#ሚካኤል_ሆይ በጠላት ተማርከው
ለሚጨነቁትና ለሚሰቃዩት ዋስ
ጠበቃቸው አንተ ነህና በእኔ ለይ
የሚተበትቡትን የጠላቶቼን የምክር
መረብ በጣጥሰህ ጣልልኝ ነፍሴንም
ስጋዬንም ለአንተ አደራ ሰጥቼሀለሁና።
#ኃያሉ_ሚካኤል_ሆይ ኃይልህን የሰው
ኃይል ሊተካከለው አይችልምና
እንግደለው እናጥፋው የሚሉትን
ጠላቶቼን ጭጋግ በቀላቀለ በዓዉሎ
ንፋስ በትናቸው።
#ሰናይ__ቀን 🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
ለሚጨነቁትና ለሚሰቃዩት ዋስ
ጠበቃቸው አንተ ነህና በእኔ ለይ
የሚተበትቡትን የጠላቶቼን የምክር
መረብ በጣጥሰህ ጣልልኝ ነፍሴንም
ስጋዬንም ለአንተ አደራ ሰጥቼሀለሁና።
#ኃያሉ_ሚካኤል_ሆይ ኃይልህን የሰው
ኃይል ሊተካከለው አይችልምና
እንግደለው እናጥፋው የሚሉትን
ጠላቶቼን ጭጋግ በቀላቀለ በዓዉሎ
ንፋስ በትናቸው።
#ሰናይ__ቀን 🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤18🙏3👍2🥰2
🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
[ ❖ የካቲት ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
🕊 † ማር ፊቅጦር † 🕊
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በደማቸውና በገድላቸው ያስጌጡ ብዙ ሰማዕታት አሉ:: ነገር ግን ከኮከብም ኮከብ ይበልጣልና ማን እንደ ጊዮርጊስና እስጢፋኖስ ! ከእነርሱ ቀጥለው ከሚጠሩ ሰማዕታት ደግሞ አንዱና ዋነኛው ቤተ ክርስቲያን "ማር" የምትለው ቅዱስ ፊቅጦር ነው::
እስኪ ከበዛው መዓዛ-ገድሉ ጥቂት እንካፈል :-
- ቅዱስ ፊቅጦር አባቱ ኅርማኖስ ይባላል:: አረማዊና ጨካኝ ነው:: እናቱ ግን የተመሰገች ቅድስት ማርታ ትባላለች:: ልጇን እንደሚገባ አሳድጋው ፳ [ 20 ] ዓመት ሲሞላው የአንጾኪያ ንጉሥ የሠራዊት አለቃና በመንግሥቱ ፫ [3] ኛ አድርጐ ሾመው::
የድሮዋ አንጾኪያ [ሮም] እንደ ዛሬዋ አሜሪካ ዓለምን የተቆጣጠረች ሃገር ነበረች:: ቅዱስ ፊቅጦር ደም ግባቱ ያማረ: በጦርነትም ኃይለኛ ስለ ነበር ሁሉ ያከብሩት: ይወዱትም ነበር::
እርሱ ግን ቀን ቀን ሲጾም: ነዳያንን ሲያበላ ይውል ነበር:: ሌሊት ደግሞ እኩሉን ሲጸልይና ሲሰግድ እኩሉን የእስረኞችን እግር ሲያጥብ ያድር ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆንኮ እርሱ የንጉሡ ፫ [3] ኛ : የሠራዊትም አለቃ ነው:: በዘመኑ የሚያገድፍ ምግብና የወይን ጠጅ በአፉ ዙሮ አያውቅም::
ከነገር ሁሉ በሁዋላ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ካደ:: ዘመነ ሰማዕታትም ጀመረ:: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ:: ከ፵፯ [47] ሚሊየን በላይ ክርስቲያኖች በመንኮራኩር ተፈጩ:: በመጋዝ ተተረተሩ:: ለአራዊት ተሰጡ:: በግፍም ተጨፈጨፉ:: ቀባሪ አጥተውም ወደቁ::
በዚሕ ጊዜ ማር ፊቅጦር እናቱን ቅድስት ማርታን በዕንባ ተሰናብቶ ወደ ንጉሡ ቀርቦ በክርስቶስ ስም ታመነ:: ክፉ አባትም በልጁ ላይ ሞትን መከረ::
ከዚያም ቅዱሱን አፉን በብረት ለጉመው ወደ ምድረ ግብፅ አወረዱት:: መሪያቸው እንዳልነበረ ወታደሮቹ መኩዋንንቱ ሁሉ ተዘባበቱበት:: እርሱ ከምድራዊ ንግሥና ሰማያዊ መንግስትን: በሰዎች ፊት ከመክበር ስለ ክርስቶስ ሲል መናቅን መርጧልና::
ለቀናት : ለወራትና ለዓመታት መኩዋንንቱ እየተፈራረቁ አሰቃዩት:: በርሱ ላይ ያልሞከሩት የስቃይ ዓይነት አልነበረም:: አካሉን ቆራርጠዋል: ዓይኖቹን አውጥተዋል: ምላሱንም ቆርጠዋል:: ሚያዝያ ፳፯ [ 27 ] ቀን ግን በሰይፍ አንገቱን ቆርጠውታል:: ስለዚህም እናት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ማክበር ታከብረዋለች::
