Telegram Web
#አማኑኤል__ሆይ

#አቤቱ_ተወዳጅ_አማኑኤል_ሆይ
የምንኮራበት ክብራችን የምንደምቅበት አክሊላችን አንተ ነህ፤ ቀና ያልንብህ ትምክህታችን ያረፍንብህ ክንዳችን አንተ ነህ፤ እግራችን እንዳይሰናከል የምትጠብቀን እንዳንባዝን የምታረጋጋን አንተ ነህ፤

#አማኑኤል_ሆይ ፦ ፍቅርህን የሚመስለው የለም፡፡ እንዳንወድቅ የምትጠብቀን ብንወድቅ የምታነሳን አንተ ነህ፤ እንዳንደክም የምትራራልን ብንደክም የምታበረታን አንተ ነህ፤ እንዳንታመም ባንተ እንታመናለን ብንታመምም ስላንተ ተስፋ አለን፤

#አማኑኤል_ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? እንዳንሰናከል መላእክቱን ስለእኛ አዘጋጀልህን ጠላቶች እንደበዙብን አይተህ ወዳጆችን አበዛኅልን፤ ፈተናወቻችንን አይተህ መውጫውን ደግሞ አመላከትከን የቀደመውን ፍቅራችንን ብንቀንስ ያንተን ፍቅር አበዛህልን፤

#አማኑኤል_ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ራቅንህ አንተ ወደኛ ቀረብክ፤ በግብራችን ናቅንህ አንተ ግን እኛን አከበርክ፤ ያለአንተ መኖር እንደማንችል ታውቃለህና ክፋታችንን ሳታይ ራራህልን ስንፍናችንን ሳታይ ቀረብከን ፤

#አማኑኤል_ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ተወዳጅ ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ማንም የለንምና ክብራችንን አውቀን እንኖር ዘንድ አንተን ሳናስብ የምንውልበት ጊዜ አይኑረን፡፡
#ክብርና_ምስጋና_ላንተ_ይሁን🙏

      #_ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
7🙏2❤‍🔥1
                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]

         [      የመጨረሻ ክፍል     ]

                         🕊  

[     ስለ እግዚአብሔር ቃል መስማት !    ]

🕊

❝ አባ መቃርዮስ ታላቁ እንዲህ አለ ፦ “በጌታ ቃል ደስ የሚልህ መሆኑ መልካም ነው ፣ ቃሉን ስትሰማ ግን ለመስማት ብቻ ሳይሆን ለመታዘዝና ለማድረግ እንድትችል ሆነህ እንድትማር ሁን ፤ የእግዚአብሔርን ቃል በሙሉ ኃይሉ የሚሰማ ሰው ለማድረግም ይማራልና፡፡

ብዙዎች የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተዋል ፣ ሆኖም ግን በእግዚአብሔር ኃይልና በደስታ ሆነው አልሰሙትም ፤ ስለዚህም የሕይወት መሻሻልና ዕድገት አላመጡም፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደዚህ ስላሉት ሰዎች እንዲህ ሲል አሰምቶ ተናግሯል ፦ "የሚሰማ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ፡፡" ሁሉም መስማትን ባያቆሙ ኖሮ እንደዚህ ብሎ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ብሎ ደጋግሞ ባልተናገረ ነበር፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስ ሥራ ነፍሳት የእግዚአብሔርን ቃል እንዳይሰሙና ሰምተው እንዳይድኑ መዋጋት መሆኑን ያውቃልና፡፡ ስለዚህም ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ” አለ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰሙ ለውጥና ዕድገት ያሳያሉና ፣ በነፍስና በሥጋ ፈቃዳትና በፍትወታት ሁሉ ላይም ድል አድራጊዎች ናቸውና፡፡

“ ነገር ግን ዲያብሎስ ነፍስን የእግዚአብሔርን ቃል በኃይል ከመስማት ቢያስቆማት [ቢያግዳት] መሻሻልና ማደግ አትችልም ፣ የሰውነት ፈቃዳትንና ፍትወታትን ለመዋጋትም መንገድ አታገኝም ፤ የእግዚአብሔር ቃል በውስጧ አይኖርባትምና፡፡ ጠላት በእርሷ ላይ ኃይል ቢጠቀም ከክፉ ፍትወታትና ከእኩያት ሕሊናት አንዳቸውንም ከእርሷ ለማባረር የምትችልበት መንገዱ ይጠፋባታል፡፡

ቃሉን ገንዘብ ያደረገች ነፍስ ግን ፍትወታት እኩያትንና ክፉ ሕሊናትን ከእርሷ በማባረር ብርቱ ናት ፣ ጠላት ዲያብሎስንም ከእርሷ ታስወጣዋለች ፣ እርሱም ኃፍረትን ተከናንቦ ፈጥኖ ተለይቷት ይሸሻል ፤ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ፦ 'የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና ፣ የሚሠራም ሁለትም አፍ ካለው ሠይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው ፣ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል ፣ የልብንም ስሜትና ሃሳብ ይመረምራል፡፡'

“ሰው የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ከቻለ እንዴት ክፉ ሃሳቦችን መቋቋምና ማባረር እንደሚችል ማየት እንችላለን ፣ የማይሰማ ከሆነ ግን ነፍስ ምንም ዓይነት ክፉ ሃሳቦችን ሳታባርር እንደ እርሳስ ትሆናለች፡፡ ስለዚህም ዲያብሎስ እንደዚህ ዓይነት ሰዎችን ይሳለቅባቸዋል ፤ እንደዚህ ያሉ ሰዎች ሕይወታቸውን በሙሉ በገዳምና በድንግልና ያሳለፉ ቢሆኑም እንኳ በምንም ነገር መለወጥና ማደግ አይችሉም፡፡ ከማርና ከማር ወለላ ይልቅ እጅግ በጣም ጣፋጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ጣፋጭነት ጣዕምም አላወቁትም ፣ በተጨማሪም ከምንም ነገር በላይ የሆነውንና የጻድቅ ሰው ልቡ ከአንበሳ ይልቅ ጀግና ነው' እንደ ተባለ ነፍስን ዕለት በዕለት የሚያበረታታትን ፣ ኃይል የሚሰጣትንና የሚያጸናትን የእግዚአብሔርን ኃይል አያውቁም፡፡

ልጆቼ ሆይ ! እውነተኛና ጻድቅ የሆነ ሰው ልብ እንዴት ጽኑና ጀግና እንደ ሆነ ታያላችሁን ? ምክንያቱም መንፈሳዊ ምግብን ለመቀበል ስለሚፈቅድለት ነው ፣ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ስለዚህም ምክንያት ለሰውነቱ ቀን በቀን ጥንካሬን ስለሚሰጠው ሥጋዊ ምግብን እንደሚወስድ ሰው ነፍሱ ጽኑዕና ደፋር ናት፡፡ ስለሆነም ለመብላትና ኃይል ጽንዕ የሚሆነውን ምግብ ለመውሰድ የማይፈልግ ከሆነ ሰውነቱ እየዛለ ይሄዳል፡፡

ጠላቶቹ ቢዋጉት በቀላሉ ያሽንፉታል፡፡ እናም ልጆቼ ሆይ ፣ በጠላቶቻችሁ ላይ ድል አድራጊዎች ትሆኑ ዘንድ እንዲህ ዓይነት ምግብ ለመመገብ ራሳችሁን አለማምዱ ፣ ይኸውም ቃለ እግዚአብሔር ነው ፤ ጠላቶቻቸውን ድል ለማድረግ የሚያስችላቸውን ኃይልና ድፍረት ያገኙበት የነበረውን ይህን መንፈሳዊ ምግብ መላ የሕይወት ዘመናቸውን አጋንንት ሳይመገቡ እንዲቀሩ ያደረጓቸው ቁጥራቸው በጣም ብዙ የሆነ መነኰሳትና ደናግል አሉና፡

