tgoop.com/ETH724/26
Last Update:
አሸባሪው ህውሀት በፈንቲ ረሱ ጋሊኮማ ጭፍጨፋ ከፈጸመባቸው 240 ንጹሀን በተጨማሪ የሟቾች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ ተገለጸ
#Ethiopia : አሸባሪው የህውሀት ጁንታ ቡድን በፈንቲ ረሱ ዞን ጉሊና ወረዳ ጋሊኮማ ቀበሌ አሳፋሪና ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ከፈጸመባቸው 240 ንጹሀን አርብቶ አደሮች በተጨማሪ በየጊዜው ቁጥሩ እየጨመረ መምጣቱን የአፍር ክልል መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ አስታውቋል ፡፡
ከፈንቲ ረሱ ዞን አራት ወረዳዎች አውራ፣እዋ፣ያሎ እና ጉሊና ወረዳዎች ተፈናቅለው በጋሊኮማ ትምህርት ቤት እና ጤና ጣቢያ ተጠልለው በነበሩ ንጹሀን ህጻናት፣ሴቶች እና አዛውንቶች ላይ ጁንታው በአንድ ቀን በከባድ መሳሪያ የጨፈጨፋቸው እና የሞቱት 240 የደረሰ መሆኑ ይታወሳል ፡፡
በመሆኑም ጁንታው በየጫካው በከብት እረኝነት የነበሩትንም ሆነ በየቦታው ያገኘውን ንጹሀን የጨፈጨፈ በመሆኑ እና እንዲሁም በጊዜው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ህይወታቸው በማለፉ ምክንያት የሟቾች ቁጥር መጨመሩን የአፋር ክልል መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡
የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ቢላይ አህመድ በጋሊኮማ ንጹሀን አርብቶ አደሮች ህጻናት፣ሴቶች እና አዛውንቶች ላይ ዘራፊው እና አሸባሪው ጁንታው ከዚህ በፊት ከተጠቀሰው 240 ንጹሀን ሞት በተጨማሪ ሌሎች አስክሬኖች እየተገኙ በመሆናቸው የሟችች ቁጥሩ መጨመሩን እና እንዲሁም እስካሁን ይሙቱ ይዳኑ የማይታወቅ የጠፉ ንጹሀን አርብቶ አደሮችም መኖራቸውን ገልጸዋል ፡፡
የቴሩ ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ከዲጋ ያሲን በበኩላቸው በንጹሀኑ አርብቶ አደር ማህበረሰብ ህጻናት፣ሴቶች እና አዛውንቶች ላይ ጁንታው ያደረሰው ጭፍጨፋ ዘግናኝ መሆኑን በመግለጽ እስካሁን አስክሬናቸው ያልተገኙ መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡
@ETH724
@ETH724
BY ኢትዮ 7/24 መረጃ
Share with your friend now:
tgoop.com/ETH724/26