DUZZL Telegram 2604
ከዚህ ወዲያ ፍቅር!


በዕድሜ ማለዳ በአበባው የልጅነት ወቅት የሚታደሉት የለመለመ ዓለም ነው።ኣው! ለኔ የሩሔን ፍሰሃ የምቋደስበት ምድረገነቴ ነው።እድሉ ገጥሞት የቀረበ ያደገበት፣ወይም የተጠጋው ያውቀዋል።
የኻዲሞች መተናነስን ከሩቅ እያየን ስንገረም ያደግነበት ሐድራ።ትልቅ ሰዎች ታናናሾቻቸውን ሲካድሙ፣ወጣቶች ተቀምጠው አባቶች ቡና ሲቀዱ፣እሳት ሲያነዱ እያየን እንገረም ነበር።ኻዲሞች የሚለዩት ደግሞ ሻላቸውን ወገባቸው ላይ(ኣንዳንድ ቦታ ደግሞ ከትከሻቸው ላይ) ጠበቅ ኣርገው በማሰር ነው።ለካ ለኺድማው ታጥቂያለው ነው!።
እድሜ እውቅና ሳይገድበው ለታናሽ ማዘንን፣ታላቅን ማክበርን እዚህ በተግባር ይዳሰሳል።አባቶች ከነ ትጥቃቸው ወዲህ ወዲያ ሲሉ ይውላሉ።የኺድማ ተራቸው ሲደርስ ልባቸው በሐሴት የሚደልቅ መሆኑ እርምጃቸው፣ቅልጥፍናቸው፣
ከፊታቸው የሚነበብ ፈገግታ በጉልህ ያሳብቃል።

ልብን በአደብ አስተምሕሮና ማንነትን በዕመነት ቀርፆ፣ ኣስዉቦ ከሚያሰለጥን ስልጣኔ ኹሉ ቀዳሚ የማደርገው ሐድራን ነው።ምናልባትም ዛሬ ብዙዎች ላይ ከሚታየው የመልካም ስነ–ምግባር ነፀብራቅ ጀርባ የዚህኛው ዓለም ጠብታዎች ይኖራሉ።በወንድምነት ሰንሰለት የተጋመደ ሁሉ ሶፉን ደምድሞ
ይቀመጣል።ክብ መጅሊስ መሐል የተቀመጠች የእጣን ማጨሻ እቃ እንኳ በከበቧት አስሃቦች ነሻጣ የነሸጠች ትመስላለች።ሽቅብ የሚምዘገዘግ ጭሷን እያንቦገቦገች ቅጥሩን በመልካም መዓዛ ታውደዋለች።እዚህ ከተሰበሰበው ዙምራ ውስጥ አንድም የግል ፍላጎት ኣይንፀባረቅም።አንድም ሰው "እኔ"ብሎ ሚያብሰለስለው ሐጀት የለውም።
ሁሉም ሁሉንም ይረሳል።ግጣሙ ህብረት እኛነትን ገንብቶ፣እኔነትን ኣጥፍቷል።

ሩህ በኺያል ሲከንፍ ዛት ግራና ቀኝ ይወዘወዛል።ጃሊሶች ሁሉ ህብረት በኳለው ዜማ የሚቀኙት ሰላዋት ላይ ተጠምደዋል።ቀልባቸው ላይ የሚፈስስ ዘምዘም ይኖር ይመስል ፍካትን ተላብሰዋል።እዚህ መደማመጥ እንጂ ረብሻ አይታሰብም።ኢማሙ ቢቻ ወይም ኢማሙን ያስፈቀደ ሰው ብቻ! ለዚያውም ቀልብን የሚያርስ፣የሼኾችን ተርቲብ የጠበቀ ወግ ካለው ያወጋል።ሁሉም በጥሞና ያዳምጣል።

በየ ደውሩ ሶፉን ደምድሞ ከተቀመጠው ሐዲር ላይ የሚነበብ ፍቅር፣የቀልብ ሰላም አለ።የወንድምነት ጥምረቱ ባቀማመጥ ይጌጣል።እግሩን ኣጣጥፎ ከተቀመጠ ወንድም ኣጠገብ ጉልበቱ ከጉልበቱ ጋር የገጠመ ወንድም ከጎኑ አለ።በዚሁ ትስስር ሁሉም ኣንድ ይሆናል።በመሐል ደወሩን የሚመሩት ሼኽ እስካላዘዙ ድረስ ኸልዋው ላይ ፍፁም ሰላማዊ ፀጥታ ይሰፍናል።ምንም ኣይነት ኮሽታ ይጠፋል።ፀጥ ረጭ ያሉ ሓዲሮች ቀልባቸው ወደ ኻሊቅ የኮበለሉ ጅስሞች።
………

