❤️በቤተ ክርስቲያን 5 አይነት አክሊላት አሉ❤️
1 አክሊለ ሰማዕት
ይህ አክሊል ሰማእታት በተጋድሎ የሚያገኙት አክሊል ነው ቅዱስ
ጳውሎስም ስለዚህ አክሊል ሲናገር ሃይማኖቴን ጠብቄለው ሩጫዬን ጨርሻለው ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ብሎ ጠቅሶታል
2 ጢሞ 4+6-7
በተመሳሳይ ባለራዕዩ ቅዱስ ዮሐንስም እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወት አክሊል እሰጥሃለው ብሎ የተናገረው ስለ ሰማእታት አክሊል ነው ራዕ 2+10 ክርስቶስም አክላሎሙ ለሰማእት ተብሏል እመቤታችንም አክሊለ ሰማእት ትባላለች
2 አክሊለ ሶክ (አስኬማ መላእክት)
ይሄ አክሊል የአባ እንጦንዮስ አክሊል ሲሆን መነኮሳት የሚያደርኩት አክሊል ነው ይሄ አክሊል በምንኩስና ዓለምን ከናቁ በኋላ የሚገኝ ነው ክርስቶስ በዕለተ አርብ የተቀበለው አክሊለ ሶክ የሚታሰብበት ሲሆኔ ይሄን አክሊል ያደረጉ መነኮሳት እንደ መላእክት በንጽሕና በቅድስና ስለሚኖሩ አስኬማ መላእክት ተብሏል
3 ተክሊል (የተክሊል አክሊል)
ይህ አክሊል በድንግልና ኑረው ለሚጋቡ ኦርቶዶክሳውያን የሚደረግ የድንግልና ምልክት የሆነ አክሊለ ከብካብ ነው ደናግል ላልሆኑ ፈጽሞ የማይደረግ ነው
4 አክሊለ ነገሥት ይህ አክሊል ለነገሥታት ብቻ የሚደረግ ነው ሰሎሞን ሲነግሥ ሲቀባ የተደረገለት አክሊል ነው አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው ወአክሊሉ ለሰሎሞን የሰሎሞን አክሊል ነሽ ብሎ የተናገረው የነገሥታት አክሊል እመቤታችን እንደሆነችና ነገሥታት ሲነግሢ ተቀብተው አክሊል እንደሚያደርጉ ለመግለጽ ነው
5 አክሊለ ካህናት
ይህ አክሊል በክህነት የሚያገለግሉ ካህናትና ዲያቆናት የሚያደርርጉት አክሊል ነው
ክህነት ለሌለው ፈጽሞ የማይደረግ ሲሆን የካህናት አክሊል አሰራሩ ከላይ 4 ማዕዘን ሲሆን የዲያቆናት አክሊለም በአሰራር ከካህናት የተለየ ክብ ነው ዲያቆን የቄሱን አክሊል ፈጽሞ ማድረግ አይችልም አምስቱ አክሊላት እነዚህ ናቸው
አሁን አሁን ግን የካህኑን እና የዲያቆኑን አክሊል ሴቶች ሳይቀር አድርገውት እየታየ ስለሆነ እጅግ የሚያሳዝን ነው
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየተጣሰ ቸል ተብሎ እየታየ ነው ስለዚህ የሊቃውንት ጉባኤ ይሄን ጉዳይ እልባት ሊሰጥበት ይገባል።
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
1 አክሊለ ሰማዕት
ይህ አክሊል ሰማእታት በተጋድሎ የሚያገኙት አክሊል ነው ቅዱስ
ጳውሎስም ስለዚህ አክሊል ሲናገር ሃይማኖቴን ጠብቄለው ሩጫዬን ጨርሻለው ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ብሎ ጠቅሶታል
2 ጢሞ 4+6-7
በተመሳሳይ ባለራዕዩ ቅዱስ ዮሐንስም እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወት አክሊል እሰጥሃለው ብሎ የተናገረው ስለ ሰማእታት አክሊል ነው ራዕ 2+10 ክርስቶስም አክላሎሙ ለሰማእት ተብሏል እመቤታችንም አክሊለ ሰማእት ትባላለች
2 አክሊለ ሶክ (አስኬማ መላእክት)
ይሄ አክሊል የአባ እንጦንዮስ አክሊል ሲሆን መነኮሳት የሚያደርኩት አክሊል ነው ይሄ አክሊል በምንኩስና ዓለምን ከናቁ በኋላ የሚገኝ ነው ክርስቶስ በዕለተ አርብ የተቀበለው አክሊለ ሶክ የሚታሰብበት ሲሆኔ ይሄን አክሊል ያደረጉ መነኮሳት እንደ መላእክት በንጽሕና በቅድስና ስለሚኖሩ አስኬማ መላእክት ተብሏል
3 ተክሊል (የተክሊል አክሊል)
ይህ አክሊል በድንግልና ኑረው ለሚጋቡ ኦርቶዶክሳውያን የሚደረግ የድንግልና ምልክት የሆነ አክሊለ ከብካብ ነው ደናግል ላልሆኑ ፈጽሞ የማይደረግ ነው
4 አክሊለ ነገሥት ይህ አክሊል ለነገሥታት ብቻ የሚደረግ ነው ሰሎሞን ሲነግሥ ሲቀባ የተደረገለት አክሊል ነው አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው ወአክሊሉ ለሰሎሞን የሰሎሞን አክሊል ነሽ ብሎ የተናገረው የነገሥታት አክሊል እመቤታችን እንደሆነችና ነገሥታት ሲነግሢ ተቀብተው አክሊል እንደሚያደርጉ ለመግለጽ ነው
5 አክሊለ ካህናት
ይህ አክሊል በክህነት የሚያገለግሉ ካህናትና ዲያቆናት የሚያደርርጉት አክሊል ነው
ክህነት ለሌለው ፈጽሞ የማይደረግ ሲሆን የካህናት አክሊል አሰራሩ ከላይ 4 ማዕዘን ሲሆን የዲያቆናት አክሊለም በአሰራር ከካህናት የተለየ ክብ ነው ዲያቆን የቄሱን አክሊል ፈጽሞ ማድረግ አይችልም አምስቱ አክሊላት እነዚህ ናቸው
አሁን አሁን ግን የካህኑን እና የዲያቆኑን አክሊል ሴቶች ሳይቀር አድርገውት እየታየ ስለሆነ እጅግ የሚያሳዝን ነው
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየተጣሰ ቸል ተብሎ እየታየ ነው ስለዚህ የሊቃውንት ጉባኤ ይሄን ጉዳይ እልባት ሊሰጥበት ይገባል።
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
YouTube
⭕"ቤተ ክርስቲያንን ለተሀድሶ አሳልፎ ለመስጠት መንገድ ጠራጊዎች ናቸው" ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ |አክሊል | ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
private የተደረገው ቪዲዮ ለማየት ከፈለጋችሁ https://youtu.be/m8uBgImVbB0
ይህንን ቻናል ለማሳደግ እና እገዛ ለማድረግ ከፈለጋችሁ
የንግድ ባንክ 1000148595918
አቢሲኒያ ባንክ 45326977
ዘመን ባንክ 1551211205309013
የምጠቀምበትን ማይክ ለማወቅ 👉🏿 https://www.youtube.com/watch?v=UfmkIR3Af8I
ሁለተኛ ቻናሌ ለመቀላቀል http…
ይህንን ቻናል ለማሳደግ እና እገዛ ለማድረግ ከፈለጋችሁ
የንግድ ባንክ 1000148595918
አቢሲኒያ ባንክ 45326977
ዘመን ባንክ 1551211205309013
የምጠቀምበትን ማይክ ለማወቅ 👉🏿 https://www.youtube.com/watch?v=UfmkIR3Af8I
ሁለተኛ ቻናሌ ለመቀላቀል http…
👍2
በአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በሊባኖስ የፓኖሲያን ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አናንያ ኩጃኒያን ሊባኖስ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት ተገደሉ !ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም
ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አራም ቀዳማዊ በጳጳሱ ግድያ የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የሊባኖስ ሪፐሊክ ፕሬዝዳንት ጄኔራል ጆሴፍ አውን በሊባኖስ የአርመን ኦርቶዶክስ ጳጳስ የማኅበረሰብ ጉዳዮችን በመምራት ላይ ሳሉ በተፈፀመው ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።
ፕሬዝደንቱ ወንጀሉን አጥብቀው እንደሚያወግዙ የገለጹ ሲሆን የፀጥታ አካላት የወንጀል ሁኔታን ለማወቅ ፣ወንጀለኞችን ለመያዝ እና ለሚመለከተው የፍትህ አካል እንዲተላለፉ ለማድረግ ምርመራቸውን እየተከታተሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የደኅንነት ምንጮች እንደገለፁት ጳጳሱ ትናንት ከሰዓት በኋላ መጥፋታቸው ተነግሯል። በምርመራው ወቅት የጸጥታ አካላት አስከሬናቸውን በቤታቸው ውስጥ በማግኘታቸው መገደላቸውን አረጋግጠዋል።
©ተ.ሚ.ማ
ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አራም ቀዳማዊ በጳጳሱ ግድያ የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የሊባኖስ ሪፐሊክ ፕሬዝዳንት ጄኔራል ጆሴፍ አውን በሊባኖስ የአርመን ኦርቶዶክስ ጳጳስ የማኅበረሰብ ጉዳዮችን በመምራት ላይ ሳሉ በተፈፀመው ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።
ፕሬዝደንቱ ወንጀሉን አጥብቀው እንደሚያወግዙ የገለጹ ሲሆን የፀጥታ አካላት የወንጀል ሁኔታን ለማወቅ ፣ወንጀለኞችን ለመያዝ እና ለሚመለከተው የፍትህ አካል እንዲተላለፉ ለማድረግ ምርመራቸውን እየተከታተሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የደኅንነት ምንጮች እንደገለፁት ጳጳሱ ትናንት ከሰዓት በኋላ መጥፋታቸው ተነግሯል። በምርመራው ወቅት የጸጥታ አካላት አስከሬናቸውን በቤታቸው ውስጥ በማግኘታቸው መገደላቸውን አረጋግጠዋል።
©ተ.ሚ.ማ
❤1
ት/ቤቶቻችን እና መስተጋብራቸው
***
በቤተ ክርስቲያን የአብነት ት/ቤት ወጥ የሆነ ዘመናትን የተሻገረ ርቱዕ ትምህርት ይሰጣል፤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ይወጡበታል። እነዚህ መምህራን የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና እና አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ በዚህ የአብነት መሠረታቸው ይመለከታሉ፤ ያብራራሉ።
ቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸው የሥነ መለኮት ት/ቤቶችም አሏት። እነዚህ ት/ቤቶች ሰፋ ያሉ የጥንት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፣ ታሪክ፣ የአበው ድርሳናት (ወደ ግእዝ ተተርጉመው የማናገኛቸውን ወይም ቀድሞ ኖረው በኋላ የጠፉትን ጨምሮ)፣ ንጽጽራዊ ሥነ መለኮት እና ነገረ-መለኮትን ለመረዳት የሚጠቅሙ ልዩ ልዩ ጥንታውያን ቋንቋዎች ይሰጡባቸዋል። ምርምር እንደሚያስፈልጋቸው በሚታመንባቸው ጉዳዮች ላይ ጥናቶችም ይሠሩባቸዋል።
ቤተ ክርስቲያን አብነቱን እንደያዘች ሥነ መለኮት ት/ቤቶች እንደሚያስፈልጓት አምና ሁለቱንም ይዛለች። ይህ የሌሎች ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት እውነታም ነው።
ለወደፊቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ተግዳሮት ከሚፈጥሩ ነገሮች አንዱ የሁለቱ ት/ቤቶች መስተጋብር ነው። መፈራረጅ እና መቆሳሰል ብዙ ጉዳት አድርሶ የግለሰቦች መጣያ እና መጠላለፊያ ከመሆኑ በፊት በትልቁ ምሥል ላይ በቂ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል። በጉዳዮች ላይ በቂ ውይይት ሳይደረግ ሲቀር ጉዳይ ግለሰባዊ መነቃቀፊያ ወደ መሆን ይወርዳልና።
ጤናማው የአካሄድ መሥመር የቱ ነው? በአብነቱ የማናገኛቸውን ነገር ግን በዘመኑ ለሚነሡ ጥያቄዎች አስፈላጊ የሆኑ የአበው ድርሳናት እና የታሪክ ምንጮች እንዴት እንጠቀም? ተቃርኖ የሚመስሉ ነገሮች ሲገጥሙ እንዴት እንፍታ? የሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሊቃውንት መጻሕፍት ስናነብ የሚያስፈልገው ጥንቃቄ ምንድር ነው? የሚሉት እና መሰል ጉዳዮች ሳይረፍድ እና ችግሮች ሳይገነግኑ ለውይይት መቅረብ ይኖርባቸዋል።
የእኔን አጭር እይታ ላስቀምጥ። በሥነ መለኮት ት/ቤቶች የሚማሩ ሰዎች የአብነቱን ትምህርት ትልቅ ዋጋ ሰጥተው ማጥናት ይገባቸዋል፤ የአብነቱን ት/ት ዜማውን ለመማር ቢከብድ እንኳ ይዘቱን (መልእክቱን) አክብሮ ማወቅ እና መረዳት ግዴታ ይመስለኛል። በአብነት ት/ቤት ያሉ ሊቃውንት ደግሞ የሥነ መለኮት ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ተጨማሪ እውቀቶች እና ምንጮች ቢያገኙ የአብነቱን የበለጠ በጥልቀት ለመረዳት እና ለማብራራት ይረዳቸዋል። ነገሮችን ከታሪካዊ ዳራቸው ለመረዳት እና ታሪካዊ ዓውዳቸውን ለመረዳት የሥነ መለኮት ምንጮች ጠቃሚ ናቸው። በመሆኑም ሳይጠራጠሩት በበጎ ኅሊና ሊያዩት፣ እድሉ ከተገኘም ሊማሩት ይገባል። በተለይ ደግሞ የአብነት መሠረት ያላቸው ሊቃውንት የሥነ መለኮት ት/ቤቶች ውስጥ መኖራቸው ሁለቱንም በአግባቡ የመያዝ ሕያው ምስክሮች ስለሚሆኑ በእጅጉ ጠቃሚ ይሆናል። በዚህ መንገድ ለቤተ ክርስቲያን የሠመረ አገልግሎት ትልቅ መመጋገብ ሊኖራቸው ይችላል።
✍️ዲያቆን በረከት አዝመራው
***
በቤተ ክርስቲያን የአብነት ት/ቤት ወጥ የሆነ ዘመናትን የተሻገረ ርቱዕ ትምህርት ይሰጣል፤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ይወጡበታል። እነዚህ መምህራን የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና እና አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ በዚህ የአብነት መሠረታቸው ይመለከታሉ፤ ያብራራሉ።
ቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸው የሥነ መለኮት ት/ቤቶችም አሏት። እነዚህ ት/ቤቶች ሰፋ ያሉ የጥንት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፣ ታሪክ፣ የአበው ድርሳናት (ወደ ግእዝ ተተርጉመው የማናገኛቸውን ወይም ቀድሞ ኖረው በኋላ የጠፉትን ጨምሮ)፣ ንጽጽራዊ ሥነ መለኮት እና ነገረ-መለኮትን ለመረዳት የሚጠቅሙ ልዩ ልዩ ጥንታውያን ቋንቋዎች ይሰጡባቸዋል። ምርምር እንደሚያስፈልጋቸው በሚታመንባቸው ጉዳዮች ላይ ጥናቶችም ይሠሩባቸዋል።
ቤተ ክርስቲያን አብነቱን እንደያዘች ሥነ መለኮት ት/ቤቶች እንደሚያስፈልጓት አምና ሁለቱንም ይዛለች። ይህ የሌሎች ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት እውነታም ነው።
ለወደፊቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ተግዳሮት ከሚፈጥሩ ነገሮች አንዱ የሁለቱ ት/ቤቶች መስተጋብር ነው። መፈራረጅ እና መቆሳሰል ብዙ ጉዳት አድርሶ የግለሰቦች መጣያ እና መጠላለፊያ ከመሆኑ በፊት በትልቁ ምሥል ላይ በቂ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል። በጉዳዮች ላይ በቂ ውይይት ሳይደረግ ሲቀር ጉዳይ ግለሰባዊ መነቃቀፊያ ወደ መሆን ይወርዳልና።
ጤናማው የአካሄድ መሥመር የቱ ነው? በአብነቱ የማናገኛቸውን ነገር ግን በዘመኑ ለሚነሡ ጥያቄዎች አስፈላጊ የሆኑ የአበው ድርሳናት እና የታሪክ ምንጮች እንዴት እንጠቀም? ተቃርኖ የሚመስሉ ነገሮች ሲገጥሙ እንዴት እንፍታ? የሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሊቃውንት መጻሕፍት ስናነብ የሚያስፈልገው ጥንቃቄ ምንድር ነው? የሚሉት እና መሰል ጉዳዮች ሳይረፍድ እና ችግሮች ሳይገነግኑ ለውይይት መቅረብ ይኖርባቸዋል።
የእኔን አጭር እይታ ላስቀምጥ። በሥነ መለኮት ት/ቤቶች የሚማሩ ሰዎች የአብነቱን ትምህርት ትልቅ ዋጋ ሰጥተው ማጥናት ይገባቸዋል፤ የአብነቱን ት/ት ዜማውን ለመማር ቢከብድ እንኳ ይዘቱን (መልእክቱን) አክብሮ ማወቅ እና መረዳት ግዴታ ይመስለኛል። በአብነት ት/ቤት ያሉ ሊቃውንት ደግሞ የሥነ መለኮት ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ተጨማሪ እውቀቶች እና ምንጮች ቢያገኙ የአብነቱን የበለጠ በጥልቀት ለመረዳት እና ለማብራራት ይረዳቸዋል። ነገሮችን ከታሪካዊ ዳራቸው ለመረዳት እና ታሪካዊ ዓውዳቸውን ለመረዳት የሥነ መለኮት ምንጮች ጠቃሚ ናቸው። በመሆኑም ሳይጠራጠሩት በበጎ ኅሊና ሊያዩት፣ እድሉ ከተገኘም ሊማሩት ይገባል። በተለይ ደግሞ የአብነት መሠረት ያላቸው ሊቃውንት የሥነ መለኮት ት/ቤቶች ውስጥ መኖራቸው ሁለቱንም በአግባቡ የመያዝ ሕያው ምስክሮች ስለሚሆኑ በእጅጉ ጠቃሚ ይሆናል። በዚህ መንገድ ለቤተ ክርስቲያን የሠመረ አገልግሎት ትልቅ መመጋገብ ሊኖራቸው ይችላል።
✍️ዲያቆን በረከት አዝመራው
አመ ፳ወ፯ ለጥር – በእንተ ሰማእታት ዘምድረ ሻሸመኔ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አመ ፳ወ፯ ለጥር በዛቲ ዕለት ውኅዘ ደመ ሰማእታት በምድረ ሻሸመኔ በመዋዕሊሁ ለዐቢይ አህመድ ወውእቱ ንጉሥ ኮነ ዘያሌዕል ርእሶ እምኩሉ ሰብእ ወይብል አንሰ ባህቲትየ አአምሮ ለኲሉ ነገር ወበመዋዕሊሁ ኮነ አቢይ ስደት በቤተክርስቲያን ወተቀትሉ ምእመናን ወምእመናት ዘየአምኑ በክርስቶስ ዘእንበለ ሙስና ዳእሙ በእንተ ኃይማኖቶሙ
ወተንስኡ ፫ቱ ጳጳሳት ተላውያነ ንጉሥ እንዘ ይብሉ ንህነሰአ ኢንትዌከፍአ ትእዛዘ ቅዱስ ሲኖዶስ ወንሠይምአ ኤጲስ ቆጶሳተአ እምነገደ ዚአነአ ወእሙንቱሰአ እምድኅረ ተሠይሙአ ይረድኡነአ ከመ ናማስናአ ለቤተክርስቲያንአ ወንሬሲአ ስዒረ ሲኖዶስአ ወንጉሥሰአ ሀሎአ ምስሌነአ መኑአ ይከልአነአ ወዘንተ ብሂሎሙ ኃረዩ መነኮሳተ ዘይትኤመሩ በብዙኅ ነውር ወቦ እምኔሆሙ ዘአውሰበ ብእሲተ ወቦ እምኔሆሙ ዘኢየአምን በክርስቶስ ወቦ እምኔሆሙ ሰራቂ ወቦ እማእከሎሙ ዘማዊ ወሰራቂ ወተማከሩ ምስለ መሳፍንተ ሀገር ወሤምዎሙ በህቡዕ ዘእንበለ ሥርዓት ወህግ ወወሀብዎሙ አስማተ ቅዱሳን ክቡዳተ ዘኢይደሉ ለግብሮሙ
ወሶበ ሰምዑ ሊቃነ ጳጳሳት ተጋብዑ ፍጡነ በጉባዔ ሲኖዶስ ወአውገዝዎሙ ለእልክቱ አማሳንያነ ሥርአት ወህግ ወሶበ ሰምዐ ንጉስ ተምአ ጥቀ ላእለ ቤተክርስቲያን ወላእለ አበው ወተናገረ እንዘ ይብል አነ ብዙኃ ሠናየ ነገረ ገበርኩ ለቤተክርስቲያን ወበእንተዝ ስምዑኒ ወተዐረቁ ፍጡነ ምስለ ሠዐርያነ ሲኖዶስ ወተወከፍዎሙ ለዘተሠይሙ ወሶበ ሰምዑ ዓበው ጳጳሳት ብህሉ ከመዝ ንህነሰ ኢተፃባእነ ምስለ አሀዱ ሰብእ ባህቱ ሐሎነ ህግ ወሥርአት ዘተወከፈሰናሁ እምሐዋርያት ወእምሊቃውንት ወለእመ ተመይጡሰ በህግ ወበሥርአት ንትዌከፎሙ በንስሀ ወበትእዛዘ ንጉሥሠ ኢንገብሮ ለዝንቱ ዳእሙ በትእዛዘ አምላክነ።
ወንጉሥሠ ተቆጥአ ወይቤሎሙ ለመኳንንቲሁ ኢትግበሩ ምንተኒ ግብረ ሶበ ይመጽእ ሀውክ ላዕለ ቤተክርስቲያን ወእምድህረ ዝንቱ ዕለት በዝኀ መከራ ላዕለ ቤተክርስቲያን ወእሙንቱ ጳጳሳተ ሐሰት ገብሩ ብዙኃ ኃጢአተ ወሞቅህዎ ለአባ እስጢፋኖስ ወሰደድዎ እመንበሩ ዘትሠመይ ጅማ ወለአባ ያሬድኒ ከማሁ ሰደድዎ እመንበሩ ዘስማ አርሲ ወቦኡ በኃይል ምስለ መንገኒቅ ኃበ መንበረ ጵጵስናሆሙ ለአባ ናትናኤል ወለአባ ሩፋኤል ወመዝበሩ ብዙኃ ንዋያተ ቅዱሳተ ዘቤተክርስቲያን ወወኃብዎሙ ለሐራ ንጉሥ ወሖሩ ኃበ ሻሸመኔ ከመ ያብዕዎ ለአሀዱ ጳጳሰ ሐሰት ዘስሙ ገብረ እግዚአብሔር ወግብሩ እኩይ ወሰብአ ሻሸመኔሰ ከልሁ እንዘ ይብሉ አሐቲ ቤተክርስቲያን አሐዱ ሲኖዶስ ወአሐዱ መንበር ወመጽአ ተአጊቶ በብዙኅ ሰራዊት ኃበ ሻሸመኔ ወሖረ ሐበ ቤተክርስቲያኑ ለቅዱስ ሚካኤል ወብዙኃን ሰብእ ሐለዉ እንዘ ይፄልዩ ወይዜምሩ ወሶበ በጽሐ ዝንቱ እኩይ ኃበ ከኒሳ ወከልእዎ ምእመናን ከመ ኢይባእ እንዘ ይጠቅዑ መጥቅዐ ወሶቤሀ ተምዑ ወዐልያነ ንጉሥ ላእለ ህዝበ ክርስቲያን ወቀተልዎሙ ለምእመናን በመንገኒቅ ወብዙኃን ኮኑ ሰማእተ ወኃበ ቤተክርስቲያኑ ለተክለሃይማኖትኒ ከማሁ ቀተልዎሙ ወአቁሰልዎሙ ለክርስቲያን ወሰማእተ ኮኑ በእንተ ጽድቅ ወበእንተ ክርስቶስ በረከቶሙ ተሀሉ ምስሌነ ወኪያነሂ ይምሀረነ በፀሎቶሙ ለሰማዕታት ወየሀብ ሰላመ ለቤተክርስቲያን ለዓለመ ዓለም አሜን
ሰላም ሰላም ለሰማዕታት ኩሎሙ
በእንተ ከኒሳ ቅድስት እለ ከአዉ ደሞሙ
ሶበ መጽአ ሐሳዊ ሀበ ሻሸመኔ ምድሮሙ
ኢፈርህዎ ለመንገኒቅ ወተወክፍዎ በፍጽሞሙ
እንዘ ይኄልዩ ገነተ ርስቶሙ
በመሪጌታ Birhanu Tekleyared የተዘጋጀ
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ጥር 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1. ቅዱስ ኄኖክ ነቢይ (ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረገበት)
2. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)
3. ቅዱስ አባ ቢፋሞን ሰማዕት
4. ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕት
5. ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት (ከሰባቱ ሊቃናት አንዱ)
ወርኀዊ በዓላት
1. መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ
2. አቡነ መባዐ ጽዮን
3. አባ መቃርስ ርዕሰ መነኮሳት
4. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
5. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
6. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
©ጴጥሮስ አሸናፉ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አመ ፳ወ፯ ለጥር በዛቲ ዕለት ውኅዘ ደመ ሰማእታት በምድረ ሻሸመኔ በመዋዕሊሁ ለዐቢይ አህመድ ወውእቱ ንጉሥ ኮነ ዘያሌዕል ርእሶ እምኩሉ ሰብእ ወይብል አንሰ ባህቲትየ አአምሮ ለኲሉ ነገር ወበመዋዕሊሁ ኮነ አቢይ ስደት በቤተክርስቲያን ወተቀትሉ ምእመናን ወምእመናት ዘየአምኑ በክርስቶስ ዘእንበለ ሙስና ዳእሙ በእንተ ኃይማኖቶሙ
ወተንስኡ ፫ቱ ጳጳሳት ተላውያነ ንጉሥ እንዘ ይብሉ ንህነሰአ ኢንትዌከፍአ ትእዛዘ ቅዱስ ሲኖዶስ ወንሠይምአ ኤጲስ ቆጶሳተአ እምነገደ ዚአነአ ወእሙንቱሰአ እምድኅረ ተሠይሙአ ይረድኡነአ ከመ ናማስናአ ለቤተክርስቲያንአ ወንሬሲአ ስዒረ ሲኖዶስአ ወንጉሥሰአ ሀሎአ ምስሌነአ መኑአ ይከልአነአ ወዘንተ ብሂሎሙ ኃረዩ መነኮሳተ ዘይትኤመሩ በብዙኅ ነውር ወቦ እምኔሆሙ ዘአውሰበ ብእሲተ ወቦ እምኔሆሙ ዘኢየአምን በክርስቶስ ወቦ እምኔሆሙ ሰራቂ ወቦ እማእከሎሙ ዘማዊ ወሰራቂ ወተማከሩ ምስለ መሳፍንተ ሀገር ወሤምዎሙ በህቡዕ ዘእንበለ ሥርዓት ወህግ ወወሀብዎሙ አስማተ ቅዱሳን ክቡዳተ ዘኢይደሉ ለግብሮሙ
ወሶበ ሰምዑ ሊቃነ ጳጳሳት ተጋብዑ ፍጡነ በጉባዔ ሲኖዶስ ወአውገዝዎሙ ለእልክቱ አማሳንያነ ሥርአት ወህግ ወሶበ ሰምዐ ንጉስ ተምአ ጥቀ ላእለ ቤተክርስቲያን ወላእለ አበው ወተናገረ እንዘ ይብል አነ ብዙኃ ሠናየ ነገረ ገበርኩ ለቤተክርስቲያን ወበእንተዝ ስምዑኒ ወተዐረቁ ፍጡነ ምስለ ሠዐርያነ ሲኖዶስ ወተወከፍዎሙ ለዘተሠይሙ ወሶበ ሰምዑ ዓበው ጳጳሳት ብህሉ ከመዝ ንህነሰ ኢተፃባእነ ምስለ አሀዱ ሰብእ ባህቱ ሐሎነ ህግ ወሥርአት ዘተወከፈሰናሁ እምሐዋርያት ወእምሊቃውንት ወለእመ ተመይጡሰ በህግ ወበሥርአት ንትዌከፎሙ በንስሀ ወበትእዛዘ ንጉሥሠ ኢንገብሮ ለዝንቱ ዳእሙ በትእዛዘ አምላክነ።
ወንጉሥሠ ተቆጥአ ወይቤሎሙ ለመኳንንቲሁ ኢትግበሩ ምንተኒ ግብረ ሶበ ይመጽእ ሀውክ ላዕለ ቤተክርስቲያን ወእምድህረ ዝንቱ ዕለት በዝኀ መከራ ላዕለ ቤተክርስቲያን ወእሙንቱ ጳጳሳተ ሐሰት ገብሩ ብዙኃ ኃጢአተ ወሞቅህዎ ለአባ እስጢፋኖስ ወሰደድዎ እመንበሩ ዘትሠመይ ጅማ ወለአባ ያሬድኒ ከማሁ ሰደድዎ እመንበሩ ዘስማ አርሲ ወቦኡ በኃይል ምስለ መንገኒቅ ኃበ መንበረ ጵጵስናሆሙ ለአባ ናትናኤል ወለአባ ሩፋኤል ወመዝበሩ ብዙኃ ንዋያተ ቅዱሳተ ዘቤተክርስቲያን ወወኃብዎሙ ለሐራ ንጉሥ ወሖሩ ኃበ ሻሸመኔ ከመ ያብዕዎ ለአሀዱ ጳጳሰ ሐሰት ዘስሙ ገብረ እግዚአብሔር ወግብሩ እኩይ ወሰብአ ሻሸመኔሰ ከልሁ እንዘ ይብሉ አሐቲ ቤተክርስቲያን አሐዱ ሲኖዶስ ወአሐዱ መንበር ወመጽአ ተአጊቶ በብዙኅ ሰራዊት ኃበ ሻሸመኔ ወሖረ ሐበ ቤተክርስቲያኑ ለቅዱስ ሚካኤል ወብዙኃን ሰብእ ሐለዉ እንዘ ይፄልዩ ወይዜምሩ ወሶበ በጽሐ ዝንቱ እኩይ ኃበ ከኒሳ ወከልእዎ ምእመናን ከመ ኢይባእ እንዘ ይጠቅዑ መጥቅዐ ወሶቤሀ ተምዑ ወዐልያነ ንጉሥ ላእለ ህዝበ ክርስቲያን ወቀተልዎሙ ለምእመናን በመንገኒቅ ወብዙኃን ኮኑ ሰማእተ ወኃበ ቤተክርስቲያኑ ለተክለሃይማኖትኒ ከማሁ ቀተልዎሙ ወአቁሰልዎሙ ለክርስቲያን ወሰማእተ ኮኑ በእንተ ጽድቅ ወበእንተ ክርስቶስ በረከቶሙ ተሀሉ ምስሌነ ወኪያነሂ ይምሀረነ በፀሎቶሙ ለሰማዕታት ወየሀብ ሰላመ ለቤተክርስቲያን ለዓለመ ዓለም አሜን
ሰላም ሰላም ለሰማዕታት ኩሎሙ
በእንተ ከኒሳ ቅድስት እለ ከአዉ ደሞሙ
ሶበ መጽአ ሐሳዊ ሀበ ሻሸመኔ ምድሮሙ
ኢፈርህዎ ለመንገኒቅ ወተወክፍዎ በፍጽሞሙ
እንዘ ይኄልዩ ገነተ ርስቶሙ
በመሪጌታ Birhanu Tekleyared የተዘጋጀ
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ጥር 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1. ቅዱስ ኄኖክ ነቢይ (ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረገበት)
2. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)
3. ቅዱስ አባ ቢፋሞን ሰማዕት
4. ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕት
5. ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት (ከሰባቱ ሊቃናት አንዱ)
ወርኀዊ በዓላት
1. መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ
2. አቡነ መባዐ ጽዮን
3. አባ መቃርስ ርዕሰ መነኮሳት
4. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
5. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
6. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
©ጴጥሮስ አሸናፉ
❤1
የተሰበረ ጽዋዕ
እዚኽ ፎቶ ውስጥ በአካል የማውቀው ዘማርያምን ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ግን በማኅበራዊው ሚዲያ መልስ ሲሰጡና ሲጠይቁ አያቸዋለሁ እንጂ ፊት ለፊት ተገናኝተን አናውቅም፡፡በወንድሞቻችን ፊት ፕሮቴስታንት ሰባክያን ምላሳቸውን ሲተሳሰር ብዙ ጊዜ አይቻለኹ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ "ከኦርቶዶክስ ወንድሞች ጋር እንዳትከራከሩ" የሚል አዋጅ ሲያውጁ ሰምቻለኹ ጰንጤዎቹ፡፡
በአጭሩ፥ እኒኽ ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን መላእክትና ሰዎችን ታመልካለች የሚለውን ፕሮቴስታንታዊ የድር ምሽግ ሲበጣጥሱ ተመልክቻለኹ፡፡ ከዐይን ያውጣችኹ አልላችኹም፡፡ ዐይንም ጆሮም ውስጥ ናችኹና፡፡
ጽንዑ ወኀይሉ፡፡ ለማለት ነው አመጣጤ፡፡
ከእኒኽ ወንድሞች መኻል አንዱ ወይም ኹሉም ሊሳሳቱ የሚችሉ ናቸው፡፡ የቀለም ሠረገላ የማያሰናክለው የለምና፡፡ ደግሞም እኔ እንኳ የሰማኋቸው የሚታረሙ ስሕተቶች አሉ፡፡የሚታረም ነገር ተገኘ ማለት ግን፥ ሙሉ እርሻው አረም ነውና አያስፈልግም የሚል ቧልት መናገር ግን ቅንነትና ወንድማዊ ፍቅር ይጎድለዋል፡፡
በአንድ ወቅት፦
አንድ እጅግ የተከበሩ ሊቅ ከአንዲት ሴት ጋር ድቀት አገኛቸው፡፡ እኒኽን ሊቅ ብዙ ሰው ያውቃቸዋል፡፡ በዚኽኛው ታሪክ ግን ሰፊው ሕዝብ ስለማያውቃቸው ስማቸውን ልለፈው፡፡ ይኽን ድቀታቸውን የሰማ ደብተራ አንድ ቀን ማሕሌት ውስጥ አገኛቸው ሊቁን፡፡"ደግሞ አንተ እዚኽ ምን ልታደርግ ገባኽ?"
ሲል በፍና ተሣልቆ አፌዘባቸው፡፡ እርሳቸውም "እኔኮ የተሰበርኩ ጽዋዕ ነኝ" ብለው አንጀት የሚበላ መልስ ሰጡት፡፡
የተሰበረ ጽዋዕ ሰባራ ስለኾነ አይጣልም፡፡ንዋይ ቅዱስ ነውና በክብር ከዕቃ ቤት ይቀመጣል እንጂ፡፡
እንደዚያ ደብተራ ለቤተክርስቲያን የቀናን እየመሰለን ጥቂት ሸራፋ ያገኘንባቸው ጽዋወችን ኹሉ አውጥተን እንጣል ማለት እጅግ የከፋ በደል ነው፡፡ክርስቶሳዊውን መንገድ የረሳ ነውና፡፡ "ድኅረ ተሰብረ አጽንዖ ለሰብእናነ ልሕኵት፥ ለብሓዊ ክርስቶስ በማየ ሐዲስ ጥምቀት" የምትል ድንቅ የንጉሥ ጉባኤ ቃና አለች፡፡ ግርድፍ ትርጉሟ፦ ገላ'ችን ከተሰበረ በኋላ ሸክላ ሠሪው ክርስቶስ በአዲስ የውኀ ጥምቀት እንደገና ሠራው፡፡ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ከጌታዋ የተማረችው የተሰበረን መጠገን ነው፡፡
ችግሩ፥ መጠገን እንደመስበር ቀላል አይደለም፡፡ ለመጠገን ዕውቀትና ቅንነት ያስፈልጋል፡፡ ለመስበር ግን ኦርቶዶክሳዊ የዘብነት ቀለም የተቀባች ምላስ በቂ ናት፡፡
ወንድሞች በጎ ሲሠሩ እናበርታ፡፡ሲስቱ እንክርዳድ ከስንዴ እየለየን በፍቅር እናርም፡፡አልታረምም የሚል ካለ ደግሞ የቤክርስቲያን ቱንቢ ያርመዋል፡፡እንደ ግለሰብእ እኔ ነኝ ቱንቢው ማለት ግን የስሕተት ስሕተት ነው፡፡
በየሚዲያው ሌሎች ጥሩ ወንድሞችም አሉ፡፡ ነገር ግን በልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን አገልግሎት የተገለጡ ናቸውና ተውኳቸው፡፡
ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው እንደጻፉት
እዚኽ ፎቶ ውስጥ በአካል የማውቀው ዘማርያምን ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ግን በማኅበራዊው ሚዲያ መልስ ሲሰጡና ሲጠይቁ አያቸዋለሁ እንጂ ፊት ለፊት ተገናኝተን አናውቅም፡፡በወንድሞቻችን ፊት ፕሮቴስታንት ሰባክያን ምላሳቸውን ሲተሳሰር ብዙ ጊዜ አይቻለኹ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ "ከኦርቶዶክስ ወንድሞች ጋር እንዳትከራከሩ" የሚል አዋጅ ሲያውጁ ሰምቻለኹ ጰንጤዎቹ፡፡
በአጭሩ፥ እኒኽ ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን መላእክትና ሰዎችን ታመልካለች የሚለውን ፕሮቴስታንታዊ የድር ምሽግ ሲበጣጥሱ ተመልክቻለኹ፡፡ ከዐይን ያውጣችኹ አልላችኹም፡፡ ዐይንም ጆሮም ውስጥ ናችኹና፡፡
ጽንዑ ወኀይሉ፡፡ ለማለት ነው አመጣጤ፡፡
ከእኒኽ ወንድሞች መኻል አንዱ ወይም ኹሉም ሊሳሳቱ የሚችሉ ናቸው፡፡ የቀለም ሠረገላ የማያሰናክለው የለምና፡፡ ደግሞም እኔ እንኳ የሰማኋቸው የሚታረሙ ስሕተቶች አሉ፡፡የሚታረም ነገር ተገኘ ማለት ግን፥ ሙሉ እርሻው አረም ነውና አያስፈልግም የሚል ቧልት መናገር ግን ቅንነትና ወንድማዊ ፍቅር ይጎድለዋል፡፡
በአንድ ወቅት፦
አንድ እጅግ የተከበሩ ሊቅ ከአንዲት ሴት ጋር ድቀት አገኛቸው፡፡ እኒኽን ሊቅ ብዙ ሰው ያውቃቸዋል፡፡ በዚኽኛው ታሪክ ግን ሰፊው ሕዝብ ስለማያውቃቸው ስማቸውን ልለፈው፡፡ ይኽን ድቀታቸውን የሰማ ደብተራ አንድ ቀን ማሕሌት ውስጥ አገኛቸው ሊቁን፡፡"ደግሞ አንተ እዚኽ ምን ልታደርግ ገባኽ?"
ሲል በፍና ተሣልቆ አፌዘባቸው፡፡ እርሳቸውም "እኔኮ የተሰበርኩ ጽዋዕ ነኝ" ብለው አንጀት የሚበላ መልስ ሰጡት፡፡
የተሰበረ ጽዋዕ ሰባራ ስለኾነ አይጣልም፡፡ንዋይ ቅዱስ ነውና በክብር ከዕቃ ቤት ይቀመጣል እንጂ፡፡
እንደዚያ ደብተራ ለቤተክርስቲያን የቀናን እየመሰለን ጥቂት ሸራፋ ያገኘንባቸው ጽዋወችን ኹሉ አውጥተን እንጣል ማለት እጅግ የከፋ በደል ነው፡፡ክርስቶሳዊውን መንገድ የረሳ ነውና፡፡ "ድኅረ ተሰብረ አጽንዖ ለሰብእናነ ልሕኵት፥ ለብሓዊ ክርስቶስ በማየ ሐዲስ ጥምቀት" የምትል ድንቅ የንጉሥ ጉባኤ ቃና አለች፡፡ ግርድፍ ትርጉሟ፦ ገላ'ችን ከተሰበረ በኋላ ሸክላ ሠሪው ክርስቶስ በአዲስ የውኀ ጥምቀት እንደገና ሠራው፡፡ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ከጌታዋ የተማረችው የተሰበረን መጠገን ነው፡፡
ችግሩ፥ መጠገን እንደመስበር ቀላል አይደለም፡፡ ለመጠገን ዕውቀትና ቅንነት ያስፈልጋል፡፡ ለመስበር ግን ኦርቶዶክሳዊ የዘብነት ቀለም የተቀባች ምላስ በቂ ናት፡፡
ወንድሞች በጎ ሲሠሩ እናበርታ፡፡ሲስቱ እንክርዳድ ከስንዴ እየለየን በፍቅር እናርም፡፡አልታረምም የሚል ካለ ደግሞ የቤክርስቲያን ቱንቢ ያርመዋል፡፡እንደ ግለሰብእ እኔ ነኝ ቱንቢው ማለት ግን የስሕተት ስሕተት ነው፡፡
በየሚዲያው ሌሎች ጥሩ ወንድሞችም አሉ፡፡ ነገር ግን በልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን አገልግሎት የተገለጡ ናቸውና ተውኳቸው፡፡
ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው እንደጻፉት
YouTube
⭕የአባቶች ዝምታ እስከመቼ ድረስ ነው❓ የእንዳልካቸው ጉድ ተጋለጠ | የእፎይ ክርክር | የሻሸመኔ ሰማእታት
እኔን ለማገዝ ከፈለጋችሁ እና ከቻላችሁ VPN አብርታችሁ ተመልከቱልኝ
ይህንን ቻናል ለማሳደግ እና እገዛ ለማድረግ ከፈለጋችሁ
የንግድ ባንክ 1000148595918
አቢሲኒያ ባንክ 45326977
ዘመን ባንክ 1551211205309013
የምጠቀምበትን ማይክ ለማወቅ 👉🏿 https://www.youtube.com/watch?v=UfmkIR3Af8I
ሁለተኛ ቻናሌ ለመቀላቀል https://www.youtube.c…
ይህንን ቻናል ለማሳደግ እና እገዛ ለማድረግ ከፈለጋችሁ
የንግድ ባንክ 1000148595918
አቢሲኒያ ባንክ 45326977
ዘመን ባንክ 1551211205309013
የምጠቀምበትን ማይክ ለማወቅ 👉🏿 https://www.youtube.com/watch?v=UfmkIR3Af8I
ሁለተኛ ቻናሌ ለመቀላቀል https://www.youtube.c…
❤1👍1
ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
የተሰበረ ጽዋዕ እዚኽ ፎቶ ውስጥ በአካል የማውቀው ዘማርያምን ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ግን በማኅበራዊው ሚዲያ መልስ ሲሰጡና ሲጠይቁ አያቸዋለሁ እንጂ ፊት ለፊት ተገናኝተን አናውቅም፡፡በወንድሞቻችን ፊት ፕሮቴስታንት ሰባክያን ምላሳቸውን ሲተሳሰር ብዙ ጊዜ አይቻለኹ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ "ከኦርቶዶክስ ወንድሞች ጋር እንዳትከራከሩ" የሚል አዋጅ ሲያውጁ ሰምቻለኹ ጰንጤዎቹ፡፡ በአጭሩ፥ እኒኽ ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ…
እየው ስሙር ሲያሰምረው
ሲሆን ሲሆንማ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ማለት እንደ ደጉ ሳምራዊ ወንበዴዎች በተባሉ አጋንንት ተደብድበው ወድቀው መስማት መልማት ያልቻሉትንም አይቶ ማዘን፣ አዝኖ መቅረብ፣ ቀርቦ ቁስላቸውን ማጠብ፣ ወይንና ዘይት አድርጎ ማሠር፣ ማንሣት መሸከም የእንግዶች ማረፊያ ወደተባለች ቤተ ክርስቲያን አምጥቶ ማዳን ነበረ። አሁን ያለው ግን በግልባጭ ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ማቅረብ ሳይሆን ድካም ያለበትን አውጥቶ ለመጣል መድከም፣ የወደቀ ማንሣት ሳይሆን የሚፍገመገመውን ለመጣል መታገል ነው። ይህም ሆኖ ደግሞ ራሳችን ችለን ያልቆምን ሰዎች የቆምን መስሎን መድከማችን ያሳዝናል። ቅዱስ ጳውሎስ "ማንም የቆመ የመሰለው ቢኖር እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ" ያለውም ትዝም አይለንም። እግዚአብሔር ልቡና ይስጠን።
ለሁሉም ስሙር የሆነ አሳብ ነውና ያስምርልን።
✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
ሲሆን ሲሆንማ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ማለት እንደ ደጉ ሳምራዊ ወንበዴዎች በተባሉ አጋንንት ተደብድበው ወድቀው መስማት መልማት ያልቻሉትንም አይቶ ማዘን፣ አዝኖ መቅረብ፣ ቀርቦ ቁስላቸውን ማጠብ፣ ወይንና ዘይት አድርጎ ማሠር፣ ማንሣት መሸከም የእንግዶች ማረፊያ ወደተባለች ቤተ ክርስቲያን አምጥቶ ማዳን ነበረ። አሁን ያለው ግን በግልባጭ ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ማቅረብ ሳይሆን ድካም ያለበትን አውጥቶ ለመጣል መድከም፣ የወደቀ ማንሣት ሳይሆን የሚፍገመገመውን ለመጣል መታገል ነው። ይህም ሆኖ ደግሞ ራሳችን ችለን ያልቆምን ሰዎች የቆምን መስሎን መድከማችን ያሳዝናል። ቅዱስ ጳውሎስ "ማንም የቆመ የመሰለው ቢኖር እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ" ያለውም ትዝም አይለንም። እግዚአብሔር ልቡና ይስጠን።
ለሁሉም ስሙር የሆነ አሳብ ነውና ያስምርልን።
✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
👍9🙏3❤1
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ
ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው፡፡
ጥር 29 ቀን 2017ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባዔ፡-
‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)
ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤
• የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !
እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን፤
እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው፤
በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት
ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤
ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤
እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን፤
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ጥር ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ፎቶ መልአከ ሰላም አባ ኪሮስ ወልደአብ
ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው፡፡
ጥር 29 ቀን 2017ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባዔ፡-
‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)
ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤
• የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !
እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን፤
እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው፤
በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት
ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤
ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤
እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን፤
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ጥር ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ፎቶ መልአከ ሰላም አባ ኪሮስ ወልደአብ
❤2👍2🙏1
ስለ ገድላት ማስተዋል የሚሹ ጉዳዮች
--
#አስፈላጊነታቸው፡- ለድርድር አይቀርብም፡፡ የክርስትና ሕይወት በሞት አይቋረጥም ለሚለው አቋማችን ምስክሮች ናቸው፡፡ በአስፈላጊነታቸው ላይ የሚሰጥ የማርያም መንገድ የለም፡፡ ገድላት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተቀደሱ የአገልግሎትና የጸሎት መጻሕፍት መካከል ናቸው፡፡
#ይዘታቸው፡- የገድልት ይዘት ‹‹ገድል›› ነው፡፡ በጠባዩ የሃይማኖት መግለጫ፣ የታሪክ ሰነድ፣ ግለታሪክ፣ የሕይወት ታሪክ፣ ቀኖናዊ መጽሐፍ (መጽሐፍ ቅዱስ)፣ ወዘተ. አይደለም፡፡ ገድል ነው! ገድል አንድ የቤተ ክርስቲያን የሥነ ጽሑፍ ክፍል ነው፡፡ መነበብም ሆነ መመዘን ያለበት፣ መቃናትና መታረምም ያለበት፣ መጠናትም ያለበት በዚያ መንገድና ዐውድ ነው፡፡
#ፈራጁን_ጠርጥሩ፡- ገድላት ከሥነ ጽሑፍና ከቅጂ አንጻር ውጫዊ የሆነ ጥናት በፊሊዮሎጂ ይጠናሉ፡፡ በነገ መለኮት ኮሌጆች ግን የሚገባውን ያህል እየተጠኑ አይመስለኝም፡፡ በጉባኤ ቤት ውስን ድርሳናት እንደየአጥቢያው በተማሪው ይነበባሉ፡፡ ገድል ሕይወት በተግባር የተተረጐመበትን ታሪክ ስለያዘ እንደ ገቢራዊ ማሳያ ይጠቀሳል፡፡ መጥቀስና ማጥናት ተቀራራቢ አይደሉም፡፡ ዳኝነት ለመስጠት አያበቁም፡፡ ስለዚህ ገድላት ላይ ከውስጥም ቢሆን የሚሰጡ አስተያየቶች በተገቢው ንባብና ጥናት መመርኮዛቸው ላይ ጥርጣሬ አለን፡፡ ትልልቆቹ የሀገራችን የጥናት ሰዎች እነ ፕ/ር ጌታቸው፣ ፕ/ር ታደሰ፣ ከውጪም ስቴፈን ካፕላንና የመሳሰሉ አጥኚዎች ገድላትን በስፋት አጥንተዋል፡ ጥናታቸው ግን በሃይማኖት ዐይን አይደለም፡፡ በታሪክና በሥነ ድርሳን መነጽር ነው፡፡ በእነሱ መነጽር ገድላትን እንዲህ ናቸው ማለት ሃይማኖትን በታሪክና በሥነ ድርሳን ሕግጋት መዳኘት ይሆናል፡፡ በአጭሩ ገድላት ተገቢውን ኦርቶዶክሳዊ የጥናት ዐይን ይፈልጋሉ፡፡ በዚህ ረገድ ቀሲ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ (የነቅዐ መጻሕፍት ደራሲ) ደስ ብሎኝ እጠቅሳቸዋለሁ፡፡ የፕ/ር ጌታቸው ‹‹ስለግዕዝ ሥነ ጽሑፍ የተሰበሰቡ አንዳንድ ማስታወሻዎች›› የተሻለ ሃይማኖታዊ መነጽር አለበት (‹‹ከግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ጋራ ብዙ አፍታ ቆይታ›› ከሚለው በተለየ)፡፡
ለሰማዕያንና አንባብያን ያለን ምክር፡- አብዛኛው የውስጥም ሆነ የውጭ ተናጋሪ ስለገድላት ሲናገር ንባቡን ጠርጥሩ! ግምቱን ነው ወይስ ንባቡን? ቁንፅል ዕውቀቱን ነው ወይስ ጥናቱን? ሥራዬ ብሎ ውሎበታል አልዋለበትም? የሚለውን ጠርጥሩ! ብዙ ፈትነን ያረጋገጥነው ምክንያታዊ ጥርጣሬ ስለሆነ! የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ ማስመስከር ወይም የሥነ መለኮት ምሩቅ መሆን ስለገድላት በሥልጣን ለመናገር መብት እንደሚሰጥ ተደርጎ መታመኑ መበረታታት ያለበት ተግባር ሆኖ አይታየንም፡፡
#የመሥዋዕቱ_ማሳረጊያ፡- የቤተ ክርስቲያን ዋነኛ የአምልኮ መፈጸሚያ ቅዳሴው ነው፡፡ በቅዳሴ ውስጥ የሚነበቡት መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ የተመረጡ 4 ምንባባት (ከመልእክታት፣ ከሐዋ.ሥራና ከወንጌል) ብቻ ናቸው፡፡ ገድል በቅዳሴ አይነበብም (የቅዳሴውን አንድምታ ትርጓሜ ገጽ 96 ማየት ይቻላል)፡፡ የመሥዋዕት ማሳረጊያው ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡ ገድላት ከቅዳሴ በኋላ ወይም በፊት ለማጽኛና መጽናኛ ይነበባሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለቅዱስ ወንጌል በምትሰጠው ቦታ ላይ ብዥታ የለም፡፡
#ገድላትና_ድርሳናት_ለሃይማኖት_ማስረጃነት፡-
(1)ገድላትና ድርሳናት በቤተ ክርስቲያን ለቅዱሳት መጻሕፍት መተርጐሚያና ማብራሪያነት ይጠቀሳሉ፡፡ በነገረ ሃይማኖት ረገድም በቀደሙት አበው ዘንድ ገድላትና ድርሳናት ለሃይማኖት ማስረጃነት ሲጠቀሱ እናያለን (ሃይ.አበ.ዘባስልዮስ ም.96፡42 እና ዘዮሐንስ 114፡20)፡፡ በቦሩ ሜዳ ጉባኤ ሦስት ልደቶች ከደብረ ብርሃኑ ተአምረ ማርያም መጥቀሳቸው የተነቀፈበት ዐውድ መለጠጥ የለበትም፡፡
(2)መጀመሪያ ወደ ምንጭና ሥልጣን ወዳለው ንባብ ክርክር የተሔደው ያላስማማ ኃይለ ቃል ስላለ ነው፤ የተአምሩ አስፈላጊነት ላይ ክርክር የለም፤ ቦሩ ሜዳ ክርክርና ጥያቄ ሲነሣ በበላይነት መምራት ያለበትና ልንከተለው የሚገባው ዋነኛው የበላይ ገዢ የክርስትና ሕግ መጽሐፍ ቅዱስ ነው በሚል የተነገረበት ነው፤ ጥያቄ በማይነሣባቸውና በትርጉም ባላከራከሩ ነጥቦች መጠቀሱ ይቀጥላል፤ ማረም ቢያስፈልግ የደብረ ብርሃኑ ተአምረ ማርያም የሦስት ልደቶችን በመደገፍ የተጻፈው ክፍል ተለይቶ ይታረማል እንደማለት ነው፡፡ እናስተውል! ገድል ቀኖናዊ መጽሐፍ (Canonical Book) አይደለም! አዳዲስ ተአምራት ሲፈጸሙ ተጨምረው ይጻፋሉ፤ የተፋለሱ ምንባባት ይቃናሉ፡፡
(3)የቦሩ ሜዳ ጉባኤ ውሳኔ የቤተ ክርስቲያን የዶግማ መግለጫዎችን በምንረዳበት ጊዜ ስለሚኖረን የምንጮች ተዋረድ(Hierarchy of sources)ና ምንጮች ሲያከራክሩ በስተመጨረሻ በየትኛው ፍጹማዊ መስፈሪያ እንደሚፀኑ (በሕግ validity requirement እንደሚባለው) በሚያስታውቅ ዐውድ የተነገረ መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡ በጉባኤው ‹‹ሁለት ልደት›› ተብሎ የተወሰነው በዋናነት በሃይማኖተ አበው ምንባባት ነው፤ ሃይማኖተ አበው ቁጥሩ ከድርሳን ነው፡፡ እዚህ ላይ ድርሳን የሚለው የግእዝ ቃል የመጽሐፍ ማብራሪያን (Homily) እና የመላእክት/ቅዱሳን ድርሳንን (Encomium) ስለሚጠቅልል ዐውዱ እንዳያሳስተን፡፡
--
የመልእክቱ ጭብጥ፡- በገድላት ጉዳይ የማርያም መንገድ ለመስጠት አንፋጠን!
ሦስት ነገሮች ይቅደሙ፡-
(1)የገድላቱን አስፈላጊነት አምኖ መነሣት፣
(2)በሃይማኖታዊ መነጽር ማጥናት፣
(3)ማቅናት፣ የቀናውን ማጽናት፡፡
--
በቀናች ሃይማኖት አጽንቶ ከቅዱሳኑ ይደምረን! አሜን!!!
✍️ደብተራ በአማን ነጸረ እንደጻፉት
--
#አስፈላጊነታቸው፡- ለድርድር አይቀርብም፡፡ የክርስትና ሕይወት በሞት አይቋረጥም ለሚለው አቋማችን ምስክሮች ናቸው፡፡ በአስፈላጊነታቸው ላይ የሚሰጥ የማርያም መንገድ የለም፡፡ ገድላት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተቀደሱ የአገልግሎትና የጸሎት መጻሕፍት መካከል ናቸው፡፡
#ይዘታቸው፡- የገድልት ይዘት ‹‹ገድል›› ነው፡፡ በጠባዩ የሃይማኖት መግለጫ፣ የታሪክ ሰነድ፣ ግለታሪክ፣ የሕይወት ታሪክ፣ ቀኖናዊ መጽሐፍ (መጽሐፍ ቅዱስ)፣ ወዘተ. አይደለም፡፡ ገድል ነው! ገድል አንድ የቤተ ክርስቲያን የሥነ ጽሑፍ ክፍል ነው፡፡ መነበብም ሆነ መመዘን ያለበት፣ መቃናትና መታረምም ያለበት፣ መጠናትም ያለበት በዚያ መንገድና ዐውድ ነው፡፡
#ፈራጁን_ጠርጥሩ፡- ገድላት ከሥነ ጽሑፍና ከቅጂ አንጻር ውጫዊ የሆነ ጥናት በፊሊዮሎጂ ይጠናሉ፡፡ በነገ መለኮት ኮሌጆች ግን የሚገባውን ያህል እየተጠኑ አይመስለኝም፡፡ በጉባኤ ቤት ውስን ድርሳናት እንደየአጥቢያው በተማሪው ይነበባሉ፡፡ ገድል ሕይወት በተግባር የተተረጐመበትን ታሪክ ስለያዘ እንደ ገቢራዊ ማሳያ ይጠቀሳል፡፡ መጥቀስና ማጥናት ተቀራራቢ አይደሉም፡፡ ዳኝነት ለመስጠት አያበቁም፡፡ ስለዚህ ገድላት ላይ ከውስጥም ቢሆን የሚሰጡ አስተያየቶች በተገቢው ንባብና ጥናት መመርኮዛቸው ላይ ጥርጣሬ አለን፡፡ ትልልቆቹ የሀገራችን የጥናት ሰዎች እነ ፕ/ር ጌታቸው፣ ፕ/ር ታደሰ፣ ከውጪም ስቴፈን ካፕላንና የመሳሰሉ አጥኚዎች ገድላትን በስፋት አጥንተዋል፡ ጥናታቸው ግን በሃይማኖት ዐይን አይደለም፡፡ በታሪክና በሥነ ድርሳን መነጽር ነው፡፡ በእነሱ መነጽር ገድላትን እንዲህ ናቸው ማለት ሃይማኖትን በታሪክና በሥነ ድርሳን ሕግጋት መዳኘት ይሆናል፡፡ በአጭሩ ገድላት ተገቢውን ኦርቶዶክሳዊ የጥናት ዐይን ይፈልጋሉ፡፡ በዚህ ረገድ ቀሲ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ (የነቅዐ መጻሕፍት ደራሲ) ደስ ብሎኝ እጠቅሳቸዋለሁ፡፡ የፕ/ር ጌታቸው ‹‹ስለግዕዝ ሥነ ጽሑፍ የተሰበሰቡ አንዳንድ ማስታወሻዎች›› የተሻለ ሃይማኖታዊ መነጽር አለበት (‹‹ከግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ጋራ ብዙ አፍታ ቆይታ›› ከሚለው በተለየ)፡፡
ለሰማዕያንና አንባብያን ያለን ምክር፡- አብዛኛው የውስጥም ሆነ የውጭ ተናጋሪ ስለገድላት ሲናገር ንባቡን ጠርጥሩ! ግምቱን ነው ወይስ ንባቡን? ቁንፅል ዕውቀቱን ነው ወይስ ጥናቱን? ሥራዬ ብሎ ውሎበታል አልዋለበትም? የሚለውን ጠርጥሩ! ብዙ ፈትነን ያረጋገጥነው ምክንያታዊ ጥርጣሬ ስለሆነ! የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ ማስመስከር ወይም የሥነ መለኮት ምሩቅ መሆን ስለገድላት በሥልጣን ለመናገር መብት እንደሚሰጥ ተደርጎ መታመኑ መበረታታት ያለበት ተግባር ሆኖ አይታየንም፡፡
#የመሥዋዕቱ_ማሳረጊያ፡- የቤተ ክርስቲያን ዋነኛ የአምልኮ መፈጸሚያ ቅዳሴው ነው፡፡ በቅዳሴ ውስጥ የሚነበቡት መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ የተመረጡ 4 ምንባባት (ከመልእክታት፣ ከሐዋ.ሥራና ከወንጌል) ብቻ ናቸው፡፡ ገድል በቅዳሴ አይነበብም (የቅዳሴውን አንድምታ ትርጓሜ ገጽ 96 ማየት ይቻላል)፡፡ የመሥዋዕት ማሳረጊያው ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡ ገድላት ከቅዳሴ በኋላ ወይም በፊት ለማጽኛና መጽናኛ ይነበባሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለቅዱስ ወንጌል በምትሰጠው ቦታ ላይ ብዥታ የለም፡፡
#ገድላትና_ድርሳናት_ለሃይማኖት_ማስረጃነት፡-
(1)ገድላትና ድርሳናት በቤተ ክርስቲያን ለቅዱሳት መጻሕፍት መተርጐሚያና ማብራሪያነት ይጠቀሳሉ፡፡ በነገረ ሃይማኖት ረገድም በቀደሙት አበው ዘንድ ገድላትና ድርሳናት ለሃይማኖት ማስረጃነት ሲጠቀሱ እናያለን (ሃይ.አበ.ዘባስልዮስ ም.96፡42 እና ዘዮሐንስ 114፡20)፡፡ በቦሩ ሜዳ ጉባኤ ሦስት ልደቶች ከደብረ ብርሃኑ ተአምረ ማርያም መጥቀሳቸው የተነቀፈበት ዐውድ መለጠጥ የለበትም፡፡
(2)መጀመሪያ ወደ ምንጭና ሥልጣን ወዳለው ንባብ ክርክር የተሔደው ያላስማማ ኃይለ ቃል ስላለ ነው፤ የተአምሩ አስፈላጊነት ላይ ክርክር የለም፤ ቦሩ ሜዳ ክርክርና ጥያቄ ሲነሣ በበላይነት መምራት ያለበትና ልንከተለው የሚገባው ዋነኛው የበላይ ገዢ የክርስትና ሕግ መጽሐፍ ቅዱስ ነው በሚል የተነገረበት ነው፤ ጥያቄ በማይነሣባቸውና በትርጉም ባላከራከሩ ነጥቦች መጠቀሱ ይቀጥላል፤ ማረም ቢያስፈልግ የደብረ ብርሃኑ ተአምረ ማርያም የሦስት ልደቶችን በመደገፍ የተጻፈው ክፍል ተለይቶ ይታረማል እንደማለት ነው፡፡ እናስተውል! ገድል ቀኖናዊ መጽሐፍ (Canonical Book) አይደለም! አዳዲስ ተአምራት ሲፈጸሙ ተጨምረው ይጻፋሉ፤ የተፋለሱ ምንባባት ይቃናሉ፡፡
(3)የቦሩ ሜዳ ጉባኤ ውሳኔ የቤተ ክርስቲያን የዶግማ መግለጫዎችን በምንረዳበት ጊዜ ስለሚኖረን የምንጮች ተዋረድ(Hierarchy of sources)ና ምንጮች ሲያከራክሩ በስተመጨረሻ በየትኛው ፍጹማዊ መስፈሪያ እንደሚፀኑ (በሕግ validity requirement እንደሚባለው) በሚያስታውቅ ዐውድ የተነገረ መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡ በጉባኤው ‹‹ሁለት ልደት›› ተብሎ የተወሰነው በዋናነት በሃይማኖተ አበው ምንባባት ነው፤ ሃይማኖተ አበው ቁጥሩ ከድርሳን ነው፡፡ እዚህ ላይ ድርሳን የሚለው የግእዝ ቃል የመጽሐፍ ማብራሪያን (Homily) እና የመላእክት/ቅዱሳን ድርሳንን (Encomium) ስለሚጠቅልል ዐውዱ እንዳያሳስተን፡፡
--
የመልእክቱ ጭብጥ፡- በገድላት ጉዳይ የማርያም መንገድ ለመስጠት አንፋጠን!
ሦስት ነገሮች ይቅደሙ፡-
(1)የገድላቱን አስፈላጊነት አምኖ መነሣት፣
(2)በሃይማኖታዊ መነጽር ማጥናት፣
(3)ማቅናት፣ የቀናውን ማጽናት፡፡
--
በቀናች ሃይማኖት አጽንቶ ከቅዱሳኑ ይደምረን! አሜን!!!
✍️ደብተራ በአማን ነጸረ እንደጻፉት
❤1👍1