#የኃጢአት ምኞትህን የሚዛን ልክ በልብህ ውስጥ ያመጣጥን ዘንድ ማንኛውንም ዓይነት #መንፈሳዊ ሥራ በመሥራት የክፋታቸውንና የአደጋቸውን መጠን ቀንስ። #የምኞት ኃጢአት እስክታስወግደው ድረስ #መልካም ፈቃድ በልብህ ውስጥ ቀስ በቀስ እንደሚያብብ እርግጠኛ ሁን። #መንፈስ_ቅዱስ በውስጥህ እንደሚሰራ ሲታወቅህ ችላ አትበለው፤ ከእርሱ ጋር ሥራ እንጂ #በምኞትህ ልትቀጥል አትሞክር።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
••• #_ሰናይ__ቀን🙏 ...
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
••• #_ሰናይ__ቀን🙏 ...
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6👍5🙏3🥰1
🕊
[ † እንኳን ለአባታችን ታላቁ ቅዱስ በርሱማ ሶርያዊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ † 🕊 ታላቁ አባ በርሱማ 🕊 † ]
† ታላቁ [THE GREAT ይሉታል] አባ በርሱማ በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ምንኩስናና ገዳማዊ ሕይወትን ያስፋፋ አባት ነው::
በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ምድረ ሶርያን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች የቅድስና ሕይወትን ያስፋፋው ቅዱስ በርሱማ ለቤተ ክርስቲያን ምሰሶ ከሆኑላት አበው አንዱ ነው:: እርሱ ከተጋድሎው ብዛት ለ54 ዓመታት ያለ እንቅልፍ ቆይቷል::
በእነዚህ ዘመናትም ግድግዳ ላይ ጠጋ ብሎ ከማረፉ በቀር መቀመጥን እንኩዋ አልመረጠም:: በመዓልትም በሌሊትም በፍቅር አብዝቶ ስለ ራሱና ስለ ሕዝቡ በመጸለዩ የብዙዎቹን ነፍስ ወደ ሕይወት ማርኩዋል::
ገዳማትን ከማስፋፋትና ደቀ መዛሙርትን ከማብዛቱ ባለፈ በስብከተ ወንጌልም የተመሰከረለት አባት ነበር:: በ፬፻፴፩ (431) ፬፻፳፫ (423) ዓ/ም በኤፌሶን በተደረገው የቅዱሳን ጉባኤ ላይ ከተገኙ ሊቃውንትም አንዱ ነው:: በቅድስና ሕይወቱ የተገረመው የቁስጥንጥንያው ንጉሥ [ትንሹ ቴዎዶስዮስ] የንግሥና ቀለበቱን እና ማኅተሙን ሸልሞታል::
ቅዱሱም የዋዛ አልነበረምና በንጉሡ ማኅተም እያተመ "ተፋቀሩ" የሚሉ ብዙ አዋጆችን ወደ መላው ዓለም ልኩዋል:: በ፬፻፶፩ [451] ፬፻፵፫ (443) ዓ/ም በኬልቄዶን ፮፻፴፮ [636] ሰነፍ ዻዻሳት ጉባኤ አድርገው አባ ዲዮርስቆሮስን እንደ ገደሉት ሲሰማም ወደ ቤተ መንግስት ሒዶ ከሃዲዎቹን [መርቅያንና ሚስቱ ብርክልያን] በአደባባይ ዘልፏቸዋል::
ስለ አዘነባቸውም ተቀስፈዋል:: ታላቁ ቅዱስ አባ በርሱማ ፀሐይን ማቆሙን ጨምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቶ በዚህች ቀን ዐርፏል::
† ቸር አምላኩ ከበረከቱ ይክፈለን::
[ † የካቲት ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ በርሱማ ሶርያዊ [ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት]
፪. አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ኢትዮዽያዊ] የመነኮሱበት በዓል
፫. ቅዱስ ዻውሎስ ሶርያዊ [ሰማዕት]
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. "318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት [ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ]
፪. የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
፫. አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ [ኢትዮዽያዊ]
፬. ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ [ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት]
† " ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን ? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?" † [ሚክ.፮፥፮] (6:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለአባታችን ታላቁ ቅዱስ በርሱማ ሶርያዊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ † 🕊 ታላቁ አባ በርሱማ 🕊 † ]
† ታላቁ [THE GREAT ይሉታል] አባ በርሱማ በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ምንኩስናና ገዳማዊ ሕይወትን ያስፋፋ አባት ነው::
በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ምድረ ሶርያን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች የቅድስና ሕይወትን ያስፋፋው ቅዱስ በርሱማ ለቤተ ክርስቲያን ምሰሶ ከሆኑላት አበው አንዱ ነው:: እርሱ ከተጋድሎው ብዛት ለ54 ዓመታት ያለ እንቅልፍ ቆይቷል::
በእነዚህ ዘመናትም ግድግዳ ላይ ጠጋ ብሎ ከማረፉ በቀር መቀመጥን እንኩዋ አልመረጠም:: በመዓልትም በሌሊትም በፍቅር አብዝቶ ስለ ራሱና ስለ ሕዝቡ በመጸለዩ የብዙዎቹን ነፍስ ወደ ሕይወት ማርኩዋል::
ገዳማትን ከማስፋፋትና ደቀ መዛሙርትን ከማብዛቱ ባለፈ በስብከተ ወንጌልም የተመሰከረለት አባት ነበር:: በ፬፻፴፩ (431) ፬፻፳፫ (423) ዓ/ም በኤፌሶን በተደረገው የቅዱሳን ጉባኤ ላይ ከተገኙ ሊቃውንትም አንዱ ነው:: በቅድስና ሕይወቱ የተገረመው የቁስጥንጥንያው ንጉሥ [ትንሹ ቴዎዶስዮስ] የንግሥና ቀለበቱን እና ማኅተሙን ሸልሞታል::
ቅዱሱም የዋዛ አልነበረምና በንጉሡ ማኅተም እያተመ "ተፋቀሩ" የሚሉ ብዙ አዋጆችን ወደ መላው ዓለም ልኩዋል:: በ፬፻፶፩ [451] ፬፻፵፫ (443) ዓ/ም በኬልቄዶን ፮፻፴፮ [636] ሰነፍ ዻዻሳት ጉባኤ አድርገው አባ ዲዮርስቆሮስን እንደ ገደሉት ሲሰማም ወደ ቤተ መንግስት ሒዶ ከሃዲዎቹን [መርቅያንና ሚስቱ ብርክልያን] በአደባባይ ዘልፏቸዋል::
ስለ አዘነባቸውም ተቀስፈዋል:: ታላቁ ቅዱስ አባ በርሱማ ፀሐይን ማቆሙን ጨምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቶ በዚህች ቀን ዐርፏል::
† ቸር አምላኩ ከበረከቱ ይክፈለን::
[ † የካቲት ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ በርሱማ ሶርያዊ [ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት]
፪. አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ኢትዮዽያዊ] የመነኮሱበት በዓል
፫. ቅዱስ ዻውሎስ ሶርያዊ [ሰማዕት]
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. "318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት [ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ]
፪. የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
፫. አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ [ኢትዮዽያዊ]
፬. ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ [ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት]
† " ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን ? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?" † [ሚክ.፮፥፮] (6:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍2
#ቤተክርስቲያንን__አይችሏት ??
#ከቤተ_ክርስቲያን የሚበልጥ ብርቱ (ጠንካራ) ምንም የለም። ይህችውም ከሰማይ ከፍ ያለች ከምድርም ይልቅ የሰፋች ናት። አታረጅም ነገር ግን ዘወትር ታበራለች። #ቤተ_ክርስቲያን በዘመናት ሁሉ ትሰፋለች። መታሰቢያዋም የሚጠፋ (የሚሞት) አይደለም። ቤተ ክርስቲያን በስንቶች ውጊያ ተደርጎባት ነበር? #አልተሸነፈችም እንጂ። የተዋጓት አላውያን፣ የጦር መሪዎች፣ ነገሥታቱስ ምን ያህል ናቸው?
#የተማሩና_ኃይልን የተሞሉ ጎበዞች ሐዲሲቷን ቤተ ክርስቲያን በብዙ ጎዳናዎች ተዋግተዋት ነበር። #ሊነቅሏት ግን አልቻሉም። ነገር ግን እርሷን የተዋጉ ጥቂቶች ለዝምታና ቶሎም ለመረሳት ተላልፈው ተሰጥተዋል። የወጓት ቤተ ክርስቲያን ግን ከሰማይ በላይ ከፍ ከፍ ብላለች። #ቤተ_ክርስቲያንን ድል ከማድረግስ ፀሐይን ማጥፋት (ማጨለም) ይቀላል። ሰው ሆይ! ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ኃያል ምንም የለም። ከሰው ብትጣላ ወይ ታሸንፋለህ አልያም ትሸነፋለህ። #ቤተ_ክርቲያንን ግን ብትጣላ፣ ታሸነፍ ዘንድ የሚቻልህ አይደለም። #እግዚአብሔር ከሁሉ ይልቅ ኃያል ነውና። እግዚአብሔር መስርቷታል፣ እንግዲህ ማን #ሊነቀንቃት ይችላል? "
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#መልካም_ዕለተ_ሰንበት🙏
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ከቤተ_ክርስቲያን የሚበልጥ ብርቱ (ጠንካራ) ምንም የለም። ይህችውም ከሰማይ ከፍ ያለች ከምድርም ይልቅ የሰፋች ናት። አታረጅም ነገር ግን ዘወትር ታበራለች። #ቤተ_ክርስቲያን በዘመናት ሁሉ ትሰፋለች። መታሰቢያዋም የሚጠፋ (የሚሞት) አይደለም። ቤተ ክርስቲያን በስንቶች ውጊያ ተደርጎባት ነበር? #አልተሸነፈችም እንጂ። የተዋጓት አላውያን፣ የጦር መሪዎች፣ ነገሥታቱስ ምን ያህል ናቸው?
#የተማሩና_ኃይልን የተሞሉ ጎበዞች ሐዲሲቷን ቤተ ክርስቲያን በብዙ ጎዳናዎች ተዋግተዋት ነበር። #ሊነቅሏት ግን አልቻሉም። ነገር ግን እርሷን የተዋጉ ጥቂቶች ለዝምታና ቶሎም ለመረሳት ተላልፈው ተሰጥተዋል። የወጓት ቤተ ክርስቲያን ግን ከሰማይ በላይ ከፍ ከፍ ብላለች። #ቤተ_ክርስቲያንን ድል ከማድረግስ ፀሐይን ማጥፋት (ማጨለም) ይቀላል። ሰው ሆይ! ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ኃያል ምንም የለም። ከሰው ብትጣላ ወይ ታሸንፋለህ አልያም ትሸነፋለህ። #ቤተ_ክርቲያንን ግን ብትጣላ፣ ታሸነፍ ዘንድ የሚቻልህ አይደለም። #እግዚአብሔር ከሁሉ ይልቅ ኃያል ነውና። እግዚአብሔር መስርቷታል፣ እንግዲህ ማን #ሊነቀንቃት ይችላል? "
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#መልካም_ዕለተ_ሰንበት🙏
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤16🙏3👍1
🕊
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን። ✞✞✞
[ † እንኩዋን ለቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ: ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕትና አባ ኤስድሮስ ገዳማዊ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ያእቆብ † 🕊
ቅዱስ ያዕቆብ [ የእልፍዮስ ልጅ ] ከ፲፪ [12]ቱ ሐዋርያት አንዱ [ ማቴ.፲፥፩ ] ብዙ አሕጉር አስተምሮ በዚህ ቀን በሰማዕትነት ወደ ፈጣሪው ሔዷል::
ቅዱስ ዮስጦስ በ፫ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ ምድራዊ የንግሥና ዙፋንን ንቆ በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ከሚስቱ ቅድስት ታውክልያና ከአንድ ልጁ ቅዱስ አቦሊ ጋር ሰማያዊ ክብርን ተቀዳጅቷል::
አባ ኤስድሮስ ግብፃዊ ሲሆኑ ሹመትን ጠልተው ፈርማ በሚባል ገዳም ለ፷ [ 60 ] ዓመታት በበርሃ ውስጥ ከ፲፰ ሺህ [ 18,000 ] በላይ ድርሳናትን ፅፈዋል:: ይሕም በዓለም ታሪክ ብዙ መጻሕፍትን በመጻፍ ቀዳሚው ያደርጋቸዋል:: ከድርሳናቱ መካከል ፪ ሺህ [ 2,000 ] ያህሉ ዛሬም ድረስ በግብፅ በርሃ ውስጥ ይገኛሉ::
ከስንክሳር
🕊 † አባ ፌሎ † 🕊
በዚች ቀን የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ፌሎ በሰማእትነት አረፈ ። ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሰዋ ለፀሀይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉስ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ስቃይን አሰቃይቶ እራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግስተ ሰማያት የሰማእትነትን አክሊል ተቀበለ ።
በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር።
🕊 † አባ ኤስድሮስ † 🕊
በዚችም እለት በገድል የተጠመደ ምሁር የሆነ የአለሙ ሁሉ መምህር አባ ኤስድርስ ፈርማ ከሚባል አገር አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለፀጉች ናቸው።
ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸውከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩት።
ግልፅ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሄድና አለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሁትና የሚተጋ ሆነ።
በሀገሮችም ያለ ሰዎች ሰለርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾመት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ ። በሌሊትም ወጥቶ ሽሽ ወደ ፈረማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኮሰ።
ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ዋሻ ገብቶ ብቻውን በወስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሳፃትንም ደረሰ ከዕርሳቸውም ስለ ነገስታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ የቤተ ክርስቲያንን መፃህፍቶችን ብሉያትና ሀዲሳትን ተረጉመ።
የመፅሀፍታቹም ቁጥራቸው አስራ ስምንት ሺህ ነው። እነዚህም ድርሳናት ተግሳፃት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልእክቶች ናቸው። ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያስፈልቃቸው ሆኗልና።
ይህንንም በጎ ስራውን ሲፈፅሙ መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሄርንም አግልግሎ በሰላም አረፈ።
[ † የካቲት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ ወልደ እልፍዮስ ]
፪. ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት
፫. አባ ኤስድሮስ ጻድቅ [ ዘሃገረ ፈርማ ]
፬. አባ ፌሎ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ስምዖን
፮. ቅዱስ ኒቆላዎስ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕፀ-መስቀል
፪. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፬. ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
" . . . ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ በእናንተ ላይ ከሚሆነው: ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ይናፍቁዋቹሀል:: ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን::" [፪ኛ ቆሮ.፱፥፲፬ ]
" ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ: ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ:: " [ኤፌ.፭፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን። ✞✞✞
[ † እንኩዋን ለቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ: ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕትና አባ ኤስድሮስ ገዳማዊ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ያእቆብ † 🕊
ቅዱስ ያዕቆብ [ የእልፍዮስ ልጅ ] ከ፲፪ [12]ቱ ሐዋርያት አንዱ [ ማቴ.፲፥፩ ] ብዙ አሕጉር አስተምሮ በዚህ ቀን በሰማዕትነት ወደ ፈጣሪው ሔዷል::
ቅዱስ ዮስጦስ በ፫ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ ምድራዊ የንግሥና ዙፋንን ንቆ በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ከሚስቱ ቅድስት ታውክልያና ከአንድ ልጁ ቅዱስ አቦሊ ጋር ሰማያዊ ክብርን ተቀዳጅቷል::
አባ ኤስድሮስ ግብፃዊ ሲሆኑ ሹመትን ጠልተው ፈርማ በሚባል ገዳም ለ፷ [ 60 ] ዓመታት በበርሃ ውስጥ ከ፲፰ ሺህ [ 18,000 ] በላይ ድርሳናትን ፅፈዋል:: ይሕም በዓለም ታሪክ ብዙ መጻሕፍትን በመጻፍ ቀዳሚው ያደርጋቸዋል:: ከድርሳናቱ መካከል ፪ ሺህ [ 2,000 ] ያህሉ ዛሬም ድረስ በግብፅ በርሃ ውስጥ ይገኛሉ::
ከስንክሳር
🕊 † አባ ፌሎ † 🕊
በዚች ቀን የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ፌሎ በሰማእትነት አረፈ ። ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሰዋ ለፀሀይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉስ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ስቃይን አሰቃይቶ እራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግስተ ሰማያት የሰማእትነትን አክሊል ተቀበለ ።
በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር።
🕊 † አባ ኤስድሮስ † 🕊
በዚችም እለት በገድል የተጠመደ ምሁር የሆነ የአለሙ ሁሉ መምህር አባ ኤስድርስ ፈርማ ከሚባል አገር አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለፀጉች ናቸው።
ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸውከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩት።
ግልፅ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሄድና አለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሁትና የሚተጋ ሆነ።
በሀገሮችም ያለ ሰዎች ሰለርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾመት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ ። በሌሊትም ወጥቶ ሽሽ ወደ ፈረማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኮሰ።
ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ዋሻ ገብቶ ብቻውን በወስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሳፃትንም ደረሰ ከዕርሳቸውም ስለ ነገስታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ የቤተ ክርስቲያንን መፃህፍቶችን ብሉያትና ሀዲሳትን ተረጉመ።
የመፅሀፍታቹም ቁጥራቸው አስራ ስምንት ሺህ ነው። እነዚህም ድርሳናት ተግሳፃት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልእክቶች ናቸው። ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያስፈልቃቸው ሆኗልና።
ይህንንም በጎ ስራውን ሲፈፅሙ መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሄርንም አግልግሎ በሰላም አረፈ።
[ † የካቲት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ ወልደ እልፍዮስ ]
፪. ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት
፫. አባ ኤስድሮስ ጻድቅ [ ዘሃገረ ፈርማ ]
፬. አባ ፌሎ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ስምዖን
፮. ቅዱስ ኒቆላዎስ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕፀ-መስቀል
፪. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፬. ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
" . . . ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ በእናንተ ላይ ከሚሆነው: ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ይናፍቁዋቹሀል:: ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን::" [፪ኛ ቆሮ.፱፥፲፬ ]
" ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ: ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ:: " [ኤፌ.፭፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤3👍2
አምላኬ፥ በቀን ወደ አንተ እጣራለሁ፥ አልመለስህልኝም፤ በሌሊትም እንኳ ዕረፍት የለኝም።
፤ በእስራኤል የተመሰገንህ አንተ ግን በቅድስና ትኖራለህ።
፤ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ፥ ተማመኑ አንተም አዳንሃቸው።
፤ ወደ አንተ ጮኹ አመለጡም፥ አንተንም ተማመኑ አላፈሩም።
፤ እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፤ የሰው ማላገጫ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ።
፤ የሚያዩኝ ሁሉ ይላግጡብኛል፤ ራሳቸውን እየነቀነቁ በከንፈሮቻቸው እንዲህ ይላሉ።
፤ በእግዚአብሔር ተማመነ፥ እርሱንም ያድነው፤ ቢወድደውስ ያድነው።
፤ አንተ ግን ከሆድ አውጥተኸኛልና፥ በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ።