ልጅ ሆነን፣ በረንዳ ተቀምጠን ከሩቅ የምንቃኘው እኛ እንኳን ገብቶን ይሁን ሳይገባን ብቻ በንዝረት እንወዛወዝ ነበር።

ጥንፍ የጥንፍፍ ልጅ ባባቱም በናቱ፣
ውልውልም የለው መድሓኒትነቱ፣
እንዴት ናት ወላጁ እንዴት ናት እናቱ፣
የኑር ማኖሪያቱ የኑር ሱንዱቂቱ፣
ያለችው ሴቶቹን አትወልዱም እንደኔ።
አሏሁመሶሊ………ሲሉ ሰሊውን ያቀብላሉ።
ኣሺቁም በህበረት ይቀበላል።

ባንድነት የተዋበ፣ባብሮነት ጣምራ የተጌጠ የፍቅር ዜማ ይንቆረቆራል።ቅጥሩ ዳግም ይጀድዳል።
ሳር ቅጠሉም በመደድ ይገባል።ትዕይንቱ ልባችንን በፍቅር ይሞላዋል።ያኔ የተጋትነውን ፍቅር በሩሓችን አፀድ ላይ ነግሷል።እናም ከዚህ ወዲያ ፍቅር የታለ ያስብለናል!❤️



tgoop.com/Duzzl/2604
Create:
Last Update:

ከዚህ ወዲያ ፍቅር!


በዕድሜ ማለዳ በአበባው የልጅነት ወቅት የሚታደሉት የለመለመ ዓለም ነው።ኣው! ለኔ የሩሔን ፍሰሃ የምቋደስበት ምድረገነቴ ነው።እድሉ ገጥሞት የቀረበ ያደገበት፣ወይም የተጠጋው ያውቀዋል።
የኻዲሞች መተናነስን ከሩቅ እያየን ስንገረም ያደግነበት ሐድራ።ትልቅ ሰዎች ታናናሾቻቸውን ሲካድሙ፣ወጣቶች ተቀምጠው አባቶች ቡና ሲቀዱ፣እሳት ሲያነዱ እያየን እንገረም ነበር።ኻዲሞች የሚለዩት ደግሞ ሻላቸውን ወገባቸው ላይ(ኣንዳንድ ቦታ ደግሞ ከትከሻቸው ላይ) ጠበቅ ኣርገው በማሰር ነው።ለካ ለኺድማው ታጥቂያለው ነው!።
እድሜ እውቅና ሳይገድበው ለታናሽ ማዘንን፣ታላቅን ማክበርን እዚህ በተግባር ይዳሰሳል።አባቶች ከነ ትጥቃቸው ወዲህ ወዲያ ሲሉ ይውላሉ።የኺድማ ተራቸው ሲደርስ ልባቸው በሐሴት የሚደልቅ መሆኑ እርምጃቸው፣ቅልጥፍናቸው፣
ከፊታቸው የሚነበብ ፈገግታ በጉልህ ያሳብቃል።

ልብን በአደብ አስተምሕሮና ማንነትን በዕመነት ቀርፆ፣ ኣስዉቦ ከሚያሰለጥን ስልጣኔ ኹሉ ቀዳሚ የማደርገው ሐድራን ነው።ምናልባትም ዛሬ ብዙዎች ላይ ከሚታየው የመልካም ስነ–ምግባር ነፀብራቅ ጀርባ የዚህኛው ዓለም ጠብታዎች ይኖራሉ።በወንድምነት ሰንሰለት የተጋመደ ሁሉ ሶፉን ደምድሞ
ይቀመጣል።ክብ መጅሊስ መሐል የተቀመጠች የእጣን ማጨሻ እቃ እንኳ በከበቧት አስሃቦች ነሻጣ የነሸጠች ትመስላለች።ሽቅብ የሚምዘገዘግ ጭሷን እያንቦገቦገች ቅጥሩን በመልካም መዓዛ ታውደዋለች።እዚህ ከተሰበሰበው ዙምራ ውስጥ አንድም የግል ፍላጎት ኣይንፀባረቅም።አንድም ሰው "እኔ"ብሎ ሚያብሰለስለው ሐጀት የለውም።
ሁሉም ሁሉንም ይረሳል።ግጣሙ ህብረት እኛነትን ገንብቶ፣እኔነትን ኣጥፍቷል።

ሩህ በኺያል ሲከንፍ ዛት ግራና ቀኝ ይወዘወዛል።ጃሊሶች ሁሉ ህብረት በኳለው ዜማ የሚቀኙት ሰላዋት ላይ ተጠምደዋል።ቀልባቸው ላይ የሚፈስስ ዘምዘም ይኖር ይመስል ፍካትን ተላብሰዋል።እዚህ መደማመጥ እንጂ ረብሻ አይታሰብም።ኢማሙ ቢቻ ወይም ኢማሙን ያስፈቀደ ሰው ብቻ! ለዚያውም ቀልብን የሚያርስ፣የሼኾችን ተርቲብ የጠበቀ ወግ ካለው ያወጋል።ሁሉም በጥሞና ያዳምጣል።

በየ ደውሩ ሶፉን ደምድሞ ከተቀመጠው ሐዲር ላይ የሚነበብ ፍቅር፣የቀልብ ሰላም አለ።የወንድምነት ጥምረቱ ባቀማመጥ ይጌጣል።እግሩን ኣጣጥፎ ከተቀመጠ ወንድም ኣጠገብ ጉልበቱ ከጉልበቱ ጋር የገጠመ ወንድም ከጎኑ አለ።በዚሁ ትስስር ሁሉም ኣንድ ይሆናል።በመሐል ደወሩን የሚመሩት ሼኽ እስካላዘዙ ድረስ ኸልዋው ላይ ፍፁም ሰላማዊ ፀጥታ ይሰፍናል።ምንም ኣይነት ኮሽታ ይጠፋል።ፀጥ ረጭ ያሉ ሓዲሮች ቀልባቸው ወደ ኻሊቅ የኮበለሉ ጅስሞች።
………

ልጅ ሆነን፣ በረንዳ ተቀምጠን ከሩቅ የምንቃኘው እኛ እንኳን ገብቶን ይሁን ሳይገባን ብቻ በንዝረት እንወዛወዝ ነበር።

ጥንፍ የጥንፍፍ ልጅ ባባቱም በናቱ፣
ውልውልም የለው መድሓኒትነቱ፣
እንዴት ናት ወላጁ እንዴት ናት እናቱ፣
የኑር ማኖሪያቱ የኑር ሱንዱቂቱ፣
ያለችው ሴቶቹን አትወልዱም እንደኔ።
አሏሁመሶሊ………ሲሉ ሰሊውን ያቀብላሉ።
ኣሺቁም በህበረት ይቀበላል።

ባንድነት የተዋበ፣ባብሮነት ጣምራ የተጌጠ የፍቅር ዜማ ይንቆረቆራል።ቅጥሩ ዳግም ይጀድዳል።
ሳር ቅጠሉም በመደድ ይገባል።ትዕይንቱ ልባችንን በፍቅር ይሞላዋል።ያኔ የተጋትነውን ፍቅር በሩሓችን አፀድ ላይ ነግሷል።እናም ከዚህ ወዲያ ፍቅር የታለ ያስብለናል!❤️

BY ባህረል ሙገ(غ)የባ (የሳዳቶች ስርፋ)


Share with your friend now:
tgoop.com/Duzzl/2604

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

In 2018, Telegram’s audience reached 200 million people, with 500,000 new users joining the messenger every day. It was launched for iOS on 14 August 2013 and Android on 20 October 2013. The SUCK Channel on Telegram, with a message saying some content has been removed by the police. Photo: Telegram screenshot. Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN. On June 7, Perekopsky met with Brazilian President Jair Bolsonaro, an avid user of the platform. According to the firm's VP, the main subject of the meeting was "freedom of expression." Click “Save” ;
from us


Telegram ባህረል ሙገ(غ)የባ (የሳዳቶች ስርፋ)
FROM American