ይህን ምግብ መመገብ ያልቻሉት ለምንድን ነው ? ምክንያቱ ልባቸው የቀና ስላልሆነና የልባቸውን ምኞት መቋቋም ስለማይችሉ ነው ፣ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ልባቸው የረከሰ ስለ ሆነና ስለ እግዚአብሔር ትንሽ እንኳ እውቀት ስለሌላቸው ነው:: ከዚህም የተነሣ ነፍሳቸውን ያበረቱ ዘንድ አጋንንት የተቀደሰ የሆነውን መንፈሳዊ ምግብ ይመገቡ ዘንድ አያሰናብቷቸውም፡፡

ስለዚህም ምክንያት መላ ሕይወታቸውን በፈሪነት ፣ ግራ በመጋባት ፣ በሥቃይ እና እርስ በእርስ በመወነጃጀልና በማመካኘት አጠፉት፡፡ ስለዚህ ተወዳጆች የሆናችሁ ልጆቼ ሆይ ፣ በሕይወት ትኖሩ ዘንድና በመድኃኒታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር ሱቱፋን [ተሳታፊዎች] ሆናችሁ ትቆጠሩ ዘንድ ራሳችሁን ከዚህ መጥፎ ፍሬ ጠብቁ፡፡ ❞

🕊

አነሳስቶ ላስጀመረን ፥ አስጀምሮም ላስፈጸመን ለቅዱሳን ሁሉ አምላክ ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን፡፡ የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


💖                      🕊                      💖
👍41
3
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


የቅዱስ መቃርዎስ ሕይወቱና ትምህርቱ ተፈጸመ !

🕊

አነሳስቶ ላስጀመረን ፥ አስጀምሮም ላስፈጸመን ለቅዱሳን ሁሉ አምላክ ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን፡፡ የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

አሜን !


🕊                       💖                     🕊
👍32❤‍🔥1🙏1
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊

▷     "  የሚያበራ ንጽሕና !  "

[   💖   አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ   💖   ]

[                        🕊                        ]
-------------------------------------------------

❝ ወዳጆች ሆይ ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን ፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን።

በእርሱም ይህን ተስፋ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ንጹሕ እንደ ሆነ ራሱን ያነጻል። ❞

[   ፩ዮሐ.፫፥፪  ]


🕊                       💖                     🕊
4
Audio
🥰2
5
🕊

[  † እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃነ ዴጌ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †

🕊  †   ጻድቃነ ዴጌ   †  🕊

† እነዚህ ጻድቃን ኢትዮዽያውያን ባይሆኑም ያበሩት በሃገራችን ነው:: ቅዱሳኑ በቁጥር ፫ ሺህ [3,000] : በዜግነት ሮማውያን ናቸው:: ከሺህ አዝማናት በፊት ከሮም ግዛት ተሰባስበው እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮዽያ [አክሱም] መጥተዋል::

ቀጥለውም እዛው አካባቢ ወደሚገኝ ገዳም ገብተዋል:: ይህ ቦታ ለአክሱም ቅርብ ሲሆን በዘመነ ሐዋርያት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በዓት ነበር:: የሐዋርያው በትረ መስቀልም እስካሁን አለች::

ጻድቃነ ዴጌ ሕጋቸው አንዲት : እርሷም ፍቅር ናት:: ለዘመናት በፍቅረ ክርስቶስ ታሥረው : ፍቅርን ለብሰው : በፍቅር ኑረዋል:: ሁሌም በ፳፱ [29] የጌታችንን ስም እየጠሩ ጽዋ ጠጥተዋል:: ስለ ፍቅራቸውም ጌታችን ፫ ሺህ ፩ኛ [3,001] ኛ ሆኖ : ነዳይ መስሎ አብሯቸው ጠጥቷል::

በመጨረሻም ፫ ሺው በአንድነት ተሠውረዋል::

† ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን:: እኛንም በወዳጆቹ ጸሎት ይማረን:: . . .አሜን !

🕊

[   † ጥር ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ [ዴጌ ጻድቃን]
[አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ ፫ ሺህ [3,000] ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው]
፪. አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት [ኢትዮዽያዊ]
፫. ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
፬. ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
፭. አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
፮. ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት

[    † ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅድስት አርሴማ ሰማዕት
፪. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እናታችን
፫. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍፃሜተ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፭. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ

" ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " † [መዝ.፴፮፥፳፱]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
🙏1
9❤‍🔥1
#_______ፀሎት

#ፀሎት ልማድህ ሲሆን ተአምራቶች የህይወትህ ዘይቤ ይሆናሉ።
#ፀሎት የሰው ልጅ ካለምንም የአለማዊ ኔትዎርክ ዝርጋታ በቀጥታ #ከእግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርበት የመገናኛ መስመር ነው።
#ፀሎት ዘር ነውና መኸር አለው፣
#ፀሎት እንባ ነውና ሳቅ አለው፣
#ፀሎት ትግል ነውና ድል አለው፣
#ፀሎት ጩኸት ነውና መልስ አለው፣
#ፀሎት መንበርከክ ነውና ማሸነፍ አለው
በእግዚአብሔር ፊት #የሚንብረከክ ሰው በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ መቆም ይችላል።
#በፀሎት የማይቻለው ይቻላል🙏🙏🙏

#መልካም__ቀን🙏

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
11🙏4
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

[ የመርሐ-ግብር ማሳወቂያ ! ]

🕊

[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]

እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በቀኑ መርሐ-ግብር የቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] ድርሳን ላይ "መንፈሳዊው መሰላል" በሚል ርዕስ የቀረበው ትምህርትና ድንቅ ምክር ለንባብ እንዲመች እየተመጠነ የሚቀርብ ይሆናል።

በመርሐ-ግብሩ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ ልንወጣ ስለሚገባን የቅድስና መሰላልና የንጽሕና ሕይወት ጉዞ አስደናቂ ትምህርቶችን የምናገኝበት ነው፡፡

[   🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊  ]

- ተከታታይ መርሐ-ግብር
- ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ
- ከቀኑ ፱ ሰዓት [ 09:00 ] ላይ


🕊                       💖                     🕊
6👍1
7
                         †                        

 [       🕊    ፍኖተ ቅዱሳን    🕊      ]

[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

             [        ትሕትና !         ]

------------------------------------------

❝ አባ ኤስድሮስ እንዲህ አለ ፦ ሁል ጊዜ የምትጾም ከሆነ በትዕቢት ራስህን ወደ ላይ አታውጣ ፤ ከዚህ የተነሣ ራስህን ከፍ አድርገህ የምትመለከት ከሆነ ግን ሥጋ ብትበላ ይሻልሃል፡፡ ለአንድ ሰው ራሱን በትዕቢት ከመንፋትና ራሱን ከማክበር ሥጋ ቢበላ ይሻለዋልና፡፡ ❞
-------------------------------------------

❝ ቅድስት ሰንቀሌጢቃ እንዲህ አለች ፦ "መርከብ ያለ ምስማር ሊሠራ እንደማይችል ሁሉ ድኅነትም [ መዳንም ] ያለ ትሕትና ሊገኝ አይችልም፡፡ " ❞
--------------------------------------------

ለአባ ዮሐንስ ፦ " ሰውች መላእክትን አየናቸው ይላሉ። " አሉት። እርሱም ፦ " ብፁዕስ ሁል ጊዜ ኃጢአቱን የሚያይ ሰው ነው።" አላቸው
-------------------------------------------

🕊

የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡


†                         †                         †
💖                      🕊                      💖
1🥰1
6
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊

▷   "  ደስተኛ መሆን ትፈልጋለህ ? "

[   💖  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  💖  ]

[                        🕊                        ]
-------------------------------------------------

❝ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር ፥ ደስታ ፥ ሰላም ፥ ትዕግሥት ፥ ቸርነት ፥ በጎነት ፥ እምነት ፥ የውሃት ፥ ራስን መግዛት ነው። ❞

[   ገላ.፭፥፳፪  ]


🕊                       💖                     🕊
🥰32
2025/07/08 22:18:11
Back to Top
HTML Embed Code: