Telegram Web
أصبحنا واصبح المُلك لله
اللهم اعطنا من الخير فوق ما نرجوا وأصرف عنّا السوء فوق ما نحذر اللهم اسكن دواخلنا طمأنينة من لدنك لا تفنى ولا تزول
صباح الخير 🌞

     
እውነተኛ ልቦች የባህር ጥልቀት የሚያክል ርቀት እርስ በርስ ቢኖራቸውም አላህ ያገናኛቸዋል!
#semir ami
.
ሽማግሌው የከተማ አውቶብስ መጠበቂያ ስፍራ ቆመው አውቶብስ እየጠበቁ ነው። አከባቢው እንደሳቸው ሁሉ አውቶብስ የሚጠብቀውና በወጪ ወራጅ መንገደኛው ተጨናንቋል።
በይኽ መሃል በኪሳቸው ያለው ተንቀሳቃሽ ስልካቸው (ሞባይላቸው) መጮህ ጀመረ። ጥሪ ነበር። ሽማግሌው የስልካቸውን ጥሪ ቢሰሙትም በይኽ ግር ግር መኻል ስልክ ቢያነጋግሩ የቀማኞች ሲሳይ መሆናቸው ስለገባቸው ዝም አሉ።
የ "ሞባይሉ"ን ድምፅ የሰማው አንድ ጩሉሌ ሌባ ከኃላቸው አድፍጦ ሽማግሌው ስልካቸውን ከወሸቁበት ሲያወጡ መንትፎ ለመሮጥ ቋምጧል።
ሽማግሌው ግን የዋዛ አልነበሩም። ስልኩ ይጮኻል እሳቸው ግን እንኳንስ አውጥተው ሃሎ ሊሉ ድንግጥም አላሉ።
ይሄኔ ሌባው ወደ ሽማግሌው ብሎ " አባቴ ስልክዎ እየጮኸ ነው እኮ ያንሱት እንጂ"አላቸው። ውስጠ ዘ ው (ምስጢሩ) የገባቸው ጠንቃቃው ሽማግሌ ተወው ልጄ እኔ ኃላ ከምጮህ እሱ አሁን ይጩኽ "አሉት።

@Ekramcalligraphy

Semir ami
አንዳንድ በሰወች ልቦና ውስጥ መልካም ነገርን ዘርተው የሚሄዱ አሉ ያምንም ቅድመ ሁኔታወች..

ምስጋናም ጥቅምም አይፈልጉም
የጌታን ስጧታ ይበልጥ ስለሚወዱ ነው..

እነዛ ምነኛ አማሩ!
እናንተን መለየት የፈለገ ከበሩ ሽንቁር ላይ መሄጃ ይመለከታል እናንተን መቅረብ የፈለገ በግድግዳው ላይ መግቢያ በር ይሰራል!
ከሙሉነት ጥቂቱን...
:
#ዝቅ_ያሉትን_አንሺ
መንገድ ላይ የምናገኘውን ሚስኪን የመገላገል አይነት ሳንቲም ወርውረን የምንሄድ እኛ... አሏህ ይስጥልን ለማለት ምላሳችን የሚፈጥንብን እኛ... ለሐብታም አሸርጋጅ፣ ድሐን አንቋሻሽ የሆንነው እኛ... ሰደቃ ብለን የገዛ ሐብታም ዘመዶቻችንን ብቻ እየጠራን ሰደቅን የምንል እኛ እውነት እናስተዛዝባለን ኮ!!
አስተማሪውማ የነገሩንና ሰርተው ያሳዩን ሌላ ነበር...አንዴ ወደ መስጂድ ሲገቡ ችግረኞች በአንድ ጎን ተቀምጠው አዩ። ከነሱ ጋር ተቀመጡና ከእነሱው ጋር መሳሳቅና ማውራት ያዙ፤ ከዚያም ይህን ተናገሩ:<ለስደተኛ ድሆች መልካም አቀራረብ ይኑራችሁ። እነሱ ከሐብታሞች አርባ አመት ቀድመው ነው ጀነት የሚገቡት። ምክንያቱም ከገንዘብና ከንብረት ላይ የሚደረግ ምርመራ የለባቸውምና> አስከተሉና ይሄን ዱዐ አደረጉ: <አላህ ሆይ! ልክ እንደ ድሆች አኑረኝ። እንደነርሱም ግደለኝ። ከእነርሱ ጋርም ቀስቅሰኝ>
ይሄው ነው የኛው አስተምህሮ...ባንዱ ጆሮ ሰምተን በሌላው የማፍሰሳችን ነገር ግን እያየነው ያለበትን የሐብት ሽኩቻ ብሎም የችግረኞችን ጥላቻ አስከተለ። ነጃ ይበለን!!
ጠያቂን አትንፈግ ል አንተ ፀጋውስጥ ሰጥመህ
ለግስ ከፈን ኪስ የለውም ‼️
ህይወት የትግል መድረክ ናት…
ከፊሉ ይመራል ከፊሉ ይከተላል…
አንተ ለራስህ መሪ መሆን ካልቻልክ ለሌሎች ባሪያ አትሁን‼️
.
ሀያእ ከመልካም
ነገር ውጪ አያመጣም!
እንደ አባቶ አስከብራት
ካልሆነ ለአባቶ ተዋት
ምስል

አላህ ሲያድል መቼም ለጉድ ነው..!
የልቤን መሻት ሳላወጋው ካሰብሁት ይልቅ የሰጠኝ ገዘፈብኝ። እንዲሁ በቀናቶቼ መሃል ውል ይልብኛል ስለ ኒዕማው ሌት ተቀን አልሃምደሊላህ ያስብለኛል። ሴትነቴን ተቀብሎ እመቤቱ አደረገኝ፤ ከወንድም መራቅ አይጎልብኝ ዘንድ መከታ ሆነልኝ፤ ከእናት እቅፍ ሚማገው ፍቅር እንስፍስፍ በሚል ልቡ ያስረሳኛል፤ ብቸኝነት ይሉት ብርድ አይመታኝም፤ኧረ እንደውም ንፋሱ ከደጄ ካለፈ ስንት ዘመኑ፤ ቤተሰባዊነት እንጂ አንድ ወጥ የሆነ ሙሃባ አላሳየኝም... መቼም ጌትዬ ሲሰጥ አያልቅበት።

ያኔ በየ ማለዳው አባቴን ስሸኘው የነበረው ስስት ዛሬም በውዴው አየዋለሁ....ይኸዋ በመስኮቱ ብቅ ስል ከፊቱ የምትቀበለኝ ፀዳል ሁሉን ታስረሳኛለች።

ፈገግታው ያሞቃል እኔ ና ቤቴን...!

@ekramcalligraphy
Forwarded from Sarah Calligraphy via @like
🎁 Huda🎁

『 from A.A』

『code:A5』


@saracalligraphy
Like adergulgn 🙏🙏🙏
የህልም አለም

በህልም አለም ውስጥ ያለሁ እስኪመስል ድረስ ሁሉም ነገር ያስፈራል
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እየፈታቹ....


ከስር ያለውን የቴሌግራም ሊንክ
JOIN በማድረግ የጀመዐው አባል ይሁኑ
https://www.tgoop.com/thejubair00
Forwarded from سمير ايمي
ናስሩዲን ከተከታዮቹ ጋር በአጀብ ሆኖ በአንድ የገበያ ስፍራ ያልፋል። ምንም ነገር ቢያደርግ ተከታዮቹ የሚያደርገውን ይደግማሉ። ጥቂት ራመድ ይልና እጆቹን ሰቅሎ ይወዘውዛል፣ ዝቅ ብሎ እግሮቹን ይነካል፣ ወደላይ እየዘለለም ይጮሃል። ተከታዮቹም እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ሳያዛቡ ይደግማሉ።

🔆ታዲያ አንድ ነጋዴ ወዳጁ " ምን እያደረክ ነው የዱሮ ጓዴ? እነዚህ ሰዎችስ ለምንድነው የምታደርገውን የሚያስመስሉት? " በሚል ይጠይቀዋል

"ታላቅ ሼክ ሆንኩ እኮ! እነዚህ ደግሞ መንፈሳዊነትን ለመለማመድ የተከተሉኝ ተማሪዎቼ ናቸው ። ወደ መንፈሳዊ አብርሆት ይሸጋገሩ ዘንድ እየረዳኋቸው ነው። " ናስሩዲን መለሰ።
ወዳጁ ግራ ተጋብቶ ጠየቀ። "አሃ! አብርሆት [Enlightenment] ላይ መድረሳቸውን በምን ታውቃለህ?

🔆ናስሩዲንም " ያ ቀላል ነው። በየማለዳው ተከታዮቼን እቆጥራቸዋለሁ። ከሰልፉ የጎደሉት በርቶላቸዋል ማለት ነው!"

P.S: የናስሩዲን አይነት አሰላፊዎች ሞልተውናል። አሰላፊዎቹ የስሜት ህዋስህን በገዛ አንጎላቸው ያዙታል። ምናለፋህ your conformist being is a humble robot for them.

📍ባላበጀኸውና ባልፈተሽከው ሃሳብ ላይ ተለጥፎ ሰልፍ ውስጥ ራስህን ካገኘኸው "ዘናጭ በግ" ሆነህ ሰዎችን ተከትለህ አትትመም!

ከሰልፉ ጉደል !
ተነጠል፣ መፃፍት ግለጥ ፣ ሃሳብ ፈትሽ፣ ሐሳብ አመንጭ።!

ውብ አሁን

@semiraklu
የሰው ልጅ የክብር ጉዞ የኔና ያንተ ክብር ነው፤ የሰው ልጅ የውርደት እሽቁልቁሊት
የኔና ያንተ ውርደት ነው። ከመኪና እያወረዱ የረሸኑን እኔና አንተን ነው፤ ረሻኞችም
እኛው ነን።
በወለጋ የተጨፈጨፍነው እኔና አንተ ነን፤ ጨፍጫፊዎቹም እኛው ነን።
የትም ቦታ የሚደርስ ኢሰብአዊነት ከሰውነት ተርታ የሚያስወጣን እኛኑ ነው።
ከሰውነት ክብር መውረድ ማለት ወደ እንስሳነት ደረጃ ዝቅ ማለት ነው።
እንስሳነት ሲያይል በንፁሃን ደም የሚፎክርና ነውሩ ክብሩ የሆነ ሰው
በማህበረሰብ ውስጥ ይበቅላል።
ወንድሜ፣
"ማን ተገደለ?" ብለህ አትጠይቅ፤ የሞትነው እኔና አንተ ነን። "ማን ገደለ?"
ብለህም አትጠይቅ፤ የጨፈጨፍነው እኔና አንተ ነን። "ማን ያስቁመው?" ካልከኝ
ራሱን "ሰው" ብሎ የሚጠራ ማንኛውም ሰው ሁሉ እልሃለሁ። ፖለቲከኞች፣
የሃይማኖት አባቶች፣ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች...
አላህ ሆይ! በቃ በለን! የእውነት "ሰው" እንሆን ዘንድ እርዳን።
አስታዝ በድሩ ሁሴን
ከሙሉነት ጥቂቱን...6
(Team Huda)
:
#የእንስት_ጠበቃ

ጃሂል መሆን እዳ ነው መቼስ... ሴት ልጅ መወለዷን ሲያውቅ ንዴት የሚንጠው፣ መዋረድ የሚያዋልለውን አባት ፈጥሯል። የሴት መብት ሳይሆን "ሴት" የምትባል ፍጡር ራሷ ተዘንጊ... እያለችም የተረሳች...በምንም አይነት የውርስም ይሁን ሌሎች ህጋዊ ጉዳዮች ላይ የማትሳተፍ...የሆነ የቤቱ አንድ ጥግ ላይ እንደተቀመጠ የቤት እቃ የምትቆጠር...ሰብዐዊ መብት ይሉትን ያልተከናነበች ነበረች።

ታዲያ የኛ የብይ ሲመጡ ከስር መሰረቱ ጅህልናን ገረሰሱ...ኢቅራዕ ነዋ የጅህልና ጠላት!
ካለችበት መቃብር እፍ እፍ ብለው አፈሯን አራገፉ። እናትነት ብሎም ሴትነት ከተጣለበት ሁሉ ተሰባስቦ ራሱን ችሎ እንዲቆም ሆነ። የእናት ደረጃ በእውኑም በመጪውም ተነገረ፣ ተገለጠም። "ጀነት ከእናት እግር ስር ናት" ይሉትን አስተምህሮ ዘረጉ። ሴትን ማክበርም ብቻም ሳይሆን ተናናሽ እንዲሆንላት ሆነ። በሳቸው የተደረገው በማን ታየ?

በአንድ ጉዞ ላይ አንጃሻህ የሚባል ባሪያ እያንጎራጎረ ነበር። በእንጉርጉሮው ሰበብ ሴቶቹን የተሸከሙት ግመሎች መደንበር አመጡ። ይህን የተመለከቱት አዛኝ ነብይ ምን አሉ?
<<አንጃሽህ ሆይ እንቁወቹን አደራ፣ እንቁወቹን አደራ>>በማለት ነገሩት ።ረሱለሏህ ለምድር ሲላኩ ሴትነት እንቁነት... ጀነትነት ሆነ!



@huda_islamic_channel
በጁመዓ ንጋት ላይ

ያረብ በልባችን ውስጥ ደስታን ዝራ ምኞታችንና ህልሞቻችን አሳክተህ!
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አስርቱ የዙልሒጃ ቀናት-
ኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ

ነሲሓ ቲቪ...
ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!!
ነሲሓ ቲቪ / Nesiha Tv
2025/07/05 07:16:31
Back to Top
HTML Embed Code: