tgoop.com/Dire_Tube_news/18350
Last Update:
“ሸኔ” በምእራብ ወለጋ ዞን 10 ሰዎችን ማገቱን መንግስት አስታወቀ
ባንክ እና ፍርድ ቤትን ጨምሮ ከ34 በላይ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና ተቋማት ላይም ዝርፊያ ፈጽሟል።
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የፈረጀው “ሸኔ” በምእራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ በፈፀመው ጥቃት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን መንግስት አስታወቀ።
የቆንዳላ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ቡላ ደመረ በወረዳው “ሸኔ” በፈጸመው ጥቃት የንጹሃን የተገደሉ ሲሆን፣ በርካታ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተዘርፈው በእሳት ተቃጥለዋል ማለታቸውን ኢዜአ በአፋን ኦሮሞ ገጽ አስነብቧል።
“በጥቃቱ ሸኔ 10 ሰዎችን አግቶ ወስዷል” ያሉት አቶ ቡላ ደመረ፤ 24 ንጹሃን ዜጎችን መግደሉንም አስታውቀዋል።
ቡድኑ የወረዳውን ፍርድ ቤት እና የአቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ሙሉ በሙሉ በእሳት ማጋየቱን በመጥቀስ፤ 4 የመንግስት አመራሮች መኖሪያ ቤቶችንም አቃጥሏል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቆንዳላ ቅርንጫፍን አንዲሁም በ34 የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና ተቋማት ላይ ዝርፊያ መፈጸሙን ያስታወቁት የወረዳው አስተዳዳሪ፤ በወረዳው የሚገኝ የ2ኛ ደረጃ ትምህት ቤት ንብረት እና የተማሪዎችን ማስረጃ ማውደሙንም ተናግረዋል።
የ“ሸኔ” ታጣቂዎች በአጠቃላይ በወረዳው ከነሃሴ 9፣ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በፈጸሙት ጥቃት ከ200 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙን የቆንዳላ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ቡላ ደመረ ገልጸዋል።
“ህብረተሰቡ የሸኔ የሽብር ብድን የጥፋት ተግባርን ተረድቶ በአንድነት በመሆን የቡድኑን የጠላትነት ተግባር ሊያጋልጥ ይገባል” ሲሉም ዋና አስተዳዳው ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@Dire_Tube_news
@Dire_Tube_news
BY Dire Tube news
Share with your friend now:
tgoop.com/Dire_Tube_news/18350