ELIASGEBRU Telegram 575
ከልብ የተሰጠ ሥጦታ በብር አይተመንም።
በቅርቡ የማላውቀው የቤት ስልክ ቁጥት ሞባይሌ ላይ ደወለ__ አነሳሁት፣
"ሄሎ"
"ሄሎ፣ ዶ/ር ኤልያስ ነህ?"
"አዎን ማን ልበል?"
"ከቃሊቲ እስር ቤት ነው የምደውልልህ!.."
"እሺ"
"... ግን የአርምሞ መጽሐፍ ደራሲው ዶ/ር ኤልያስ ነህ አይደል?"
በውስጤ ቃሊቲ ማረምያ ቤት ደሞ ለምን ፈለጉኝ እያልኩኝ፣ "አዎ እኔ ነኝ" አልኹት፤
"እግዚአብሔር ይመስገን፣ በጣም አክባሪክ ነኝ፣ በድምፅም ቢሆን ስላገኘሁ በጣም ደስ ብሎኛል!" ... ሲለኝ ደዋዩ መጽሐፌን አንብቦ እንደሆነ ገመትኩኝ።
"አመሰግናለሁ ወንድሜ፣ አንተንስ ማን ልበል?" ስል ጠየቅኩት፤
"ሙሉጌታ እባላለሁ፣ በቃሊቲ እስር ቤት ለአመታት ያቆየሁ ታራሚ ነኝ ፤ አርምሞ መጽሐፍህ ውስጤ ላይ ትልቅ ተስፋን ስላበራልኝ ነው ላመሰግንህ የደወልኩት... ያው ታራሚ ነኝ፣ ምንም ላንተ የማደርግልህ ነገር የለም...  የገንዘብም አቅም የለኝም ግን ድሮ የለመድኳት የእጅ ጥበብ አለች፤  በሷ አንድ ብእር በእጆቼ ሰርቼልሃለሁ፣ በቅርቡ ይደርስሃል" አለኝ።
(ከዚያም ከመጽሐፉ ጋር የተያያዙ ብዙ ጨዋታዎችን ተጫወትን)

እውነት ለመናገር ስጋው እንጂ ነፍሱ ያልታሰረች አስተዋይ ሰው ነው። ያው የላከው መልእክተኛም ይሄንን የሚያምር ብእር ከደብዳቤ ጋር ቢሮ ለፀሐፊያችን አቀበላት። በህይወቴ ሰዎች ከሰጡኝ ትልቅ ስጦታዎች አንዱ ነው።
የሥጦታ ውዱ ከልብ የተሰጠ ነው።

(ደራሲ፣ ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አእምሮ)

@EliasGebru



tgoop.com/EliasGebru/575
Create:
Last Update:

ከልብ የተሰጠ ሥጦታ በብር አይተመንም።
በቅርቡ የማላውቀው የቤት ስልክ ቁጥት ሞባይሌ ላይ ደወለ__ አነሳሁት፣
"ሄሎ"
"ሄሎ፣ ዶ/ር ኤልያስ ነህ?"
"አዎን ማን ልበል?"
"ከቃሊቲ እስር ቤት ነው የምደውልልህ!.."
"እሺ"
"... ግን የአርምሞ መጽሐፍ ደራሲው ዶ/ር ኤልያስ ነህ አይደል?"
በውስጤ ቃሊቲ ማረምያ ቤት ደሞ ለምን ፈለጉኝ እያልኩኝ፣ "አዎ እኔ ነኝ" አልኹት፤
"እግዚአብሔር ይመስገን፣ በጣም አክባሪክ ነኝ፣ በድምፅም ቢሆን ስላገኘሁ በጣም ደስ ብሎኛል!" ... ሲለኝ ደዋዩ መጽሐፌን አንብቦ እንደሆነ ገመትኩኝ።
"አመሰግናለሁ ወንድሜ፣ አንተንስ ማን ልበል?" ስል ጠየቅኩት፤
"ሙሉጌታ እባላለሁ፣ በቃሊቲ እስር ቤት ለአመታት ያቆየሁ ታራሚ ነኝ ፤ አርምሞ መጽሐፍህ ውስጤ ላይ ትልቅ ተስፋን ስላበራልኝ ነው ላመሰግንህ የደወልኩት... ያው ታራሚ ነኝ፣ ምንም ላንተ የማደርግልህ ነገር የለም...  የገንዘብም አቅም የለኝም ግን ድሮ የለመድኳት የእጅ ጥበብ አለች፤  በሷ አንድ ብእር በእጆቼ ሰርቼልሃለሁ፣ በቅርቡ ይደርስሃል" አለኝ።
(ከዚያም ከመጽሐፉ ጋር የተያያዙ ብዙ ጨዋታዎችን ተጫወትን)

እውነት ለመናገር ስጋው እንጂ ነፍሱ ያልታሰረች አስተዋይ ሰው ነው። ያው የላከው መልእክተኛም ይሄንን የሚያምር ብእር ከደብዳቤ ጋር ቢሮ ለፀሐፊያችን አቀበላት። በህይወቴ ሰዎች ከሰጡኝ ትልቅ ስጦታዎች አንዱ ነው።
የሥጦታ ውዱ ከልብ የተሰጠ ነው።

(ደራሲ፣ ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አእምሮ)

@EliasGebru

BY ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ ወጎች ግጥሞች እና ቁም ነገሮች




Share with your friend now:
tgoop.com/EliasGebru/575

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A vandalised bank during the 2019 protest. File photo: May James/HKFP. With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. Ng, who had pleaded not guilty to all charges, had been detained for more than 20 months. His channel was said to have contained around 120 messages and photos that incited others to vandalise pro-government shops and commit criminal damage targeting police stations. fire bomb molotov November 18 Dylan Hollingsworth yau ma tei
from us


Telegram ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ ወጎች ግጥሞች እና ቁም ነገሮች
FROM American