tgoop.com/Enatachn_mareyam/16442
Last Update:
†
[ 🕊 ፍኖተ ቅዱሳን 🕊 ]
[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትሕትና ! ]
------------------------------------------
❝ በአፉ ዐረፋ እስኪያስደፍቀው ድረስ ርኩስ መንፈስ ያደረበት አንድ ሰው አንድን መነኵሴ ፊቱን በጥፊ መታው፡፡ መነኵሴውም ሌላኛውን ፊቱን አዙሮ ሰጠው:: በዚህ ጊዜ ጋኔኑ የመነኲሴው ትሕትናው ስላቃጠለው ወዲያውኑ ከሰውዬው ወጥቶ ጠፋ፡፡ ❞
-------------------------------------------
❝ አጋንንት ለምን ይህን ያህል አጽንተው ይዋጉናል?" ብለው አንድን አረጋዊ ጠየቁት፡፡ እርሱም ፦ "መሣሪያዎቻችንን አሽቀንጥረን ስለ ጣልናቸው ነው ፤ መሣሪያዎቻችን ማለቴም ክብርን መናቅን ፣ ትሕትናን ፣ ድህነትንና ጽናትን ማለቴ ነው" አላቸው፡፡ ❞
--------------------------------------------
🕊
የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡
† † †
💖 🕊 💖
BY አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
Share with your friend now:
tgoop.com/Enatachn_mareyam/16442