፤ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ።
፤ ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ።
መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 22ቁ 2-11
#መልካም_ቀን🙏
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
፤ በእስራኤል የተመሰገንህ አንተ ግን በቅድስና ትኖራለህ።
፤ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ፥ ተማመኑ አንተም አዳንሃቸው።
፤ ወደ አንተ ጮኹ አመለጡም፥ አንተንም ተማመኑ አላፈሩም።
፤ እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፤ የሰው ማላገጫ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ።
፤ የሚያዩኝ ሁሉ ይላግጡብኛል፤ ራሳቸውን እየነቀነቁ በከንፈሮቻቸው እንዲህ ይላሉ።
፤ በእግዚአብሔር ተማመነ፥ እርሱንም ያድነው፤ ቢወድደውስ ያድነው።
፤ አንተ ግን ከሆድ አውጥተኸኛልና፥ በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ።
፤ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ።
፤ ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ።
መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 22ቁ 2-11
#መልካም_ቀን🙏
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤10👍2🙏2
🕊
[ † እንኳን ለጻድቁ አባ አውሎግ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
† 🕊 አባ አውሎግ አንበሳዊ 🕊 †
† አባ አውሎግ ማለት :-
- ከቀደመው ዘመን ጻድቃን አንዱ::
- እንደ ገዳማውያን ፍፁም ባሕታዊ::
- እንደ ሐዋርያት ብዙ ሃገራትን በስብከተ ወንጌል ያሳመኑ::
- በግብፅና በሶርያ በርሃዎች ለ፺ [90] ዓመታት የተጋደሉ ጻድቅና ሐዋርያ ሲሆኑ የሚጉዋዙበትና የሚታዘዛቸው ግሩም አንበሳ ነበር::
- በዚህም አባ አውሎግ "አንበሳዊ" ስትል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትጠራቸዋለች::
አባ አውሎግ ከሚታወቁበት አገልግሎት አንዱ ስብከተ ወንጌል ነው:: ምንም እንኩዋ ገዳማዊ ቅዱስ ቢሆኑም ያላመኑትን ለማሳመን : ያመኑትንም ለማጽናት ተጋድለዋል::
እግዚአብሔር በሰጣቸው አናብስት በአንዱ ላይ ተጭነው [መዝ.፺ (90) : በሌላኛው ላይ እቃቸውን አስቀምጠው በየአኅጉራቱ ከመምህራቸው ቅዱስ አውሎጊን ጋር ይዘዋወሩም ነበር:: የጌታ ቸርነት ሆኖም አናብስቱ የቅዱሳኑን ፈቃድ ሳይነገራቸው ያውቁ ነበር::
ሲርባቸውም ተግተው ይመግቧቸው ነበር:: እንዲያውም አንዴ ቅዱሳኑ እንደራባቸው አንዱ አንበሳ ሲያውቅ ከበርሐ ወደ ገበያ መንገድ ወጥቶ ተመለከተ:: በአህያ ላይ ልጁንና ስንቁን [ዳቦ] ጭኖ የሚሔድ ሽማግሌ ነበርና ዳቦውን አንስቶ ወስዶ ለእነ አባ አውሎግ ሰጣቸው::
ከድንጋጤ የተነሳም ሕጻኑ ሙቶ ነበርና ሽማግሌ አባቱ አዘነ:: አንበሳው ግን ሕጻኑንም ወደ ቅዱሳኑ ወስዶ አስረከበ:: ቅዱሳኑም ከሕብስቱ በመጠናቸው በልተው ቢባርኩት እንዳልተበላ ሆነ:: ሕጻኑንም ከሞት በጸሎታቸው አስነስተው ለአንበሳው ሰጥተውታል::
አንበሳውም ስንቁንና ልጁን ለአረጋዊው ሰጥቶት በደስታ ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: ቅዱስ አባ አውሎግና መምህሩ አውሎጊን ከ፺ [90] ዓመታት በላይ በዘለቀ ተጋድሏቸው አጋንንትን ያሳፍሩ ዘንድ : ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ንጹሕ መስዋዕት ይሆኑለት ዘንድ በትጋት ኑረዋል::
¤ ብዙ ተአምራትን ሠርተው ፈጣሪያቸውን አክብረዋል::
¤ እንደ ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ባሕር ከፍለዋል::
¤ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙት አንስተዋል:: ድውያንን ፈውሰዋል::
¤ እንደ ቅዱስ ዳንኤል አናብስትን ገዝተዋል::
¤ ይህች ቀን ዕለተ ዕረፍታቸው ናት::
† 🕊 ቅዱስ በላትያኖስ 🕊 †
††† ይህ ቅዱስ ሐዋርያዊ ዻዻስ የቀድሞዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት ሲሆን ቸር : ትጉህና በጐ እረኛ ነበር:: መናፍቃንን ሲያርም : ምዕመናንን ሲመክር : ስለ መንጋው እንቅልፍ አጥቶ ኑሯል:: በፍጻሜውም በዚህች ቀን የሮም ንጉሥ ለ፩ (1) ዓመት አሰቃይቶ ገድሎታል:: ዕሴተ ኖሎትን [የእረኝነት ዋጋንም] ከጌታችን ተቀብሏል::
† አምላከ አበው ቅዱሳን በመጽናታቸው ያጽናን:: ከበረከታቸውም ያድለን::
[ † የካቲት ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ አውሎግ አንበሳዊ
፪. አባ አውሎጊን ጻድቅ [የአባ አውሎግ መምሕር]
፫. አባ በትራ [የጻድቁ አባ ስልዋኖስ ደቀ መዝሙር]
፬. አባ በላትያኖስ ሰማዕት [የሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረ]
፭. አባ አብርሃም ኤዺስ ቆዾስ
፮. አባ መቃቢስ
፯. አባ ኮንቲ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት
፫. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፬. ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
፭. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
† "በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምንም ከኁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ ነው::" † [ኤፌ.፩፥፲፱ (1:19)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለጻድቁ አባ አውሎግ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
† 🕊 አባ አውሎግ አንበሳዊ 🕊 †
† አባ አውሎግ ማለት :-
- ከቀደመው ዘመን ጻድቃን አንዱ::
- እንደ ገዳማውያን ፍፁም ባሕታዊ::
- እንደ ሐዋርያት ብዙ ሃገራትን በስብከተ ወንጌል ያሳመኑ::
- በግብፅና በሶርያ በርሃዎች ለ፺ [90] ዓመታት የተጋደሉ ጻድቅና ሐዋርያ ሲሆኑ የሚጉዋዙበትና የሚታዘዛቸው ግሩም አንበሳ ነበር::
- በዚህም አባ አውሎግ "አንበሳዊ" ስትል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትጠራቸዋለች::
አባ አውሎግ ከሚታወቁበት አገልግሎት አንዱ ስብከተ ወንጌል ነው:: ምንም እንኩዋ ገዳማዊ ቅዱስ ቢሆኑም ያላመኑትን ለማሳመን : ያመኑትንም ለማጽናት ተጋድለዋል::
እግዚአብሔር በሰጣቸው አናብስት በአንዱ ላይ ተጭነው [መዝ.፺ (90) : በሌላኛው ላይ እቃቸውን አስቀምጠው በየአኅጉራቱ ከመምህራቸው ቅዱስ አውሎጊን ጋር ይዘዋወሩም ነበር:: የጌታ ቸርነት ሆኖም አናብስቱ የቅዱሳኑን ፈቃድ ሳይነገራቸው ያውቁ ነበር::
ሲርባቸውም ተግተው ይመግቧቸው ነበር:: እንዲያውም አንዴ ቅዱሳኑ እንደራባቸው አንዱ አንበሳ ሲያውቅ ከበርሐ ወደ ገበያ መንገድ ወጥቶ ተመለከተ:: በአህያ ላይ ልጁንና ስንቁን [ዳቦ] ጭኖ የሚሔድ ሽማግሌ ነበርና ዳቦውን አንስቶ ወስዶ ለእነ አባ አውሎግ ሰጣቸው::
ከድንጋጤ የተነሳም ሕጻኑ ሙቶ ነበርና ሽማግሌ አባቱ አዘነ:: አንበሳው ግን ሕጻኑንም ወደ ቅዱሳኑ ወስዶ አስረከበ:: ቅዱሳኑም ከሕብስቱ በመጠናቸው በልተው ቢባርኩት እንዳልተበላ ሆነ:: ሕጻኑንም ከሞት በጸሎታቸው አስነስተው ለአንበሳው ሰጥተውታል::
አንበሳውም ስንቁንና ልጁን ለአረጋዊው ሰጥቶት በደስታ ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: ቅዱስ አባ አውሎግና መምህሩ አውሎጊን ከ፺ [90] ዓመታት በላይ በዘለቀ ተጋድሏቸው አጋንንትን ያሳፍሩ ዘንድ : ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ንጹሕ መስዋዕት ይሆኑለት ዘንድ በትጋት ኑረዋል::
¤ ብዙ ተአምራትን ሠርተው ፈጣሪያቸውን አክብረዋል::
¤ እንደ ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ባሕር ከፍለዋል::
¤ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙት አንስተዋል:: ድውያንን ፈውሰዋል::
¤ እንደ ቅዱስ ዳንኤል አናብስትን ገዝተዋል::
¤ ይህች ቀን ዕለተ ዕረፍታቸው ናት::
† 🕊 ቅዱስ በላትያኖስ 🕊 †
††† ይህ ቅዱስ ሐዋርያዊ ዻዻስ የቀድሞዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት ሲሆን ቸር : ትጉህና በጐ እረኛ ነበር:: መናፍቃንን ሲያርም : ምዕመናንን ሲመክር : ስለ መንጋው እንቅልፍ አጥቶ ኑሯል:: በፍጻሜውም በዚህች ቀን የሮም ንጉሥ ለ፩ (1) ዓመት አሰቃይቶ ገድሎታል:: ዕሴተ ኖሎትን [የእረኝነት ዋጋንም] ከጌታችን ተቀብሏል::
† አምላከ አበው ቅዱሳን በመጽናታቸው ያጽናን:: ከበረከታቸውም ያድለን::
[ † የካቲት ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ አውሎግ አንበሳዊ
፪. አባ አውሎጊን ጻድቅ [የአባ አውሎግ መምሕር]
፫. አባ በትራ [የጻድቁ አባ ስልዋኖስ ደቀ መዝሙር]
፬. አባ በላትያኖስ ሰማዕት [የሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረ]
፭. አባ አብርሃም ኤዺስ ቆዾስ
፮. አባ መቃቢስ
፯. አባ ኮንቲ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት
፫. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፬. ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
፭. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
† "በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምንም ከኁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ ነው::" † [ኤፌ.፩፥፲፱ (1:19)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤4
የሚያሳድዷችሁን መርቁ . . . ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ
እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ ። የትዕቢትን ነገር አታስቡ ። ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ ። (ሮሜ. ፲፪፥፲፬-፲፮)
#_ሰናይ__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ ። የትዕቢትን ነገር አታስቡ ። ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ ። (ሮሜ. ፲፪፥፲፬-፲፮)
#_ሰናይ__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤12👍2
🕊
[ † እንኳን ለኢትዮዽያውያን ሰማዕታት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ኢትዮዽያውያን ሰማዕታት † 🕊
† በ፲፱፻፳፱ [1929] ዓ/ም: የካቲት ፲፪ [12] ቀን ከ፴ ሺህ [30,000] በላይ ኢትዮዽያውያን አባቶች : እናቶች : ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ደማቸው ፈሷል:: እነዚሕ ወገኖቻችን ደማቸው እንደ ጐርፍ አዲስ አበባ ላይ የፈሰሰው ስለ ሃገር ፍቅር ብቻ አልነበረም:: ስለ ቀናች ሃይማኖት ተዋሕዶ ጭምር ነው እንጂ::
† ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ግፃዌ ላይ ስማቸውን ጽፋ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር እንዲህ ታስባቸዋለች::
"አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ::
የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ::
ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት::
የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ::
የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት::
ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውሃ አፈሰሱ:: የሚቀብራቸውም አጡ::" [መዝ.፸፰፥፥፩]
† ሰማዕታቱን እናስባቸው !
🕊 † ሶምሶን ረዓይታዊ † 🕊
† እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን : ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ : በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ : ነቢይና ካህን አድርጐ : ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::
አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ፻ [100] ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::
ስለዚህም ምክንያት ለ፭ ሺሀ ፭ መቶ [5,500] ዓመታት ትንቢት ሲነገር : ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር : ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ : የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::
ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::
ከእርሱም ይስሐቅ : ከዚያም ያዕቆብ [ደጋጉ] ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ: በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ርሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::
በዚያም ለ፪ መቶ ፲፭ [215] ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::
ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ፱ መቅሰፍት: በ፲ኛ ሞተ በኩር: በ፲፩ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::
አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ:: እንዲህ እንዲህ እያለም ከኃያል ሰው ሶምሶን ረዓይታዊ ደረሱ:: ይኸውም ከዓለም ፍጥረት ፬ ሺህ ፪ መቶ [4,200] ዓመታት በሁዋላ መሆኑ ነው::
በጊዜው እሥራኤል ጣዖትን እያመለኩ እግዚአብሔርን ስላሳዘኑት ለጠላቶቻቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር:: የአካባቢው መንግስታት እነ አሞን: አማሌቅ: ኢሎፍሊ ስንኩዋ ያኔ ዛሬም ቢሆን እንደምትመለከቱት ዶሮና ጥሬ ናቸው::
በጊዜውም የእሥራኤል ኃጢአት ስለ በዛ ኢሎፍላውያን [ፍልስጤማውያን] ፵ [40] ዓመት በባርነት ገዟቸው:: ንስሃ ሲገቡ ደግሞ ልጅ በማጣት ያዘኑ ማኑሄ እና ሚስቱ [እንትኩይ] : በቅዱስ ሚካኤል ተበሥረው ኃያሉን ሶምሶንን ወለዱላቸው::
እርሱም ናዝራዊ [ከእናቱ ማኅጸን ለጌታ የተለየ] ነበርና ፍልስጤማውያንን ቀጥቶ ወገኖቹን እስራኤልን ከባርነት : በአምላኩ ኃይል ታደገ:: ከኃይሉ ብዛት የተነሳም :-
- አንበሳን እንደ ጠቦት ይገድል [መሣ.፲፬፥፭]
- 300 ቀበሮዎችን አባሮ ይይዝ [መሣ.፲፭፥፫]
- በብርቱ ገመዶች ሲያስሩት እንደ ፈትል ይበጣጥሰው [መሣ.፲፭፥፲፬]
- በአህያ መንጋጋ ሽህ ሰው ይገድል [መሣ.፲፭፥፲፭]
- ጠባቂዎችን ከነ መቃናቸው ተሸክሞ ይወረውር ነበር:: [መሣ.፲፮፥፫]
ውሃ ሲጠማውም ከአህያ መንጋጋ ላይ ፈልቆለት ጠጥቷል:: [መሣ.፲፭፥፲፰] በፍጻሜው ግን ደሊላ በምትባል ሴት ተታልሎ ምሥጢሩን በመግለጡና ጸጉሩ በመላጨቱ ኃይሉን አጥቷል:: ጠላቶቹም ዐይኑን አውጥተው መዘባበቻ አድርገውታል::
በፍጻሜው ግን ኃይሉ እንዲመለስለት ፈጣሪውን ለምኖ : አሕዛብ ለጣኦት በዓል እንደተሰበሰቡ የአዳራሹን ምሰሶ አፍርሶ አጥፍቷቸው ዐርፏል:: [መሣ.፲፫፥፲፮] ቅዱስ ሶምሶን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥላ [ምሳሌ] ነው::
† በዘመኑ ሁሉ ቅዱስ ሚካኤል ረድቶታልና በዚህች ቀን መታሠቢያው ይደረግለታል::
[ † 🕊 የካቲት ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ፴ ሺህ [ 30,000 ] ሰማዕታተ ኢትዮዽያ [ሮማዊው ፋሽስት የገደላቸው]
፪. ቅዱስ ሶምሶን ረዓይታዊ [የእስራኤል መስፍን]
፫. ቅዱስ አባ ገላስዮስ ገዳማዊ
፬. ቅድስት ዶርቃስ
[ † 🕊 ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት
፪. ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ድሜጥሮስ
፬. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ [ሰማዕት]
፮. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፯. አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
፰. ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ
† አምላከ አበው ቅዱሳን መዓዛ ቅድስናቸውን ያሳድርብን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::
† " ሶምሶንም :- 'ስለ ሁለቱ ዓይኖቼ ፍልስጥኤማውያንን አሁን እንድበቀል : እግዚአብሔር አምላክ ሆይ ! እባክህ አስበኝ ? አምላክ ሆይ ! . . . እባክህ አበርታኝ ?' ብሎ እግዚአብሔርን ጠራ:: . . . ሶምሶንም :- 'ከፍልስጤማውያን ጋር ልሙት' አለ:: ተጐንብሶም ምሰሶዎችን በሙሉ ኃይሉ ገፋ:: . . . በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ::" [መሣ.፲፮፥፳፰]
† " እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ . . ." † [ዕብ.፲፩፥፴፪]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለኢትዮዽያውያን ሰማዕታት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ኢትዮዽያውያን ሰማዕታት † 🕊
† በ፲፱፻፳፱ [1929] ዓ/ም: የካቲት ፲፪ [12] ቀን ከ፴ ሺህ [30,000] በላይ ኢትዮዽያውያን አባቶች : እናቶች : ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ደማቸው ፈሷል:: እነዚሕ ወገኖቻችን ደማቸው እንደ ጐርፍ አዲስ አበባ ላይ የፈሰሰው ስለ ሃገር ፍቅር ብቻ አልነበረም:: ስለ ቀናች ሃይማኖት ተዋሕዶ ጭምር ነው እንጂ::
† ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ግፃዌ ላይ ስማቸውን ጽፋ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር እንዲህ ታስባቸዋለች::
"አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ::
የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ::
ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት::
የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ::
የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት::
ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውሃ አፈሰሱ:: የሚቀብራቸውም አጡ::" [መዝ.፸፰፥፥፩]
† ሰማዕታቱን እናስባቸው !
🕊 † ሶምሶን ረዓይታዊ † 🕊
† እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን : ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ : በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ : ነቢይና ካህን አድርጐ : ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::
አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ፻ [100] ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::
ስለዚህም ምክንያት ለ፭ ሺሀ ፭ መቶ [5,500] ዓመታት ትንቢት ሲነገር : ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር : ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ : የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::
ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::
ከእርሱም ይስሐቅ : ከዚያም ያዕቆብ [ደጋጉ] ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ: በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ርሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::
በዚያም ለ፪ መቶ ፲፭ [215] ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::
ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ፱ መቅሰፍት: በ፲ኛ ሞተ በኩር: በ፲፩ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::
አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ:: እንዲህ እንዲህ እያለም ከኃያል ሰው ሶምሶን ረዓይታዊ ደረሱ:: ይኸውም ከዓለም ፍጥረት ፬ ሺህ ፪ መቶ [4,200] ዓመታት በሁዋላ መሆኑ ነው::
በጊዜው እሥራኤል ጣዖትን እያመለኩ እግዚአብሔርን ስላሳዘኑት ለጠላቶቻቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር:: የአካባቢው መንግስታት እነ አሞን: አማሌቅ: ኢሎፍሊ ስንኩዋ ያኔ ዛሬም ቢሆን እንደምትመለከቱት ዶሮና ጥሬ ናቸው::
በጊዜውም የእሥራኤል ኃጢአት ስለ በዛ ኢሎፍላውያን [ፍልስጤማውያን] ፵ [40] ዓመት በባርነት ገዟቸው:: ንስሃ ሲገቡ ደግሞ ልጅ በማጣት ያዘኑ ማኑሄ እና ሚስቱ [እንትኩይ] : በቅዱስ ሚካኤል ተበሥረው ኃያሉን ሶምሶንን ወለዱላቸው::
እርሱም ናዝራዊ [ከእናቱ ማኅጸን ለጌታ የተለየ] ነበርና ፍልስጤማውያንን ቀጥቶ ወገኖቹን እስራኤልን ከባርነት : በአምላኩ ኃይል ታደገ:: ከኃይሉ ብዛት የተነሳም :-
- አንበሳን እንደ ጠቦት ይገድል [መሣ.፲፬፥፭]
- 300 ቀበሮዎችን አባሮ ይይዝ [መሣ.፲፭፥፫]
- በብርቱ ገመዶች ሲያስሩት እንደ ፈትል ይበጣጥሰው [መሣ.፲፭፥፲፬]
- በአህያ መንጋጋ ሽህ ሰው ይገድል [መሣ.፲፭፥፲፭]
- ጠባቂዎችን ከነ መቃናቸው ተሸክሞ ይወረውር ነበር:: [መሣ.፲፮፥፫]
ውሃ ሲጠማውም ከአህያ መንጋጋ ላይ ፈልቆለት ጠጥቷል:: [መሣ.፲፭፥፲፰] በፍጻሜው ግን ደሊላ በምትባል ሴት ተታልሎ ምሥጢሩን በመግለጡና ጸጉሩ በመላጨቱ ኃይሉን አጥቷል:: ጠላቶቹም ዐይኑን አውጥተው መዘባበቻ አድርገውታል::
በፍጻሜው ግን ኃይሉ እንዲመለስለት ፈጣሪውን ለምኖ : አሕዛብ ለጣኦት በዓል እንደተሰበሰቡ የአዳራሹን ምሰሶ አፍርሶ አጥፍቷቸው ዐርፏል:: [መሣ.፲፫፥፲፮] ቅዱስ ሶምሶን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥላ [ምሳሌ] ነው::
† በዘመኑ ሁሉ ቅዱስ ሚካኤል ረድቶታልና በዚህች ቀን መታሠቢያው ይደረግለታል::
[ † 🕊 የካቲት ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ፴ ሺህ [ 30,000 ] ሰማዕታተ ኢትዮዽያ [ሮማዊው ፋሽስት የገደላቸው]
፪. ቅዱስ ሶምሶን ረዓይታዊ [የእስራኤል መስፍን]
፫. ቅዱስ አባ ገላስዮስ ገዳማዊ
፬. ቅድስት ዶርቃስ
[ † 🕊 ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት
፪. ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ድሜጥሮስ
፬. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ [ሰማዕት]
፮. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፯. አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
፰. ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ
† አምላከ አበው ቅዱሳን መዓዛ ቅድስናቸውን ያሳድርብን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::
† " ሶምሶንም :- 'ስለ ሁለቱ ዓይኖቼ ፍልስጥኤማውያንን አሁን እንድበቀል : እግዚአብሔር አምላክ ሆይ ! እባክህ አስበኝ ? አምላክ ሆይ ! . . . እባክህ አበርታኝ ?' ብሎ እግዚአብሔርን ጠራ:: . . . ሶምሶንም :- 'ከፍልስጤማውያን ጋር ልሙት' አለ:: ተጐንብሶም ምሰሶዎችን በሙሉ ኃይሉ ገፋ:: . . . በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ::" [መሣ.፲፮፥፳፰]
† " እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ . . ." † [ዕብ.፲፩፥፴፪]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍2🙏2