tgoop.com/And_Haymanot/3902
Last Update:
✝ኃጢአትን ለንስሓ አባት/ለካህን መናዘዝ/
@And_Haymanot
ተወዳጆች የተሀድሶ መናፍቃን ምዕመናንን ከንስሃ ህይወት ለማራቅ ሃጢአትን ለንስሃ አባት መናዘዝ አያሥፈልግም በማለት ሀጢአትን ለካህን መናዘዝን ይቃወማሉ፡፡ እናት ቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ እንዲህ ታሥተምራለች
@And_Haymanot
ካህን የእግዚአብሔር ምሥጢራት አስፈፃሚ ስለሆነ ኃጢአትህን ንገረው ። ይህን ቅዱስ ጳውሎስም አስረግጦ ጽፎልሃል ። " እንዲሁ ሰው እኛን እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቁጠር ።" 1ቆሮ 4*1
አስቀድሞም በነቢዩ ሚኪያስ ያደረው እግዚአብሔር ሲናገር "ካህኑ የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ነው "ይላል ።
ኃጢአትህን ለካህን በምትነግርበት ጊዜ የሚሰማህን ኃፍረት መሸማቀቅ ሁሉ ችለህ የመመለስን ምሥጢር እንዲያስፈጽምልህ ስትጥር እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ድርጊትህን እንደ ታላቅ መሥዋእትነት ቆጥሮልህ ኃጢአትህን ሁሉ ይደመስስልሃል ።/ ዩሐ 20*21*23/ ማቴ 18*18
ካህኑ ክርስቶስ በሰጠው በዚህ ሥልጣን መሠረት ከኃጢአት እሥራት መፈታትህን ያረጋግጥልሀል ። ሕይወት ለሚሆነው ሥጋና ደሙ እንድትበቃም ያደርግሃል ።/1ቆሮ 11*27/
በሕይወትህ ውስጥ የሚታዩትን ጉድለቶች (መንፈሳዊ ድክመቶች )እየተመለከተም እንዴት አሸናፊ መሆን እንደምትችል የሚመክርህ መንፈሳዊ መሪህ ካህን የንስሓ አባት መሆኑንም አትዘንጋ ።
ለካህን ኃጢአትን መናዘዝህ በራሱ የሚያተርፍልህ ነገር አለው ። ኃጢአትን መልሰህ ስትናገረው ለአንተ ለራስህ ምን ያህል አሳፋሪ እንደሆነ ይሰማሃል ። ይህም ዳግም እንዳትመለስበት ታላቅ ትምህርት ይሰጥሀል ። መጽሐፍ ቅዱስም የሚለው ይህንኑ ነው ። " እርስ በእርሳችሁ ኃጢአታችሁን ተናዘዙ ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ሰው ስለሌለው ይጸልይ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች ።" /ያዕ 5*16 /
ምንጭ @pope_shenouda
@pope_shenouda
___፩ ሃይማኖት_______
ላልደረሳቸው እናዳርስ
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት የሲኦል ደጆች አይችሏትም ቤተክርስቲያን
@And_Haymanot
#______አትታደስም______!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
@And_Haymanot
============================
፩ ጌታ
፩ ሃይማኖት
፩ ጥምቀት ኤፌ4:5
BY ፩ ሃይማኖት
Share with your friend now:
tgoop.com/And_Haymanot/3902