅቋ቞ዋል /ማቮ.፭፥፳ፀማ቎.፲፮፥፮/፡፡

ኒቆዲሞስ ወደ ጌታቜን በሌሊት ዹሄደዉ ለምንድነው? ለምን በቀን አልሄደም?

ኒቆዲሞስ በመጀመሪያ ወደ ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚመጣው በቀን ሳይሆን በሌሊት ነበር፡፡ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታቜን ኚሄደባ቞ው ምክንያቶቜ አንዱ በቀን መሄድን ስለፈራ ነው። ለዚህም ዚቀተ ክርሰቲያን አባቶቜ በዋናነት ሁለት ምክንያቶቜን ያስቀምጣሉ፡፡ ዚመጀመሪያው ዚአይሁድ መምህር ሆኖ ሳለ በቀን በሕዝብ ፊት ኚጌታቜን ኚኢዚሱስ ክርስቶስ መማር ስላፈሚ ነው ዹሚል ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ አይሁድ “ኚእኛ ወገን በክርስቶስ ያመነ ቢኖር ኚምኩራብ ይሰደድ” ዹሚል ዐዋጅ ዐውጀው ነበርና ያንን ፈርቶ ነው ይላሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ፍራቻዎቜ ኒቆዲሞስን ወደ ክርስቶስ ኚመምጣት አላገዱትም፡፡
ኒቆዲሞስ በርቀት በአደባባይ ድንቅ ተአምራትን ሲያደርግ ያዚውን ኢዚሱስ ክርስቶስን ቀርቩ መጠዹቅ መማር ፈልጓል፡፡ ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ካደሚጋ቞ው ተአምራት ዚተሚዳው ነገር ቢኖርም ቀርቩ ደግሞ ኚእርሱ ኚራሱ ስለማንነቱ መስማት ፈልጓል፡፡ ወደ ክርስቶስም ቀርቩ “መምህር ሆይ እግዚአብሔር ኚእርሱ ጋር ኹሆነ በቀር አንተ ዚምታደርጋ቞ውን እነዚህን ምልክቶቜ ሊያደርግ ዚሚቜል ዹለምና መምህር ሆነህ ኚእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን” አለው /ዮሐ.፫፥፪/፡፡
ኒቆዲሞስ ግን ኚእነዚህ ኚፈሪሳዊያን መካኚል ዹተገኘ ልዩ ምሁሹ ኊሪት ነበር፡፡ ኒቆዲሞስ ራሱን ለእውነት ልቡን ለእምነት አዘጋጅቶ ኹሁሉ ቀድሞ በሌሊት ክርስቶስን ፍለጋ ዚመጣ ኚእነዚህ ፈሪሳዊያን ወገን ተለይቶ ወደ ጜድቅ መንገድ ዚተጠራ ነው፡፡ ሹመት እያለው ሁሉ ሳይጎድልበት በዙርያው ዚነበሩት ኚእኛ በላይ ማን አዋቂ አለ ዹሚሉ ኚእውነት ጋር ዚተጣሉ ጌታቜንን ዚሚያሳድዱ በእርሱም ዹሚቀኑና ጌታቜንንም ለመግደልም ዕለት ዕለት ዚሚመክሩ ሁነው ሳለ ኒቆዲሞስ ግን እውነትን ለማወቅ እልቅናው ሳይታሰበው፣ ኚአካባቢው ጋር መመሳሰልን ሳይመርጥ ራሱን ዝቅ አድርጎ ኚጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሊማር በሌሊት መጣ፡፡ መምህሹ ትሕትና ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስም ዚኒቆዲሞስን ትሕትናውን ተቀብሎ እስኚ ዓለም ፍጻሜ ድሚስ ትውልድ ሁሉ ዚሚማርበትን ሹቂቁን ምስጢሚ ጥምቀትን አስተማሚው፡፡

ዳግመኛ ዚመወለድ ምስጢር

ኒቆዲሞስ ዳግመኛ ዚመወለድን ምስጢርን ለማወቅ ልቡናውን ኹፍ ኹፍ አደሚገ፡፡ ኒቆዲሞስ በመጀመርያ ዚጥምቀትን ነገር ሲሰማ ለመቀበል ተ቞ግሮ ነበር፡፡ ጌታቜን ግን ዚኒቆዲሞስን አመጣጥ በማዚት ልቡናውንም ኹፍ ኹፍ ስላደሚገ ምስጢሚ ጥምቀትን ገለጞለት፡፡ “ቅዱሱን ማወቅ ማስተዋል ነው” ተብሎ በምሳሌ መጜሐፍ እንደተጻፈ /ምሳ 9፥11/ ኒቆዲሞስ ኚፈሪሳውያን ኅብሚት ወጥቶ በትሕትና ወንጌልን ለመማር፣ በሃይማኖት ልቡናውን ለእግዚአብሔር ቃል አዘጋጀ፡፡ ለአብርሃም ዚግዝሚትን ጾጋ ዹሰጠ ጌታ በትሕትና ለቀሹበው ኒቆዲሞስ ዚግዝሚት ጾጋ ፍጻሜ ዚሆነቜ ዚልጅነት ጥምቀትን ነገር አስተምሮታል፡፡

ኒቆዲሞስ ወደ መድኃኔዓለም ለመማር ዹሄደው በሌሊት ነበር፡፡ ኒቆዲሞስ በሚታሰብበት ዚዐቢይ ጟም ሰንበት በጾሎተ ቅዳሎ ዹሚዜመው ዚክቡር ዳዊት መዝሙር “በሌሊት ጎበኘኞኝፀ ልቀንም ፈተንኞው፣ ፈተንኞኝ፣ ዐመፅም አልተገኘብኝም፡፡ ዹሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር” ይህን ዚሚያስሚዳ ነው /መዝ.፲፮፥፫/፡፡ ሌሊት በባሕሪው ሕሊናን ለመሰብሰብ በተመስጊ ለመማር ዚሚመቜ ነው፡፡ ክርስትናም በተጋድሎ ሕይወት በመትጋት ሥጋን በቀንና ሌሊት ለነፍስ እንዲገዛ በማድሚግ ዹሚኖር ሕይወት ነው፡፡ ጌታቜን ሐዋርያቱን “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጞልዩ” ባለው መሠሚት ቀተክርስቲያንም በቀንና በሌሊት በኪዳኑ በቅዳሎው በማህሌቱ እግዚአብሔርን ታመሰግናለቜ፡፡

ዮሐንስ ወንጌላዊ ይህንን ዚኒቆዲሞስን ምስክርነት “ኚእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ ዹነበሹ ኒቆዲሞስ ሕጋቜን አስቀድሞ ኚእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደሚገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላ቞ው። እነርሱም መለሱና፡- አንተም ደግሞ ኹገሊላ ነህን? ነቢይ ኹገሊላ እንዳይነሣ መርምርና እይ አሉት። እያንዳንዱም ወደ ቀቱ ሄደ።” በማለት ገልጟታል /ዮሐ.፯፥፶-፶፪/፡፡ ኒቆዲሞስ ያለፍርሐትና ያለ ሀፍሚት በካህናቱ ፊት እውነትን መስክሯል፡፡ ካህናቱን መጜሐፍ ጠቅሶ እውነትን ተናግሮ አሳፍሯ቞ዋል፡፡ ኒቆዲሞስ እስኚ መጚሚሻው በመጜናት ለታላቅ ክብር በቃ፡፡
ኒቆዲሞስም ኚጌታቜን በተማሹው ትምህርት ጞንቶ ለመኖር ዹበቃ አባት ነው፡፡ ዚሃይማኖቱ ጜናትም በተግባር ዹተፈተነ ነው፡፡ ለዚህም ማሳያ ዹሚሆነን ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ ዚአርማትያስ ሰው ኹሚሆን ኚዮሎፍ ጋር በመሆን ዚአይሁድን ድንፋታ ሳይፈራ “እሱን ያገኘ ያገኘኛል” ሳይል በድፍሚት ዚጌታቜንን ቅዱስ ሥጋውን በንጹሕ ዚተልባ እግር በፍታ ገንዞ በአዲስ መቃብር፣ በጌቮሮማኒ ዹቀበሹ ሰው ነው /ዮሐ.፲፱፥ፎ፰/፡፡ ኒቆዲሞስ ኚሐዲስ ኪዳን ካህናት ቀድሞ ዚጌታቜንን ነፍስ ዹተለዹው መለኮት ዹተዋሐደው ክቡር ሥጋ ለመገነዝ ዹበቃ አባት ነው፡፡ ዚጌታቜንን ክቡር ሥጋ ገንዘው ሲቀብሩም በጞናቜ ዚተዋሕዶ እምነት ጌታ እንደገለጠላ቞ው “ቅዱስ እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ኃያል፣ ቅዱስ ህያው ዘኢይመውት” ዹሚለውን ቀተክርስቲያናቜን እስኚ ዕለተ ምጜአት ዚክርስቶስን ሥጋና ደም ስትባርክ ዚምትጠቀምበትን ጞሎት እስኚ ፍጻሜው እዚጞለዩ ነበር፡፡ በዚህም ኒቆዲሞስ ኚሐዲስ ኪዳን ካህናት ቀድሞ ምስጢሚ ጥምቀትን ኚጌታ እንደተማሚ፣ ዚሐዲስ ኪዳንን ዚምስጢራት አክሊል ምስጢሚ ቁርባንንም እንዲሁ ተማሚ፡፡ ይህንንም በሚመለኚት ሊቁ አባ ሕርያቆስ በቅዳሎ ማርያም ድርሰቱ አብሮት ይቀድስ ዹነበሹውን ንፍቅ ካህን በባሚኚበት አንቀጜ “በዚህ ምስጢር እዚተራዳኝ ኚእኔ ጋር ያለ ይህንን ካህን እርሱንም እኔንም ሥጋህን እንደገነዙት እንደ ዮሎፍና እንደ ኒቆዲሞስ አድርገን” /ቅዳሎ ማርያምፀ ቁ.115/ ብሏል፡፡

እንደ ማጠቃለያ

እኛም እንደ ኒቆዲሞስ በዕውቀታቜን፣ በሥልጣናቜን፣ በሀብታቜን፣ ባለን ማንነት ሳንታበይ ራሳቜንን ዝቅ በማድሚግ ዚእውነተኛ አባቶቜን ትምህርት፣ ምክርና ተግሣጜ ልናዳምጥ በተግባርም ልናውለው ይገባናል፡፡ ምድራዊ አመክንዮ ሳያሰናክለን በቀንና በሌሊት ወደ አማናዊት ዚክርስቶስ ቀተክርስቲያን ለምስጋና መሄድ ይኖርብናል፡፡ ክርስትና ምድራዊ ስጊታና ተዓምራት በሚገለጥበት በገሊላ ባሕር አጠገብ ብቻ ሳይሆን መኚራና ስቃይ ባለበት በቀራንዮም መገኘትን ይጠይቃልፀ በፈተናና በመኚራ ጊዜም ቢሆን በእምነት ልንጾና ዹበለጠም በመታመን ልናገለግል ይገባል፡፡

ኚኒቆዲሞስ ሕይወት ተምሹን በሃይማኖት እንድንጞና ዚአባቶቻቜን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ ጌታቜን መድኃታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ “ያመነ ዹተጠመቀ ይድናል፡፡ ያላመነ ያልተጠመቀ ግን ይፈሚድበታል” /ማር.፲፮፥፮/ በማለት በሰጠን ቃል ኪዳን መሠሚት በአምላክነቱ አምነን ዚመንግሥቱ ወራሟቜ እንሆን ዘንድ ይፍቀድልንፀ ለኒቆዲሞስ ምሥጢሩን እንደ ገለጾ ለእኛም ይግለጜልንፀ አሜን፡፡

ምንባባት ኒቆዲሞስ
መልዕክታት
✍ ሮሜ ፯፥፩-፲፱
✍ 1ኛ ዮሐ.፬፥፲-ፍጻ
ግብሚ ሐዋርያት
✍ ሐዋ.ሥራ ፭፥ፎ፬—ፍጻ
ምስባክ
✍ መዝ.፲፮÷፫
ሐውጜኚኒ ሌሊት ወፈተንኮ ለልብዚ፥
አመኹርኹኒ ወኢተሚክበ አመጻ በላዕሌዚፀ
ኹመ ኢያንብብ አፍዹ ግብሚ ዕጓለ እመሕያው

ትርጉምፊ ልቀን ፈተንኾው በሌሊትም ጐበኘኞኝፀ ፈተንኞኝ፥ ምንም አላገኘህብኝም። ዹሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዮ ነው፡፡
ወንጌል
✍ ዮሐ.፫÷፩-፳
ዚዕለቱ ቅዳሎ
✍ ቅዳሎ እግዚእ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዋቀ መጻሕፍት፡-
✍ መጜሐፍ ቅዱስ
✍ ሃይማኖተ አበው
✍ ቅዳሎ ማርያም
✍ ዚቀተክርስቲያን መዝገበ ቃላት
2025/06/28 02:31:33
Back to Top
HTML Embed Code: