CAMPUS_LOVE Telegram 1986
......የሀዘኔ መጨረሻ .........

ክፍል 19

.....አይሆንም አሉ፡፡ ከዛን ወደ መኝታ ክፍላቸው ገቡ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳም ተከትላቸው ገባች፡፡ እኔና ብሩኬ ብቻ ቀረን፡፡ "ሰላሜ ካንቺ መለየት አልፈልግም " አለኝ፡፡ እንባዬ ፈሰሰ ፊቴ ላይ የውሸት ፈገግታ ጣል እያደረኩበት "ብሩኬ የአባትህን ትዛዝ ማክበር አለብህ እኔ ሁሌም እጠብቅሀለው " ብዬው እየሮጥኩኝ ወደ ክፍሌ ገብቼ ማልቀሴን ቀጠልኩኝ፡፡

ያው ጊዜያቶች ሄዱ፡፡ ብሩኬ ወደ ሌላ ዮንቨርስቲ እንዲሄድ ሆነ፡፡ በጣም ነበር የከፋኝ፡፡ ብሩኬም እንደዛው፡፡ ብሩኬ እቃዎቹን ማዘገጃጀት ጀመረ፡፡ የመሄጃው ቀን አይኑን አፍጥጦ ወጣ፡፡ የደረሰው ባህር ዳር ዮንቨርስቲ ነበር፡፡

አመሻሽ ላይ ብሩኬን የሚወስደው መኪና መጣ፡፡ በፍጥነት ከክፍሌ ወጥቼ ወደ ሳሎን ሄድኩኝ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩኬን አቅፋ ታለቅሳለች፡፡ አቤል ሶፋው ጥግ ላይ ተቀምጦ ለንቦጩን ጥሎታል፡፡ አቶ ሄኖክ ወ/ሮ ኤልሳን ማባበል ይዘዋል፡፡ ደርቄ ቀረሁኝ፡፡ ብሩኬ ዞር ብሎ አየኝ ከማልቀሴ ብዛት አይኖቼ ቲማቲም መስለው ነበር፡፡ ወደኔ ቀረብ አለኝ አንገቴን አቀረቀርኩኝ "ሰሊ ቻው አትይኝም እንዴ " አለኝ ፡፡ ከአይኔ እንባ እየፈሰሰ ተጠመጠምኩበት፡፡ አቶ ሄኖክ በድካም ስሜት ሶፋው ላይ ቁጭ አሉ፡፡

ከብሩኬ እቅፍ መውጣት አልፈለኩም ነበር፡፡ ግን ወድያው ሹፌሩ መጣና "ዝግጁ ነኝ ጌታዮ መሄድ እንችላለን " አለ፡፡ አቶ ሄኖክም " በል ልጄ እንዳይረፍድብህ ሂድ " አሉት፡፡ እሱም ወደ መኪናው አመራ፡፡ ከአይኖቹ እንባ ጠብ ጠብ ሲል ታየኝ፡፡ ፈጣሪዬ ለምንድን ነው የምወዳቸውን ሰዎች የሚወስድብኝ ብዬ ተማረርኩኝ፡፡ ሁላችንም አቅፎን መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ሁላችንም እያለቀስን ነው፡፡ መኪናው መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ገና ከግቢ ሳይወጣ ቆመ፡፡ ብሩኬ ከመኪናው ውስጥ ወጥቶ አቶ ሄኖክ እግር ስር ወድቆ " አባቴ እባክህ እንድሄድ አታስገድደኝ እኔ እዚሁ መማር ነው የምፈልገው፡፡ ያንተን ትዕዛዝ ላለመሻር ብዬ የማልፈልገውን ነገር እንዳደርግ አትፍረድብኝ እባክህ አባት! " አለው፡፡ አቶ ሄኖክ ራሳቸውን ያዝ አደረጉ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩኬን ከአቶ ሄኖክ እግር ስር እያነሳች " ሄኖክ አሁንስ አበዛኀው ልጄ ጥሩ ልጅ ነው እንደማንኛውም ሌባ አይደለም ለሁሉምለሚፈልገው ነገር ዋጋ መክፈል ያውቃል ልጄን እንደዚ ነው ያሳደግኩት ስለዚህ እዚሁ እንዲማር አድርግ እባክህ አታስገድደው " አለችው፡፡

አቶ ሄኖክም ብሩኬን አቀፍ እያደረጉ " ልጄ ታውቃለህ ላንተ የሚበጀውን ነው የምፈልገው ግን እንደማንኛውም የሀብታም ልጅ በቤተሰብህ ብር የምትመካ እንዳትሆን ብዮ ነው " አሉት ፡፡ ብሩኬም "አይዞህ አባቴ እንደዚያ አይነት ሰው አልሆንም ብቻ አንተ አታስገድደኝ" አለው፡፡ አቶ ሄኖክም "እሺ ልጄ አምንሀለው እዚሁ ትማራለህ "አሉት፡፡ ሁላችንም ፊት ላይ ፈገግታ አበራ፡፡ ተቃቀፍን፡፡ ወደ ቤታችንም ገባን፡፡ የዛን ቀን ከምታስቡት በላይ ነበር ደስያለኝ፡፡የኔና የብሩኬ ፍቅርም ጦፈ፡፡

ብሩኬም ኮሌጅ ገባ እኔም 12ኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ብሩኬ በትምህርቱ በጣም ጎበዝ ስለሆነ ያስጠናኛል፡፡ የምር አፍቃሪ ነው፡፡ አንድ ቀን ክፍሌ ውስጥ እያስጠናኝ " ሰላሜ " አለኝ፡፡ "ወዬ " አልኩት፡፡ ትኩር ብሎ እያየኝ "በጣም እኮነው የማፈቅርሽ " አለኝ፡፡እኔም በስስት እያየሁት " እኔም በጣም አፈቅርሀለው " አልኩት፡፡ አይን ለአይን ተፋጠጥን......

ክፍል 20 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ



tgoop.com/Campus_love/1986
Create:
Last Update:

......የሀዘኔ መጨረሻ .........

ክፍል 19

.....አይሆንም አሉ፡፡ ከዛን ወደ መኝታ ክፍላቸው ገቡ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳም ተከትላቸው ገባች፡፡ እኔና ብሩኬ ብቻ ቀረን፡፡ "ሰላሜ ካንቺ መለየት አልፈልግም " አለኝ፡፡ እንባዬ ፈሰሰ ፊቴ ላይ የውሸት ፈገግታ ጣል እያደረኩበት "ብሩኬ የአባትህን ትዛዝ ማክበር አለብህ እኔ ሁሌም እጠብቅሀለው " ብዬው እየሮጥኩኝ ወደ ክፍሌ ገብቼ ማልቀሴን ቀጠልኩኝ፡፡

ያው ጊዜያቶች ሄዱ፡፡ ብሩኬ ወደ ሌላ ዮንቨርስቲ እንዲሄድ ሆነ፡፡ በጣም ነበር የከፋኝ፡፡ ብሩኬም እንደዛው፡፡ ብሩኬ እቃዎቹን ማዘገጃጀት ጀመረ፡፡ የመሄጃው ቀን አይኑን አፍጥጦ ወጣ፡፡ የደረሰው ባህር ዳር ዮንቨርስቲ ነበር፡፡

አመሻሽ ላይ ብሩኬን የሚወስደው መኪና መጣ፡፡ በፍጥነት ከክፍሌ ወጥቼ ወደ ሳሎን ሄድኩኝ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩኬን አቅፋ ታለቅሳለች፡፡ አቤል ሶፋው ጥግ ላይ ተቀምጦ ለንቦጩን ጥሎታል፡፡ አቶ ሄኖክ ወ/ሮ ኤልሳን ማባበል ይዘዋል፡፡ ደርቄ ቀረሁኝ፡፡ ብሩኬ ዞር ብሎ አየኝ ከማልቀሴ ብዛት አይኖቼ ቲማቲም መስለው ነበር፡፡ ወደኔ ቀረብ አለኝ አንገቴን አቀረቀርኩኝ "ሰሊ ቻው አትይኝም እንዴ " አለኝ ፡፡ ከአይኔ እንባ እየፈሰሰ ተጠመጠምኩበት፡፡ አቶ ሄኖክ በድካም ስሜት ሶፋው ላይ ቁጭ አሉ፡፡

