Telegram Web
3
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


የቅዱስ መቃርዎስ ሕይወቱና ትምህርቱ ተፈጸመ !

🕊

አነሳስቶ ላስጀመረን ፥ አስጀምሮም ላስፈጸመን ለቅዱሳን ሁሉ አምላክ ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን፡፡ የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

አሜን !


🕊                       💖                     🕊
👍32❤‍🔥1🙏1
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊

▷     "  የሚያበራ ንጽሕና !  "

[   💖   አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ   💖   ]

[                        🕊                        ]
-------------------------------------------------

❝ ወዳጆች ሆይ ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን ፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን።

በእርሱም ይህን ተስፋ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ንጹሕ እንደ ሆነ ራሱን ያነጻል። ❞

[   ፩ዮሐ.፫፥፪  ]


🕊                       💖                     🕊
4
Audio
🥰2
5
🕊

[  † እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃነ ዴጌ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †

🕊  †   ጻድቃነ ዴጌ   †  🕊

† እነዚህ ጻድቃን ኢትዮዽያውያን ባይሆኑም ያበሩት በሃገራችን ነው:: ቅዱሳኑ በቁጥር ፫ ሺህ [3,000] : በዜግነት ሮማውያን ናቸው:: ከሺህ አዝማናት በፊት ከሮም ግዛት ተሰባስበው እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮዽያ [አክሱም] መጥተዋል::

ቀጥለውም እዛው አካባቢ ወደሚገኝ ገዳም ገብተዋል:: ይህ ቦታ ለአክሱም ቅርብ ሲሆን በዘመነ ሐዋርያት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በዓት ነበር:: የሐዋርያው በትረ መስቀልም እስካሁን አለች::

ጻድቃነ ዴጌ ሕጋቸው አንዲት : እርሷም ፍቅር ናት:: ለዘመናት በፍቅረ ክርስቶስ ታሥረው : ፍቅርን ለብሰው : በፍቅር ኑረዋል:: ሁሌም በ፳፱ [29] የጌታችንን ስም እየጠሩ ጽዋ ጠጥተዋል:: ስለ ፍቅራቸውም ጌታችን ፫ ሺህ ፩ኛ [3,001] ኛ ሆኖ : ነዳይ መስሎ አብሯቸው ጠጥቷል::

በመጨረሻም ፫ ሺው በአንድነት ተሠውረዋል::

† ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን:: እኛንም በወዳጆቹ ጸሎት ይማረን:: . . .አሜን !

🕊

[   † ጥር ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ [ዴጌ ጻድቃን]
[አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ ፫ ሺህ [3,000] ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው]
፪. አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት [ኢትዮዽያዊ]
፫. ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
፬. ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
፭. አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
፮. ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት

[    † ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅድስት አርሴማ ሰማዕት
፪. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እናታችን
፫. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍፃሜተ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፭. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ

" ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " † [መዝ.፴፮፥፳፱]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
🙏1
9❤‍🔥1
#_______ፀሎት

#ፀሎት ልማድህ ሲሆን ተአምራቶች የህይወትህ ዘይቤ ይሆናሉ።
#ፀሎት የሰው ልጅ ካለምንም የአለማዊ ኔትዎርክ ዝርጋታ በቀጥታ #ከእግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርበት የመገናኛ መስመር ነው።
#ፀሎት ዘር ነውና መኸር አለው፣
#ፀሎት እንባ ነውና ሳቅ አለው፣
#ፀሎት ትግል ነውና ድል አለው፣
#ፀሎት ጩኸት ነውና መልስ አለው፣
#ፀሎት መንበርከክ ነውና ማሸነፍ አለው
በእግዚአብሔር ፊት #የሚንብረከክ ሰው በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ መቆም ይችላል።
#በፀሎት የማይቻለው ይቻላል🙏🙏🙏

#መልካም__ቀን🙏

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
11🙏4
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

[ የመርሐ-ግብር ማሳወቂያ ! ]

🕊

[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]

እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በቀኑ መርሐ-ግብር የቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] ድርሳን ላይ "መንፈሳዊው መሰላል" በሚል ርዕስ የቀረበው ትምህርትና ድንቅ ምክር ለንባብ እንዲመች እየተመጠነ የሚቀርብ ይሆናል።

በመርሐ-ግብሩ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ ልንወጣ ስለሚገባን የቅድስና መሰላልና የንጽሕና ሕይወት ጉዞ አስደናቂ ትምህርቶችን የምናገኝበት ነው፡፡

[   🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊  ]

- ተከታታይ መርሐ-ግብር
- ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ
- ከቀኑ ፱ ሰዓት [ 09:00 ] ላይ


🕊                       💖                     🕊
6👍1
7
                         †                        

 [       🕊    ፍኖተ ቅዱሳን    🕊      ]

[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

             [        ትሕትና !         ]

------------------------------------------

❝ አባ ኤስድሮስ እንዲህ አለ ፦ ሁል ጊዜ የምትጾም ከሆነ በትዕቢት ራስህን ወደ ላይ አታውጣ ፤ ከዚህ የተነሣ ራስህን ከፍ አድርገህ የምትመለከት ከሆነ ግን ሥጋ ብትበላ ይሻልሃል፡፡ ለአንድ ሰው ራሱን በትዕቢት ከመንፋትና ራሱን ከማክበር ሥጋ ቢበላ ይሻለዋልና፡፡ ❞
-------------------------------------------

❝ ቅድስት ሰንቀሌጢቃ እንዲህ አለች ፦ "መርከብ ያለ ምስማር ሊሠራ እንደማይችል ሁሉ ድኅነትም [ መዳንም ] ያለ ትሕትና ሊገኝ አይችልም፡፡ " ❞
--------------------------------------------

ለአባ ዮሐንስ ፦ " ሰውች መላእክትን አየናቸው ይላሉ። " አሉት። እርሱም ፦ " ብፁዕስ ሁል ጊዜ ኃጢአቱን የሚያይ ሰው ነው።" አላቸው
-------------------------------------------

🕊

የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡


†                         †                         †
💖                      🕊                      💖
1🥰1
6
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊

▷   "  ደስተኛ መሆን ትፈልጋለህ ? "

[   💖  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  💖  ]

[                        🕊                        ]
-------------------------------------------------

❝ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር ፥ ደስታ ፥ ሰላም ፥ ትዕግሥት ፥ ቸርነት ፥ በጎነት ፥ እምነት ፥ የውሃት ፥ ራስን መግዛት ነው። ❞

[   ገላ.፭፥፳፪  ]


🕊                       💖                     🕊
🥰32
Audio
🥰21
🥰6
2025/07/14 03:14:15
Back to Top
HTML Embed Code: