Telegram Web
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሐምሌ ፭ ❖

✞✞✞ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን #ዼጥሮስ #ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

=>ፍጡር ቢከብር ከእመ ብርሃን ቀጥሎ የእነዚህን
ቅዱሳን ያህል የሚከብር አይኖርም:: ለቤተ ክርስቲያን
ያልሆኑላት ምንም ነገር የለምና እርሷም "ብርሃኖቼ:
ዐይኖቼ: ዕንቁዎቼ" ብላ ትጠራቸዋለች::

+" ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት "+

=>የዮና ልጅ ስምዖን ዼጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን
ንጹሕ አንደበት ነው:: ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ
ማለት ነው::
¤በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሳ በማጥመድ
አድጐ

¤ሚስት አግብቶ ዕድሜው 56 ሲደርስ ነበር ጌታችን
የተቀበለው:: በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ:
በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል::
ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል:: (ማቴ. 16:17, ዮሐ.
21:15)

+ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሰራው
ስሕተት ንስሃ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል:: ቅዱስ ዼጥሮስ
እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ
ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በሁዋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት
አካፍሏል:: ምንም የርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን
ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል::

+በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል:: አሕዛብ
ግብራቸው እንደ እንስሳ ነውና በአባታችን ላይ ቀልደዋል::
እርሱ ግን ሁሉንም ታግሷል:: የቅዱሱን ታሪክ ለመናገር
ከመብዛቱ የተነሳ ይከብዳልና ልቡና ያለው ሰው
ሊቃውንትን ሊጠይቅ እንደሚገባ እመክራለሁ::

+ቅዱስ ዼጥሮስ መልካሙን ገድል ተጋድሎ በ66 ዓ/ም
የኔሮን ቄሳር ወታደሮች ሲሰቅሉት ለመናቸው::
"እባካችሁን? እኔ እንደ ጌታየ ሆኜ መሰቀል አይገባኝም"
አላቸው:: እነሱም ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: በበጐ
እረኝነቱም የማታልፈውን ርስት ከነመክፈቻዋ ተቀብሏል:: በሰማዕትነት ሲያርፍም ዕድሜው ወደ 88 አካባብ ደርሶ
ነበር::

=>#የቅዱስ_ዼጥሮስ መጠሪያዎች:-

1.ሊቀ ሐዋርያት
2.ሊቀ ኖሎት (የእረኞች / ሐዋርያት አለቃ)
3.መሠረተ ቤተ ክርስቲያን
4.ኰኩሐ ሃይማኖት (የሃይማኖት ዐለት)
5.አርሳይሮስ (የዓለም ሁሉ ፓትርያርክ)

+"+ #ቅዱስ_ዻውሎስ_ሐዋርያ +"+

=>የቤተ ክርስቲያን መብራቷ ቅዱስ ዻውሎስን እንደ ምን
ባለ ዐማርኛ እንገልጠዋለን?
¤ስለ እርሱ መናገርና መጻፍ የሚችልስ እንደ ምን ያለ
ሰው ነው?
¤የዓለምን ነገር ሲጽፍ በኖረ እጄስ እንደ ምን
እጽፈዋለሁ?
¤ይልቁኑስ የርሱን 14ቱን መልዕክታትና ግብረ ሐዋርያትን
መመልከቱ ሳይሻል አይቀርም::

+#ቅዱስ_ዻውሎስ ከነገደ ብንያም #ሳውል የሚባል
የጠርሴስ ሰው ሲሆን ምሑረ ኦሪት: ቀናተኛና ፈሪሳዊ
ነበር:: ጌታ በደማስቆ ጐዳና ጠርቶ በ3 ቀናት ልዩነት
ምርጥ ዕቃ አደረገው:: ይህ የሆነው በ42 ዓ/ም: ጌታ
ባረገ በ8ኛው ዓመት ነበር:: ከዚያማ ብርሃን ሆኖ አበራ::
ጨው ሆኖ አጣፈጠ::

+ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም: ከእንግሊዝ እስከ እልዋሪቆን
(የዓለም መጨረሻ) ወንጌልን ሰበከ:: ስለ ወንጌል
ተደበደበ: ታሠረ: በእሳት ተቃጠለ:: በድንጋይ ተወገረ:
በጦር ተወጋ:: ባፍም በመጣፍም ብሎ አገለገለ::
በየቦታውም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ሠራ:: ለ25 ዓመታት
ቀንና ሌሊት ያለ መታከት ወንጌልን ሰበከ::

+እርሱን የመሰሉ: እርሱንም ያከሉ ብዙ አርድእትን አፍርቶ:
በ67 ዓ/ም በኔሮን ቄሳር ትእዛዝ አንገቱ ተቆርጧል::
ከ14ቱ መልዕክታቱ ባሻገር ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን ሲጽፍ
አግዞታል:: ልክ ቅዱስ ዼጥሮስ ማርቆስን እንዳገዘው
ማለት ነው::

=>የቅዱስ ዻውሎስ መጠሪያዎች:-

1.ሳውል (ከእግዚአብሔር የተሰጠ)
2.#ልሳነ_ዕፍረት (አንደበቱ እንደ ሽቱ የሚጣፍጥ)
3.#ልሳነ_ክርስቶስ (የክርስቶስ አንደበቱ)
4.#ብርሃነ_ዓለም
5.#ማኅቶተ_ቤተ_ክርስቲያን (የቤተ ክርስቲያን መቅረዝ)
6.#የአሕዛብ_መምሕር
7.#መራሒ (ወደ መንግስተ ሰማያት የሚመራ)
8.#አእኩዋቲ (በምስጋና የተሞላ)
9.#ንዋይ_ኅሩይ (ምርጥ ዕቃ)
10.#መዶሻ (ለአጋንንትና መናፍቃን)
11.#መርስ (ወደብ)
12.#ዛኅን (ጸጥታ)
13.#ነቅዐ_ሕይወት (የሕይወት ትምሕርትን ከአንደበቱ
ያፈለቀ)
14.#ዐዘቅተ_ጥበብ (የጥበብ ምንጭ / ባሕር)
15.#ፈዋሴ_ዱያን (ድውያንን የፈወሰ) . . .

=>ጌታችን እግዚአብሔር የአባቶቻችንን ብርሃን ያብራልን::
ከበረከታቸውም ያድለን::

=>ሐምሌ 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
3.ቅዱሳን 72ቱ አርድእት (ዛሬ ሁሉም ይታሠባሉ)
4.ቅዱስ ሳቁኤል ሊቀ መላእክት
5.ቅድስት መስቀል ክብራ (የቅዱስ ላሊበላ ሚስት)
6.ቅዱሳን ዘደብረ ዓሣ
7.ቅዱሳት አንስት (ዴውርስ: ቃርያ: አቅባማ: አቅረባንያና
አክስቲያና-የቅዱስ ዼጥሮስ ተከታዮች)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
2.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
3.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
4.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)

=>+"+ ጌታ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው:: "የዮና
ልጅ ስምዖን ሆይ! በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና
ደም ይሕንን አልገለጠልህምና ብጹዕ ነህ:: እኔም
እልሃለሁ:: አንተ #ዼጥሮስ ነህ:: በዚህችም ዓለት ላይ
ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ:: የገሃነም ደጆችም
አይችሏትም:: የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች
እሰጥሃለሁ:: በምድር የምታሥረው ሁሉ በሰማያት የታሠረ
ይሆናል:: በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ
ይሆናል::" +"+ (ማቴ. 16:17)

=>+"+ በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት
ይሠዋልና:: የምሔድበትም ጊዜ ደርሷል:: መልካሙን
ገድል ተጋድያለሁ:: ሩጫውን ጨርሻለሁ:: ሃይማኖትን
ጠብቄአለሁ:: ወደ ፊት #የጽድቅ_አክሊል ተዘጋጅቶልኛል::
ይሕንም ጻድቅ: ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ
ያስረክባል:: +"+ (2ጢሞ. 4:6)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>


" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tgoop.com/zikirekdusn
#Feasts of #Hamle_5

✞✞✞On this day we commemorate the departure of Saints Peter and Paul, the Luminaries of the World✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

=>None, if any is glorified from creation as such, is honored like these Saints after the Mother of Light. Because they were everything to the Church, She in turn calls them as, “My Lights, My Eyes, and My Jewels”.

✞✞✞Saint Peter the Arch-apostle✞✞✞
=>The son of Jona, Simon, was called Peter (Cephas) by the pure tongue of our Lord. And it, his name, means a stone/ a rock, a foundation.
¤The Saint grew up with his brother, Andrew, at Bethsaida catching fish.
¤And while married and at the age of 56, was when our Lord received him. Because of his age and zeal, and for his wisdom, he was called a Foundation of the Church. And became the Arch of the Apostles. (Matt. 16:17/John21:15).

✞St. Peter became an example to all after he repented for his transgression during the night during which our Lord Jesus Christ was caught. St. Peter as a shepherd kept the Apostles and enabled them to receive the Holy Spirit, and after Pentecost he allotted dioceses for all. Though his lot was Rome, to strengthen the disciples, the Saint has traveled to all of the Sees.

✞St. Peter received much tribulation in his old age. And because the deeds of the gentiles were like those of animals, they mocked our father. Nonetheless, he endured all. Since, the account of the Saint is much and difficult to speak of, I advise the need for the one who takes heed to ask the scholars.

✞St. Peter after fighting the good fight, in 66 A.D when the soldiers of Caesar crucified him, he asked them one thing. He said, “Please, I should not be crucified like my Lord!” Hence, they crucified him upside down and killed him. And for his good shepherding, he received the everlasting inheritance and its key. And when he departed as a martyr, he was around the age of 88.

✞The Titles of St. Peter
1. Arch of the Apostles
2. Arch of the Shepherds
3. The Foundation of the Church
4. The Rock of Faith
5. Arsairos (Patriarch of the World)

✞✞✞Saint Paul the Apostle✞✞✞
=>In what words could we describe the Light of the Church, St. Paul?
¤ Who is he/she that is able to speak or write about him?
¤ How could I write [about him] with my hand that has been etching about the world?
¤ I think it is rather better to see his 14 Epistles and the Acts of the Apostles.

✞St. Paul was a man called Saul from Tarsus from the Tribe of Benjamin that was a scholar of the Old Testament, a zealot, and a pharisee. The Lord called him on the road to Damascus and in 3 days made him a chosen vessel. And this occurred in 42 A.D on the 8th year of the Ascension of the Lord. Thereafter, he became light and shone. He also became salt and gave savor to the world.

✞The Saint preached the Gospel from Jerusalem to Britain (Britannia) and form Britain to Illyricum (end to the inhabited lands). He was beaten, imprisoned, and torched for the Gospel. He was stoned and lanced as well. The Apostle served by preaching and writing letters. He also performed wonderous miracles at different places. He preached the Gospel for 25 years, day and night, without lethargy.

✞After he bore many disciples in his likeness and measure, by the order of Caesar Nero he was beheaded in 67 A.D. In addition to the 14 Epistles, St Paul aided St. Luke when he wrote the Gospel like St. Peter who helped St. Mark.

✞The Titles of St. Paul
1. Saul (Given of God)
2. Sweet Tongued
3. Tongue of Christ
4. Light of the World
5. Candle of the Church
6. Teacher of the Gentiles
7. Leader (One who leads to the Kingdom of God)
8. Praiser/Full of Praise
9. Chosen Vessel
10. Hamer (to demons and heretics)
11. Harbor
12. Calm/Peace
13. Spring of Life (A teaching of life)
14. Spring/Well of Wisdom
15. Healer of the Sick . . .

✞✞✞May our Lord, God, shine for us the light of our fathers. And may He grant us from their blessings.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 5th of Hamle
1. St. Peter the Arch-apostle
2. St. Paul the Light of the World
3. The Holy 72 Disciples (All are commemorated today)
4. St. Saquel the Archangel
5. St. Mesqel Qebra (The wife of St. Lalibela the Emperor)
6. Saints of Debre Asa
7. Holy Women (Dewres, Karia, Akbama, Akrebania, and Akestiana – followers of St. Peter)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. Abune Gebre Menfes Qidus
2. St. Yohani the Ethiopian
3. St. Amoni of Nah(i)so
4. St. Eugenia (Martyr and Righteous)

✞✞✞“And Jesus answered and said unto him, Blessed art thou, Simon Bar–jona: for flesh and blood hath not revealed it unto thee, but my Father which is in heaven. And I say also unto thee, That thou art Peter, and upon this rock I will build my church; and the gates of hell shall not prevail against it. And I will give unto thee the keys of the kingdom of heaven: and whatsoever thou shalt bind on earth shall be bound in heaven: and whatsoever thou shalt loose on earth shall be loosed in heaven.”✞✞✞
Matt. 16:17-19

✞✞✞“For I am now ready to be offered, and the time of my departure is at hand. I have fought a good fight, I have finished my course, I have kept the faith: Henceforth there is laid up for me a crown of righteousness, which the Lord, the righteous judge, shall give me at that day”✞✞✞
2 Tim. 4:6-8

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርሃ ሐምሌን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
          

🌿ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!


1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, አላማ

    2 ,እምነት

    3,ጥረት

    4 ጥንቃቄ
=>እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።


🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tgoop.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
ቅድስት መስቀል ክብራ

የደጉ ንጉሥ የቅዱስ ላል ይበላ ሚስት።

እግዚአብሔርን በቅድስና በበጎ ሥራስታገለግል የኖረች።

ከ፲፩ዱ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያን አንዱ የሆነውን ቤተ ሊባኖስን ያሳነጸች።

🌿በቅድስና ኖራ ያረፈች እናታችን በረከቷ ይደርብን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tgoop.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
ቅዱስ ሳቁኤል መልአክ

   ከ፯ቱ እና ከ፲፪ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ።

መልአከ ሞትን የሚያዘው መልአክ
ቅዱስ ሳቁኤል ጠባቂያችን
ሐምሌ፭ በዓሉ ነው።

       አማላጅነቱ ጥበቃው አይለየን ከማይጠቅም ሞት ይጠብቀን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tgoop.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
እንኳን አደረሰን!

" ... ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዕደ እግርክሙ ጌሠ፤
ጽንዐ ኃይልክሙ ሰቀለ ንጉሠ፤
ወዕበይክሙ አስገደ አፍራሠ!" (አርኬ)

የቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ ቸሩ መድኀኔዓለም፦

ሰላሙን ፍቅሩን፤
ስምምነት አንድነቱን፤
በረከት ረድኤቱን፤
ዝናመ ምሕረቱን፤
ጠረ በረከቱን . . . አይንሳን!

💥ከአርዕስተ ሐዋርያት ክቡራን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ጸጋ ክብር ያሳትፈን!

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗
https://www.tgoop.com/zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
እንኳን አደረሳችሁ!

በደመ ስምዖሙ ተማኅጸነ፤
ለጴጥሮስ አቡነ፥ ወጳውሊ ፍቁርነ፤
ጸሎተነ አጽምዕ ፍጡነ፤
እስመ ንጸንሐከ እምዘመን ዘመነ!

ቸሩ ሆይ፥ ስለ ፈሰሰ ደማቸው ብለህ ከምድሩ መቅሠፍት፥ ከሰማዩ እሳት አድነን!

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗
https://www.tgoop.com/zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
2025/07/12 01:16:28
Back to Top
HTML Embed Code: