tgoop.com/Dire_Tube_news/18355
Create:
Last Update:
Last Update:
አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያውያንን የሚጠላ ራስወዳድ ቡድን ነው፡- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ
አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያውያንን የሚጠላ እና ራሱን ብቻ ከሌሎች ነጥሎ የሚወድ ስግብግብ ቡድን መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ምልምል አባላት ምረቃ ላይ ተገኝተዋል፡፡
በዚሁ ጊዜ እንዳሉት አሸባሪው የህወሓት ቡድን ለኢትዮጵያ እንቅርት ሆኖባታል፡፡
ይህን ፈተና ለማለፍ ብልሃት፣ አንድነት እና ቆራጥነት ያስፈልጋል ያሉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ይህንን መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ባለፉት ወራቶች በተደረጉ ኦፕሬሽኖች አሁንም ኢትዮጵያ የጀግኖች ሀገር መሆኗን አይተናል ብለዋል፡፡
አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፈራረስ እና አንድነቷን ለመበተን አስቦ እየሰራ ቢሆንም በተቃራኒው ኢትዮጵያ ዳግም አንድ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል፡፡
@Dire_Tube_news
@Dire_Tube_news
BY Dire Tube news
Share with your friend now:
tgoop.com/Dire_Tube_news/18355