EAAARESPONSE Telegram 181
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ ፣ በጣም አዛኝ በሆነው።

╔───────◎ - ◎───────╗
   የሥነ-ሐዲስ ጥናት (Hadith terminology)
╚───────◎ - ◎───────╝

‹ሐዲስ› ማለት ‹ትርክት› ወይም ‹የነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) ቅዱስ ንግግር› ሲሆን የነቢዩ ‹ሰሓቦች "ባልደረቦች/companions"› ፣ ‹ታቢዒዮች "ተከታዮች/adherents"› እና የታቢዒይ ታቢዒዮች የዘገቡልን ነው።
ምሑራኖቻችንም ከጥንት ጀምሮ የአንድ ‹ሙሐዲስ "ተራኪ/narrator"› ትርክት ሲተላለፍላቸው የሱን ‹መትን "ይዞታል/content"› እና ‹ኢስናድ "ዘገባ/narration"› ከነ ዘጋቢው ጭምር ‹አስ-ሲሐህ "ታእማኒነቱ/authentication"› ለማረጋገጥ እንድንችለና ሐዲሱን ‹ሰሒሕ "በጣም ትክክለኛ/authentic"› ብለን ለመቀበል ሕጎችንና መርሆችን አፅድቀዋል፡፡


🎯 የእያንዳንዱ ተራኪ ዳራ ለማወቅ ምሑራኖች -

➲ የዑስታዞቹን ምስክርነት፤
➲ የተማሪዎቹን ምስክርነት፤
➲ የባልደረቦቹን ምስክርነት እንዲሁም፤
➲ ‹‹ዒልሙር-ሪጃል›› የሚባል ስለ እያንዳንዱ ተራኪ ማንነት የሚቋጭ ሰፊ ጥናትና ምርመራ ይደረጋል።


🎯 ማንነቱም ከታወቀ በኃላ ሐዲሱ ሰሒሕ ለመባል ተራኪው -

➊ ‹‹አድል››:- ታማኝ ሰው መሆን አለበት፤
➋ ‹‹ደብጥ››:- የማስታወስ ችሎታው ከጽሑፍ ጋር፤
➌ ‹‹ሙተሲል››:- ትረካውን የተቀበለበት አያያዥ ማንነት፤
➍ ‹‹ሰነድ››:- የሐዲሱ ተራኪዎች ስም/ሰንሰለት ያልተቋረጠ፤
➎ ‹‹ሻዘህ››:- እነዚህን አራት መስፈርት አልፎ ከቀደመው ዘገባ ጋር ምንም አይነት የሐሳብ ወይም የትርጉም ግጭት እና ፍጭት ሊኖርበት አይገባም።


🎯 የሐዲስ ዓይነቶች -

⓵ «ኣሓድ(ነጠላ)»:- በሦስት ሰዎች ወይም ከዚያ በታች የተዘገበ ሐዲስ ሲሆን በሶስት ይከፈላል-
‹‹ገሪብ››:- በአንድ ሰው ብቻ የተዘገበ።
‹‹ዐዚዝ››:- በሁለት ሰዎች ብቻ የተዘበ።
‹‹መሽሁር››:- በሶስት ሰዎች የተዘገበ።

⓶ «ሙተዋቲር(ተከታታይ)»:- በአራት እና ከዚያ በላይ ሰዎች የተዘገበ ሐዲስ ነው።


🎯 የሐዲስ ይዘት -

⓵ , «መቅቡል(ተቀባይነት ያለው)»
‹‹ሰሒህ እና ሐሰን››

⓶, «መርዱድ(ተቀባይነት የሌለው)»
‹‹ዷዒፍ እና መውዱዕ››
‹‹ዷዒፍ››:- ደካማ ሲባል ሙንቀጢዕ ፣ ሙድጠሪብ ፣ ሙዕዲል ፣ መጅሁል ፣ ሙንከር ፣ ሙርሰል ፣ ሻዝ ሲሆኑ ኢንሻአላህ ከታች በምሳሌ አንድ በአንድ እንመለከታቸዋለን...