ከብሩኬ እቅፍ መውጣት አልፈለኩም ነበር፡፡ ግን ወድያው ሹፌሩ መጣና "ዝግጁ ነኝ ጌታዮ መሄድ እንችላለን " አለ፡፡ አቶ ሄኖክም " በል ልጄ እንዳይረፍድብህ ሂድ " አሉት፡፡ እሱም ወደ መኪናው አመራ፡፡ ከአይኖቹ እንባ ጠብ ጠብ ሲል ታየኝ፡፡ ፈጣሪዬ ለምንድን ነው የምወዳቸውን ሰዎች የሚወስድብኝ ብዬ ተማረርኩኝ፡፡ ሁላችንም አቅፎን መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ሁላችንም እያለቀስን ነው፡፡ መኪናው መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ገና ከግቢ ሳይወጣ ቆመ፡፡ ብሩኬ ከመኪናው ውስጥ ወጥቶ አቶ ሄኖክ እግር ስር ወድቆ " አባቴ እባክህ እንድሄድ አታስገድደኝ እኔ እዚሁ መማር ነው የምፈልገው፡፡ ያንተን ትዕዛዝ ላለመሻር ብዬ የማልፈልገውን ነገር እንዳደርግ አትፍረድብኝ እባክህ አባት! " አለው፡፡ አቶ ሄኖክ ራሳቸውን ያዝ አደረጉ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩኬን ከአቶ ሄኖክ እግር ስር እያነሳች " ሄኖክ አሁንስ አበዛኀው ልጄ ጥሩ ልጅ ነው እንደማንኛውም ሌባ አይደለም ለሁሉምለሚፈልገው ነገር ዋጋ መክፈል ያውቃል ልጄን እንደዚ ነው ያሳደግኩት ስለዚህ እዚሁ እንዲማር አድርግ እባክህ አታስገድደው " አለችው፡፡

አቶ ሄኖክም ብሩኬን አቀፍ እያደረጉ " ልጄ ታውቃለህ ላንተ የሚበጀውን ነው የምፈልገው ግን እንደማንኛውም የሀብታም ልጅ በቤተሰብህ ብር የምትመካ እንዳትሆን ብዮ ነው " አሉት ፡፡ ብሩኬም "አይዞህ አባቴ እንደዚያ አይነት ሰው አልሆንም ብቻ አንተ አታስገድደኝ" አለው፡፡ አቶ ሄኖክም "እሺ ልጄ አምንሀለው እዚሁ ትማራለህ "አሉት፡፡ ሁላችንም ፊት ላይ ፈገግታ አበራ፡፡ ተቃቀፍን፡፡ ወደ ቤታችንም ገባን፡፡ የዛን ቀን ከምታስቡት በላይ ነበር ደስያለኝ፡፡የኔና የብሩኬ ፍቅርም ጦፈ፡፡

ብሩኬም ኮሌጅ ገባ እኔም 12ኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ብሩኬ በትምህርቱ በጣም ጎበዝ ስለሆነ ያስጠናኛል፡፡ የምር አፍቃሪ ነው፡፡ አንድ ቀን ክፍሌ ውስጥ እያስጠናኝ " ሰላሜ " አለኝ፡፡ "ወዬ " አልኩት፡፡ ትኩር ብሎ እያየኝ "በጣም እኮነው የማፈቅርሽ " አለኝ፡፡እኔም በስስት እያየሁት " እኔም በጣም አፈቅርሀለው " አልኩት፡፡ አይን ለአይን ተፋጠጥን......

ክፍል 20 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ

BY Campus love ❤ Stories


Share with your friend now:
tgoop.com/Campus_love/1986

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

“Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group. The administrator of a telegram group, "Suck Channel," was sentenced to six years and six months in prison for seven counts of incitement yesterday. As the broader market downturn continues, yelling online has become the crypto trader’s latest coping mechanism after the rise of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May and beginning of June, where holders made incoherent groaning sounds and role-played as urine-loving goblin creatures in late-night Twitter Spaces. Telegram channels enable users to broadcast messages to multiple users simultaneously. Like on social media, users need to subscribe to your channel to get access to your content published by one or more administrators. Step-by-step tutorial on desktop:
from us


Telegram Campus love ❤ Stories
FROM American