tgoop.com/ETCONpWORK/1787
Last Update:
በድጋሚ የወጣ የአጥር ስራ ጨረታ ማስታወቂያ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ክልል ውስጥ የአስኮ 40/60 የጋራ ህንፃ ባለቤቶች ኃ/የተ/ህብረት ስራ ማህበር ለአጥር ግንባታው አስፈላጊ የሆኑትን ግብዓቶች በማቅረብ የጉልበት ዋጋን በጨረታ የኮንዶሚኒየሙን ዙሪያ አጥር ለማሳጠር ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት በጨረታ መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የዘመኑን ግብር የከፈለ፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆነ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin No) ማስረጃ የሚያቀርብ መሆን ይኖርበታል።
2ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉት በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው ሆነው ደረጃ ስምንት እና ከዛ በላይ መሆን አለባቸው።
ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /CPO/ ብር 10,000.00 ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጉልበት ዋጋ ለስራው የሚያስፈልጉትን ማሽነሪዎችና መሳሪያዎች ያካተተ መሆን ይኖርበታል።
ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ አስኮ 40/60 ሳይት ብሎክ 3 አንደኛ ፎቅ ካለው የማሀበሩ ፅ/ቤት የማይመለስ ብር 400.00 በማህበሩ የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000366344547 ገቢ በማድረግ የባንክ ደረሰኙን ይዞ በመቅረብ መግዛት ይችላል።
ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በመሙላት የጨረታ መመሪያ በሚያዘው የፋይናንሻልና ቴክኒካል ፕሮፖዛላችሁን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው ከወጣበት ግዜ አንስቶ በ15 ቀን ጊዜ ውስጥ በማህበሩ ፅ/ቤት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ ህጋዊ ማህተም እና ፊርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ህጋዊ ማሀተም የሌለው ሰነድ ከውድድር ውጭ ይደረጋል።
ተጫራቾች የቦታውን ጠቅላላ ሁኔታ በሳይቱ ላይ በአካል በስራ ሰዓት በመገኘት መመልከት ይችላሉ።
ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በተዘጋ በነጋታው ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ይከፈታል።
ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማብራሪያ፡- በስልከ ቁጥር-0974-99 93 94/0911_83-38-28 ወይም የማህበሩ ጽ/ቤት ቢሮ በአካል በመቅረብ መጠየቅ ይቻላል።
የአስኮ 40/60 የጋራ ህንፃ ባለቤቶች ኃ/የተ/ህብረት ስራ ማህበር
https://www.tgoop.com/ETCONpWORK
BY Ethio Con Work
Share with your friend now:
tgoop.com/ETCONpWORK/1787