ለምሳሌ አንድ ሐዲስ -

ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ ፤ 570-633 CE)

➊, ለዐሊይ (ረ.ዐ ፣ 601-661CE)

➋, 👤 (640-741 CE)

➌, 👤 (712-795 CE)

➍, 👤 (772-847 CE)

➎, ለቡኻሪይ (ረ.ላ ፤ 810-870 CE)


☞ ከላይ በተቀመጠው መልኩ ሰንሰለቱ የተሟላ ሆኖ ከተላለፈን ሐዲሱ ‹‹ሰሒሕ(በጣም ትክክለኛ)›› ይባላል፨

☞ ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) በሰንሰለቱ ውስጥ ከሌለ ‹‹መውቁፍ(የቆመ)›› ይባላል፨

☞ ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) እና 1ኛው(ባልደረባው) በሰንሰለቱ ውስጥ ከሌሉ ‹‹መቅጡዕ (የተቆረጠ)›› ይባላል፨

☞ 1ኛው ብቻ ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ሙርሰል›› ይባላል፨

☞ 2ኛው ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ዷዒፍ(ደካማ)›› ወይም ‹‹ሙዐለቅ(የተንጠለጠለ)›› ይባላል፨

☞ 3ኛው ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ሙንቀጢዕ(የቋዋረጠ)›› ወይም ‹‹ሙዐለቅ(የተንጠለጠለ)›› ይባላል፨

☞ 4ኛው ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ሙዐለቅ(የተንጠለጠለ)›› ይባላል፨

☞ ሁለት ወይም ከዛ በላይ ከሰንሰለቱ ከተቋረጡ ‹‹ሙዕዲል(የተምታታ)›› ይባላል፨

☞ ከአምስቱ አንዳቸው የማስታወስ ችሎታው ደካማ ከሆነ ‹‹ዷዒፍ(ደካማ)›› ይሆናል፨

☞ ከአምስቱ አንዳቸው ሐሰተኛ ከሆነ ‹‹መክዙብ(የተቀጠፈ)›› ወይም ‹‹መውዱዕ(መሰረተ-ቢስ)›› ይሆናል፨

☞ ከአምስቱ አንዳቸው ማንነቱ የማይታወቅ ከሆነ ‹‹መጅሁል(ማይታወቅ)›› ይሆናል፨

☞ በአንዱ ሐዲስ ሰንሰለት ደካማ(ቶሎ የሚረሳ) ተራኪ ኖሮ በሌላ ሐዲስ ሰንሰለትም ላይ ሌላ ደካማ ተራኪ ካለ ግን ሁለቱም ያስተላለፉት ሐዲስ ይዘቱ አንድ ከሆነ(ከተደጋገፉ) ‹‹ሐሰን(መለስተኛ ትክክለኛ)›› ይሆናል፨

☞ 1ኛው ዘጋቢ ለሦስት ተማሪዎች አስተምሮ ሁለቱ በአንድ ቃል ተስማምተው ሶስተኛው ግን ለብቻው ከተለየ የሶስተኛው ሐዲስ ‹‹ሻዝ(ኢ-መደበኛ)›› ይሆናል፨

☞ ሻዝ የሆነውን ሐዲስ ያስተላለፈው ዘጋቢ ኃሳዌ ሆኖ ከተገኘ ‹‹ሙንከር(ተቀባይነት የሌለው)›› ይሆናል፨


ወሠላሙ ዐለይኩም...

Telegram  channel ~>  https://www.tgoop.com/EAAAresponse
Telegram group ~> https://www.tgoop.com/A3E1response

Facebook ~>  https://www.facebook.com/Ethiomuslimallegationhunters/



tgoop.com/EAAAresponse/181
Create:
Last Update:

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ ፣ በጣም አዛኝ በሆነው።

╔───────◎ - ◎───────╗
   የሥነ-ሐዲስ ጥናት (Hadith terminology)
╚───────◎ - ◎───────╝

‹ሐዲስ› ማለት ‹ትርክት› ወይም ‹የነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) ቅዱስ ንግግር› ሲሆን የነቢዩ ‹ሰሓቦች "ባልደረቦች/companions"› ፣ ‹ታቢዒዮች "ተከታዮች/adherents"› እና የታቢዒይ ታቢዒዮች የዘገቡልን ነው።
ምሑራኖቻችንም ከጥንት ጀምሮ የአንድ ‹ሙሐዲስ "ተራኪ/narrator"› ትርክት ሲተላለፍላቸው የሱን ‹መትን "ይዞታል/content"› እና ‹ኢስናድ "ዘገባ/narration"› ከነ ዘጋቢው ጭምር ‹አስ-ሲሐህ "ታእማኒነቱ/authentication"› ለማረጋገጥ እንድንችለና ሐዲሱን ‹ሰሒሕ "በጣም ትክክለኛ/authentic"› ብለን ለመቀበል ሕጎችንና መርሆችን አፅድቀዋል፡፡


🎯 የእያንዳንዱ ተራኪ ዳራ ለማወቅ ምሑራኖች -

➲ የዑስታዞቹን ምስክርነት፤
➲ የተማሪዎቹን ምስክርነት፤
➲ የባልደረቦቹን ምስክርነት እንዲሁም፤
➲ ‹‹ዒልሙር-ሪጃል›› የሚባል ስለ እያንዳንዱ ተራኪ ማንነት የሚቋጭ ሰፊ ጥናትና ምርመራ ይደረጋል።


🎯 ማንነቱም ከታወቀ በኃላ ሐዲሱ ሰሒሕ ለመባል ተራኪው -

➊ ‹‹አድል››:- ታማኝ ሰው መሆን አለበት፤
➋ ‹‹ደብጥ››:- የማስታወስ ችሎታው ከጽሑፍ ጋር፤
➌ ‹‹ሙተሲል››:- ትረካውን የተቀበለበት አያያዥ ማንነት፤
➍ ‹‹ሰነድ››:- የሐዲሱ ተራኪዎች ስም/ሰንሰለት ያልተቋረጠ፤
➎ ‹‹ሻዘህ››:- እነዚህን አራት መስፈርት አልፎ ከቀደመው ዘገባ ጋር ምንም አይነት የሐሳብ ወይም የትርጉም ግጭት እና ፍጭት ሊኖርበት አይገባም።


🎯 የሐዲስ ዓይነቶች -

⓵ «ኣሓድ(ነጠላ)»:- በሦስት ሰዎች ወይም ከዚያ በታች የተዘገበ ሐዲስ ሲሆን በሶስት ይከፈላል-
‹‹ገሪብ››:- በአንድ ሰው ብቻ የተዘገበ።
‹‹ዐዚዝ››:- በሁለት ሰዎች ብቻ የተዘበ።
‹‹መሽሁር››:- በሶስት ሰዎች የተዘገበ።

⓶ «ሙተዋቲር(ተከታታይ)»:- በአራት እና ከዚያ በላይ ሰዎች የተዘገበ ሐዲስ ነው።


🎯 የሐዲስ ይዘት -

⓵ , «መቅቡል(ተቀባይነት ያለው)»
‹‹ሰሒህ እና ሐሰን››

⓶, «መርዱድ(ተቀባይነት የሌለው)»
‹‹ዷዒፍ እና መውዱዕ››
‹‹ዷዒፍ››:- ደካማ ሲባል ሙንቀጢዕ ፣ ሙድጠሪብ ፣ ሙዕዲል ፣ መጅሁል ፣ ሙንከር ፣ ሙርሰል ፣ ሻዝ ሲሆኑ ኢንሻአላህ ከታች በምሳሌ አንድ በአንድ እንመለከታቸዋለን...


ለምሳሌ አንድ ሐዲስ -

ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ ፤ 570-633 CE)

➊, ለዐሊይ (ረ.ዐ ፣ 601-661CE)

➋, 👤 (640-741 CE)

➌, 👤 (712-795 CE)

➍, 👤 (772-847 CE)

➎, ለቡኻሪይ (ረ.ላ ፤ 810-870 CE)


☞ ከላይ በተቀመጠው መልኩ ሰንሰለቱ የተሟላ ሆኖ ከተላለፈን ሐዲሱ ‹‹ሰሒሕ(በጣም ትክክለኛ)›› ይባላል፨

☞ ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) በሰንሰለቱ ውስጥ ከሌለ ‹‹መውቁፍ(የቆመ)›› ይባላል፨

☞ ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) እና 1ኛው(ባልደረባው) በሰንሰለቱ ውስጥ ከሌሉ ‹‹መቅጡዕ (የተቆረጠ)›› ይባላል፨

☞ 1ኛው ብቻ ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ሙርሰል›› ይባላል፨

☞ 2ኛው ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ዷዒፍ(ደካማ)›› ወይም ‹‹ሙዐለቅ(የተንጠለጠለ)›› ይባላል፨

☞ 3ኛው ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ሙንቀጢዕ(የቋዋረጠ)›› ወይም ‹‹ሙዐለቅ(የተንጠለጠለ)›› ይባላል፨

☞ 4ኛው ከሰንሰለቱ ከተቋረጠ ‹‹ሙዐለቅ(የተንጠለጠለ)›› ይባላል፨

☞ ሁለት ወይም ከዛ በላይ ከሰንሰለቱ ከተቋረጡ ‹‹ሙዕዲል(የተምታታ)›› ይባላል፨

☞ ከአምስቱ አንዳቸው የማስታወስ ችሎታው ደካማ ከሆነ ‹‹ዷዒፍ(ደካማ)›› ይሆናል፨

☞ ከአምስቱ አንዳቸው ሐሰተኛ ከሆነ ‹‹መክዙብ(የተቀጠፈ)›› ወይም ‹‹መውዱዕ(መሰረተ-ቢስ)›› ይሆናል፨

☞ ከአምስቱ አንዳቸው ማንነቱ የማይታወቅ ከሆነ ‹‹መጅሁል(ማይታወቅ)›› ይሆናል፨

☞ በአንዱ ሐዲስ ሰንሰለት ደካማ(ቶሎ የሚረሳ) ተራኪ ኖሮ በሌላ ሐዲስ ሰንሰለትም ላይ ሌላ ደካማ ተራኪ ካለ ግን ሁለቱም ያስተላለፉት ሐዲስ ይዘቱ አንድ ከሆነ(ከተደጋገፉ) ‹‹ሐሰን(መለስተኛ ትክክለኛ)›› ይሆናል፨

☞ 1ኛው ዘጋቢ ለሦስት ተማሪዎች አስተምሮ ሁለቱ በአንድ ቃል ተስማምተው ሶስተኛው ግን ለብቻው ከተለየ የሶስተኛው ሐዲስ ‹‹ሻዝ(ኢ-መደበኛ)›› ይሆናል፨

☞ ሻዝ የሆነውን ሐዲስ ያስተላለፈው ዘጋቢ ኃሳዌ ሆኖ ከተገኘ ‹‹ሙንከር(ተቀባይነት የሌለው)›› ይሆናል፨


ወሠላሙ ዐለይኩም...

Telegram  channel ~>  https://www.tgoop.com/EAAAresponse
Telegram group ~> https://www.tgoop.com/A3E1response

Facebook ~>  https://www.facebook.com/Ethiomuslimallegationhunters/

BY E͜͡t͜͡h͜͡i͜͡o͜͡ M͜͡. A͜͡l͜͡l͜͡e͜͡g͜͡a͜͡t͜͡i͜͡o͜͡n͜͡ H͜͡u͜͡n͜͡t͜͡e͜͡r͜͡s͜͡

❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Share with your friend now:
tgoop.com/EAAAresponse/181

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Hashtags Select “New Channel” According to media reports, the privacy watchdog was considering “blacklisting” some online platforms that have repeatedly posted doxxing information, with sources saying most messages were shared on Telegram. It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart. Find your optimal posting schedule and stick to it. The peak posting times include 8 am, 6 pm, and 8 pm on social media. Try to publish serious stuff in the morning and leave less demanding content later in the day.
from us


Telegram E͜͡t͜͡h͜͡i͜͡o͜͡ M͜͡. A͜͡l͜͡l͜͡e͜͡g͜͡a͜͡t͜͡i͜͡o͜͡n͜͡ H͜͡u͜͡n͜͡t͜͡e͜͡r͜͡s͜͡
FROM American