❖ እግዚአብሔርም ለቅዱስ ፊቅጦር እንዲህ አለው :-
" እንደ አቅሙ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ : ስምህን ያከበረ: የብርሃን ልብስ አጐናጽፌ ወደ መንግስተ ሰማያት አስገባዋለሁ::"
❖ ይህች ቀን ማር ፊቅጦር የተወለደባት ናት፡፡ እናቱን ቅድስት ማርታ [ ሶፍያንም ] እናስባለን፡፡
❖ ቸሩ አምላከ ፊቅጦር ሁላችንም ይማረን:: ከቃል ኪዳኑ አሳትፎ ለርስቱ ያብቃን::
✞ 🕊 ቅዱስ አውሳብዮስ ካልዕ [ጥዑመ ዜና] 🕊 ✞
ቅዱስ አውሳብዮስ በወጣትነቱ ከተባረከች ሚስቱ ጋ በድንግልና የኖረ ፥ በዘመኑ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ ይጸልይ ፥ ፬ ሺህ [4,000] አቡነ ዘበሰማያት በአንድ ቀን ያደርስ የነበረ : ስለ ሃይማኖትም በቀስት የተወጋ : በእሳት የቃጠለ : አካሉን ቆራርጠው የጣሉትና እግዚአብሔር ከሞት ያስነሳው ጻድቅና ሰማዕት ነው:: ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ከነሥጋው ወደ ሰማይ ተነጥቆ ለ፲፬ [14] ዓመታት ቆይቷል:: ወደ ምድርም ተመልሶ ለ፵ [40] ዓመታት በሐዋርያነት ከ፹፭ ሺህ [85,000] በላይ አሕዛብን ወደ ሃይማኖት መልሷል:: ጌታም በስምህ የተማጸነውን እስከ ፯ [7] ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎታል::"
❖ አባቶቻችን ደግሞ 'ስም አጠራሩ የከበረ ዜና ሕይወቱ ያማረ' ሲሉ ይጠሩታል::
❖ ከበረከቱ ያድለን::
[ ✞ የካቲት ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አውሳብዮስ ጻድቅ [ ጥዑመ ዜና ]
፪. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት [ ልደቱ ]
፫. ቅዱስ ሰርግዮስ ሰማዕት
፬. ቅዱስ መፁን ቀሲስ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት [ የቅ/ፋሲለደስ ልጅ ]
፮. አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
፯. አባ ክፍላ
፰. አባ ኅብስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. እግዚአብሔር አብ
፪. ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
፫. ፺፱ [ 99 ] ኙ ነገደ መላዕክት
፬. ቅዱስ አስከናፍር
፭. ፲፫ [ 13ቱ ] ግኁሳን አባቶች
፮. ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
፯. አቡነ ዘርዐ ቡሩክ
" እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ : እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ : ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::" [ዕብ.፮፥፲-፲፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
[ ❖ የካቲት ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
🕊 † ማር ፊቅጦር † 🕊
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በደማቸውና በገድላቸው ያስጌጡ ብዙ ሰማዕታት አሉ:: ነገር ግን ከኮከብም ኮከብ ይበልጣልና ማን እንደ ጊዮርጊስና እስጢፋኖስ ! ከእነርሱ ቀጥለው ከሚጠሩ ሰማዕታት ደግሞ አንዱና ዋነኛው ቤተ ክርስቲያን "ማር" የምትለው ቅዱስ ፊቅጦር ነው::
እስኪ ከበዛው መዓዛ-ገድሉ ጥቂት እንካፈል :-
- ቅዱስ ፊቅጦር አባቱ ኅርማኖስ ይባላል:: አረማዊና ጨካኝ ነው:: እናቱ ግን የተመሰገች ቅድስት ማርታ ትባላለች:: ልጇን እንደሚገባ አሳድጋው ፳ [ 20 ] ዓመት ሲሞላው የአንጾኪያ ንጉሥ የሠራዊት አለቃና በመንግሥቱ ፫ [3] ኛ አድርጐ ሾመው::
የድሮዋ አንጾኪያ [ሮም] እንደ ዛሬዋ አሜሪካ ዓለምን የተቆጣጠረች ሃገር ነበረች:: ቅዱስ ፊቅጦር ደም ግባቱ ያማረ: በጦርነትም ኃይለኛ ስለ ነበር ሁሉ ያከብሩት: ይወዱትም ነበር::
እርሱ ግን ቀን ቀን ሲጾም: ነዳያንን ሲያበላ ይውል ነበር:: ሌሊት ደግሞ እኩሉን ሲጸልይና ሲሰግድ እኩሉን የእስረኞችን እግር ሲያጥብ ያድር ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆንኮ እርሱ የንጉሡ ፫ [3] ኛ : የሠራዊትም አለቃ ነው:: በዘመኑ የሚያገድፍ ምግብና የወይን ጠጅ በአፉ ዙሮ አያውቅም::
ከነገር ሁሉ በሁዋላ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ካደ:: ዘመነ ሰማዕታትም ጀመረ:: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ:: ከ፵፯ [47] ሚሊየን በላይ ክርስቲያኖች በመንኮራኩር ተፈጩ:: በመጋዝ ተተረተሩ:: ለአራዊት ተሰጡ:: በግፍም ተጨፈጨፉ:: ቀባሪ አጥተውም ወደቁ::
በዚሕ ጊዜ ማር ፊቅጦር እናቱን ቅድስት ማርታን በዕንባ ተሰናብቶ ወደ ንጉሡ ቀርቦ በክርስቶስ ስም ታመነ:: ክፉ አባትም በልጁ ላይ ሞትን መከረ::
ከዚያም ቅዱሱን አፉን በብረት ለጉመው ወደ ምድረ ግብፅ አወረዱት:: መሪያቸው እንዳልነበረ ወታደሮቹ መኩዋንንቱ ሁሉ ተዘባበቱበት:: እርሱ ከምድራዊ ንግሥና ሰማያዊ መንግስትን: በሰዎች ፊት ከመክበር ስለ ክርስቶስ ሲል መናቅን መርጧልና::
ለቀናት : ለወራትና ለዓመታት መኩዋንንቱ እየተፈራረቁ አሰቃዩት:: በርሱ ላይ ያልሞከሩት የስቃይ ዓይነት አልነበረም:: አካሉን ቆራርጠዋል: ዓይኖቹን አውጥተዋል: ምላሱንም ቆርጠዋል:: ሚያዝያ ፳፯ [ 27 ] ቀን ግን በሰይፍ አንገቱን ቆርጠውታል:: ስለዚህም እናት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ማክበር ታከብረዋለች::
❖ እግዚአብሔርም ለቅዱስ ፊቅጦር እንዲህ አለው :-
" እንደ አቅሙ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ : ስምህን ያከበረ: የብርሃን ልብስ አጐናጽፌ ወደ መንግስተ ሰማያት አስገባዋለሁ::"
❖ ይህች ቀን ማር ፊቅጦር የተወለደባት ናት፡፡ እናቱን ቅድስት ማርታ [ ሶፍያንም ] እናስባለን፡፡
❖ ቸሩ አምላከ ፊቅጦር ሁላችንም ይማረን:: ከቃል ኪዳኑ አሳትፎ ለርስቱ ያብቃን::
✞ 🕊 ቅዱስ አውሳብዮስ ካልዕ [ጥዑመ ዜና] 🕊 ✞
ቅዱስ አውሳብዮስ በወጣትነቱ ከተባረከች ሚስቱ ጋ በድንግልና የኖረ ፥ በዘመኑ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ ይጸልይ ፥ ፬ ሺህ [4,000] አቡነ ዘበሰማያት በአንድ ቀን ያደርስ የነበረ : ስለ ሃይማኖትም በቀስት የተወጋ : በእሳት የቃጠለ : አካሉን ቆራርጠው የጣሉትና እግዚአብሔር ከሞት ያስነሳው ጻድቅና ሰማዕት ነው:: ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ከነሥጋው ወደ ሰማይ ተነጥቆ ለ፲፬ [14] ዓመታት ቆይቷል:: ወደ ምድርም ተመልሶ ለ፵ [40] ዓመታት በሐዋርያነት ከ፹፭ ሺህ [85,000] በላይ አሕዛብን ወደ ሃይማኖት መልሷል:: ጌታም በስምህ የተማጸነውን እስከ ፯ [7] ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎታል::"
❖ አባቶቻችን ደግሞ 'ስም አጠራሩ የከበረ ዜና ሕይወቱ ያማረ' ሲሉ ይጠሩታል::
❖ ከበረከቱ ያድለን::
[ ✞ የካቲት ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አውሳብዮስ ጻድቅ [ ጥዑመ ዜና ]
፪. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት [ ልደቱ ]
፫. ቅዱስ ሰርግዮስ ሰማዕት
፬. ቅዱስ መፁን ቀሲስ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት [ የቅ/ፋሲለደስ ልጅ ]
፮. አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
፯. አባ ክፍላ
፰. አባ ኅብስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. እግዚአብሔር አብ
፪. ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
፫. ፺፱ [ 99 ] ኙ ነገደ መላዕክት
፬. ቅዱስ አስከናፍር
፭. ፲፫ [ 13ቱ ] ግኁሳን አባቶች
፮. ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
፯. አቡነ ዘርዐ ቡሩክ
" እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ : እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ : ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::" [ዕብ.፮፥፲-፲፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤4👍1
ሰው ከእግዚአብሔር ሲለይ ፦
ዓይኑ ያልተፈቀደውን ሁሉ ያያል።
ምላሱ ሰውን አራጅና አዋራጅ ትሆናለች።
ጀሮው የሰውን ኃጢአትና ገመና ሰሚ ይሆናል።
እጆቹ የሰውን ንብረትና አካል ዘራፊ ይሆናሉ።
እግሮቹ ነፍስንና ስጋን ወደሚያበላሹ ቦታዎች ይሮጣሉ።
ስጋው የዝሙት ፈረስ ይሆናል።
ልቡ የፍርሀትና የጭንከት ከበሮ ይመታል።
አእምሮው የአጋንንትና የሰይጣናት መስሪያ ቤት ይሆናሉ።
#_ሰናይ_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
ዓይኑ ያልተፈቀደውን ሁሉ ያያል።
ምላሱ ሰውን አራጅና አዋራጅ ትሆናለች።
ጀሮው የሰውን ኃጢአትና ገመና ሰሚ ይሆናል።
እጆቹ የሰውን ንብረትና አካል ዘራፊ ይሆናሉ።
እግሮቹ ነፍስንና ስጋን ወደሚያበላሹ ቦታዎች ይሮጣሉ።
ስጋው የዝሙት ፈረስ ይሆናል።
ልቡ የፍርሀትና የጭንከት ከበሮ ይመታል።
አእምሮው የአጋንንትና የሰይጣናት መስሪያ ቤት ይሆናሉ።
#_ሰናይ_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤18💯1
🕊
[ † እንኳን ለታላቁ ሊቅና የተዋሕዶ ጠበቃ ቅዱስ ሳዊሮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ታላቁ ቅዱስ ሳዊሮስ † 🕊
† ቅዱስ ሳዊሮስ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሶርያ አንጾኪያ የተነሳ አባት ነው። ወቅቱ መለካውያን [ሁለት ባሕርይ ባዮች] የሰለጠኑበት እንደ መሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ያነሱበትና የሚሰደዱበት ጊዜ ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስ በሥላሴ ፈቃድ ለቤተ ክርስቲያን የተነሳው። ሊቃውንት አንበሳ ሲሉ ይጠሩታል።
ቅዱሱ ለተዋሕዶ ሃይማኖት ብዙ ሆኖላታል። የመናፍቃን ጸር በመሆኑ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል። ንጉሡን ዮስጢያኖስን [Justinian] ሳይቀር በይፋ ይገስጸው ነበርና ንጉሡ ሊገድለው ቆረጠ።
ሃይማኖቷ የቀና ንግሥቲቱ ታኦድራ ግን ይህንን ስትሰማ በሌሊት ወደ ሊቁ ሒዳ "እባክህን ሽሽ።" አለችው። እርሱ ግን "ሞት ለእኔ ክብር ነውና አልሔድም።" ሲል መለሰላት። አባቶችን ሰብስባ "ስለ ቤተ ክርስቲያን ስትል" ብለው ለምነው ወደ ግብጽ ሸኙት።
እርሱ እየሔደ ገዳዮቹ ያሳድዱት ገቡ። መንገድ ላይ ቢደርሱበትም ተሰወረባቸው። ለብዙ ቀናትም አብሯቸው ተጓዘ። እነርሱ ተስፋ ቆርጠው ሲመለሱ እርሱ ግን ምድረ ግብጽ ደረሰ።
በምድረ ግብጽም የጵጵስና ልብሱን ትቶ የመነኮሳትን አሮጌ ልብስ ለብሶ ሕዝቡንና መነኮሳቱን አስተማረ ፤ አጸና። በየቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠራ።
አባቶች መነኮሳትም ማንነቱን ባወቁ ጊዜ ሰገዱለት። ዶርታኦስ ]ዱራታኦስ ] በሚባል አንድ ደግ ሰው ቤትም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ የካቲት ፲፬ ቀን ዐርፏል።
† አምላከ ቅዱሳን ሊቃውንት የድንግል እመቤታችንን ጣዕሟን ፍቅሯን ያሳድርብን። የአበውን ሃብትና በረከትም አይንሳን።
[ † የካቲት ፲፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
፪. ቅዱስ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት
፫. አባ ያዕቆብ ሊቀ ጳጳሳት
፬. ቅዱስ ዳርዮስ
፭. ቅድስት ሊድና
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. አቡነ አረጋዊ [ ዘሚካኤል ]
፪. ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
፫. ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ሙሴ [ የእግዚአብሔር ሰው]
፭. አባ ስምዖን ገዳማዊ
፮. አባ ዮሐንስ ጻድቅ
፯. እናታችን ቅድስት ነሣሒት
† " ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" †
[ይሁዳ ፩፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለታላቁ ሊቅና የተዋሕዶ ጠበቃ ቅዱስ ሳዊሮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ታላቁ ቅዱስ ሳዊሮስ † 🕊
† ቅዱስ ሳዊሮስ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሶርያ አንጾኪያ የተነሳ አባት ነው። ወቅቱ መለካውያን [ሁለት ባሕርይ ባዮች] የሰለጠኑበት እንደ መሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ያነሱበትና የሚሰደዱበት ጊዜ ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስ በሥላሴ ፈቃድ ለቤተ ክርስቲያን የተነሳው። ሊቃውንት አንበሳ ሲሉ ይጠሩታል።
ቅዱሱ ለተዋሕዶ ሃይማኖት ብዙ ሆኖላታል። የመናፍቃን ጸር በመሆኑ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል። ንጉሡን ዮስጢያኖስን [Justinian] ሳይቀር በይፋ ይገስጸው ነበርና ንጉሡ ሊገድለው ቆረጠ።
ሃይማኖቷ የቀና ንግሥቲቱ ታኦድራ ግን ይህንን ስትሰማ በሌሊት ወደ ሊቁ ሒዳ "እባክህን ሽሽ።" አለችው። እርሱ ግን "ሞት ለእኔ ክብር ነውና አልሔድም።" ሲል መለሰላት። አባቶችን ሰብስባ "ስለ ቤተ ክርስቲያን ስትል" ብለው ለምነው ወደ ግብጽ ሸኙት።
እርሱ እየሔደ ገዳዮቹ ያሳድዱት ገቡ። መንገድ ላይ ቢደርሱበትም ተሰወረባቸው። ለብዙ ቀናትም አብሯቸው ተጓዘ። እነርሱ ተስፋ ቆርጠው ሲመለሱ እርሱ ግን ምድረ ግብጽ ደረሰ።
በምድረ ግብጽም የጵጵስና ልብሱን ትቶ የመነኮሳትን አሮጌ ልብስ ለብሶ ሕዝቡንና መነኮሳቱን አስተማረ ፤ አጸና። በየቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠራ።
አባቶች መነኮሳትም ማንነቱን ባወቁ ጊዜ ሰገዱለት። ዶርታኦስ ]ዱራታኦስ ] በሚባል አንድ ደግ ሰው ቤትም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ የካቲት ፲፬ ቀን ዐርፏል።
† አምላከ ቅዱሳን ሊቃውንት የድንግል እመቤታችንን ጣዕሟን ፍቅሯን ያሳድርብን። የአበውን ሃብትና በረከትም አይንሳን።
[ † የካቲት ፲፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
፪. ቅዱስ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት
፫. አባ ያዕቆብ ሊቀ ጳጳሳት
፬. ቅዱስ ዳርዮስ
፭. ቅድስት ሊድና
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. አቡነ አረጋዊ [ ዘሚካኤል ]
፪. ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
፫. ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ሙሴ [ የእግዚአብሔር ሰው]
፭. አባ ስምዖን ገዳማዊ
፮. አባ ዮሐንስ ጻድቅ
፯. እናታችን ቅድስት ነሣሒት
† " ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" †
[ይሁዳ ፩፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👏4
#__ወዳጄ
ከፍ ከፍ ትል ዘንድ #ትሑት ሁን፤ ባለጸጋ ትሆን ዘንድ #ድኻ ሁን፤ ትጠግብ ዘንድ #ረኃብን ውደዳት። ጤነኛ ትሆን ዘንድ የመብል ሸክምን አቅልል፤ ትከብር ዘንድ #ተዋረድ፤ ደስ ይልህ ዘንድ #አልቅስ፤ ትኖር ዘንድ #ሙት፤ ትበራ ዘንድ ትጋ። ትድን ዘንድ በማስተዋል #ጸልይ፤ ኃጢአትህን ይቅር ይልህ ዘንድ አብዝተህ #ጹም፤ ታገኝ ዘንድ #ፈልግ፤ ታተርፍ ዘንድ ለመነገድ ተፋጠን። ባለጸጋ ትሆን ዘንድ በብርሃናውያን መንገድ ትመላለስ ዘንድ #መስቀልህን ተሸከም፤ ሥጋህን ጥላት #ነፍስህን አንጻት።
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
ከፍ ከፍ ትል ዘንድ #ትሑት ሁን፤ ባለጸጋ ትሆን ዘንድ #ድኻ ሁን፤ ትጠግብ ዘንድ #ረኃብን ውደዳት። ጤነኛ ትሆን ዘንድ የመብል ሸክምን አቅልል፤ ትከብር ዘንድ #ተዋረድ፤ ደስ ይልህ ዘንድ #አልቅስ፤ ትኖር ዘንድ #ሙት፤ ትበራ ዘንድ ትጋ። ትድን ዘንድ በማስተዋል #ጸልይ፤ ኃጢአትህን ይቅር ይልህ ዘንድ አብዝተህ #ጹም፤ ታገኝ ዘንድ #ፈልግ፤ ታተርፍ ዘንድ ለመነገድ ተፋጠን። ባለጸጋ ትሆን ዘንድ በብርሃናውያን መንገድ ትመላለስ ዘንድ #መስቀልህን ተሸከም፤ ሥጋህን ጥላት #ነፍስህን አንጻት።
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤17👍2👏2
🕊
† እንኳን ለታላቁ ነቢይ ቅዱስ ዘካርያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ቅዱስ ዘካርያስ ነቢይ † 🕊
† ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር] : መጻዕያትን [ገና ለወደ ፊት የሚሆነውን] የሚያውቅ ሰው ማለት ነው:: ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው ደግሞ በጸጋ ይሰጠዋል:: እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ::
ዘመነ ነቢያት ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም:: በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ:: [ሐዋ.፲፩፥፳፯] ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ: ይገስጻሉ::
ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል::
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር : ወተናጸሩ ገጸ በገጽ::" እንዳለ አባ ሕርያቆስ:: [ቅዳሴ ማርያም]
የብዙ ነቢያት ፍጻሜአቸው መከራን መቀበል ነው:: እውነትን ስለ ተናገሩ: አንዳንዶቹም በእሳት: አንዳንዶቹም በሰይፍ: አንዳንዶቹም በመጋዝ ተፈትነዋል:: ሌሎቹ ለአናብስት ሲጣሉ ቀሪዎቹ ደግሞ በድንጋይ ተወግረዋል::
ስለዚህም መከራቸው ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ተብለዋል:: ጌታም ለደቀ መዛሙርቱ "ሌሎች ደከሙ:: እናንተ በድካማቸው ገባችሁ::" ብሎ የነቢያቱን መከራ ተናግሯል:: [ዮሐ.፬፥፴፮]
ነቢያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እና ድንግል እናቱን ለማየት ብዙ ጥረዋል:: ሽተዋልም:: "ብዙ ነቢያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ሹ" እንዳለ ጌታ በወንጌል:: [ማቴ.፲፫፥፲፮, ፩ጴጥ.፩፥፲] ዛሬ ግን በሰማያት ጸጋ በዝቶላቸው: ክብር ተሰጥቷቸው ሐሴትን ያደርጋሉ::
ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት "አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት" : "አራቱ ዐበይት ነቢያት" : "አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት" እና "ካልአን ነቢያት" ተብለው በ4 ይከፈላሉ::
† "አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት" ማለት :-
፩. ቅዱስ አዳም አባታችን
፪. ሴት
፫. ሔኖስ
፬. ቃይናን
፭. መላልኤል
፮. ያሬድ
፯. ኄኖክ
፰. ማቱሳላ
፱. ላሜሕ
፲. ኖኅ
፲፩. አብርሃም
፲፪. ይስሐቅ
፲፫. ያዕቆብ
፲፬. ሙሴ እና
፲፭. ሳሙኤል ናቸው::
† " አራቱ ዐበይት ነቢያት "
፩. ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል
፪. ቅዱስ ኤርምያስ
፫. ቅዱስ ሕዝቅኤል እና
፬. ቅዱስ ዳንኤል ናቸው::
† " አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት "
፩. ቅዱስ ሆሴዕ
፪. አሞጽ
፫. ሚክያስ
፬. ዮናስ
፭. ናሆም
፮. አብድዩ
፯. ሶፎንያስ
፰. ሐጌ
፱. ኢዩኤል
፲. ዕንባቆም
፲፩. ዘካርያስ እና
፲፪. ሚልክያስ ናቸው::
† " ካልአን ነቢያት " ደግሞ :-
- እነ ኢያሱ
- ሶምሶን
- ዮፍታሔ
- ጌዴዎን
- ዳዊት
- ሰሎሞን
- ኤልያስ እና
- ኤልሳዕ . . . ሌሎችም ናቸው::
† ነቢያት በከተማም ይከፈላሉ::
- የይሁዳ [ ኢየሩሳሌም ] :
- የሰማርያ [ እሥራኤል ] እና
- የባቢሎን [ በምርኮ ጊዜ ] ተብለው ይጠራሉ::
† በዘመን አከፋፈል ደግሞ :-
- ከአዳም እስከ ዮሴፍ [ የዘመነ አበው ነቢያት ] :
- ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ነቢዩ ሳሙኤል [ የዘመነ መሳፍንት ነቢያት ]
- ከቅዱስ ዳዊት እስከ ዘሩባቤል ያሉት [ የዘመነ ነገሥት ነቢያት ] :
- ከዘሩባቤል ዕረፍት እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ያሉት ደግሞ [ የዘመነ ካህናት ነቢያት ] ይባላሉ::
† ስለ ቅዱሳን ነቢያት በጥቂቱ ይህንን ካልን ወደ ዕለቱ በዓል እንመለስ::
† ቅዱስ ዘካርያስ ቁጥሩ ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን ዘመነ ትንቢቱም ቅ/ል/ክርስቶስ በ፬፻፶ [450] ዓ/ዓ አካባቢ ነው:: "ደቂቀ ነቢያት" ማለት በጥሬው "የነቢያት ልጆች" ማለት ነው:: አንድም የጻፏቸው ትንቢቶች ሲበዙ ፲፬ [14] ምዕራፍ: ሲያንስ አንድ ምዕራፍ ያላቸው ናቸውና ደቂቅ ይላቸዋል::
† ነቢዩ ቅዱስ ዘካርያስ :-
- ከክርስቶስ ልደት ፬፻፶ [450] ዓመታት በፊት የነበረ::
- በጻድቅነቱ የተመሰከረለት::
- ፲፬ [14] ምዕራፎች ያሉት ሐረገ - ትንቢት የተናገረ::
- ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ በስፋት የተነበየ ነቢይ ሲሆን ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያትም አንዱ ነው::
† የአባታችን በረከት ይደርብን::
🕊
[ † የካቲት ፲፭ [ 15 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዘካርያስ ነቢይ [ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ]
፪. ቅዱስ አባ በፍኑትዮስ ገዳማዊ [ከጻድቅነቱ ባሻገር በግብጽ በርሃ የሚኖሩ የብዙ ቅዱሳንን ዜና ሕይወት የጻፈ አባት ነው::]
፫. ቅዱሳን አርብዐ ሐራ ሰማይ [፵ [40] የሰማይ ጭፍሮች] ለ፵ [40] ቀናት ሰብስጥያ በምትባል ሃገር መከራ ተቀብለው በሰማዕትነት ያለፉ ክርስቲያን ጓደኛሞች::
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ
፪. ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ [አፈ በረከት]
፫. ቅዱስ ሚናስ ግብጻዊ
፬. ቅድስት እንባ መሪና
፭. ቅድስት ክርስጢና
† ". . . የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:: 'ወደ እኔ ተመለሱ . . . እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ::' " † [ዘካርያስ ፩፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
† እንኳን ለታላቁ ነቢይ ቅዱስ ዘካርያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ቅዱስ ዘካርያስ ነቢይ † 🕊
† ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር] : መጻዕያትን [ገና ለወደ ፊት የሚሆነውን] የሚያውቅ ሰው ማለት ነው:: ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው ደግሞ በጸጋ ይሰጠዋል:: እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ::
ዘመነ ነቢያት ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም:: በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ:: [ሐዋ.፲፩፥፳፯] ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ: ይገስጻሉ::
ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል::
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር : ወተናጸሩ ገጸ በገጽ::" እንዳለ አባ ሕርያቆስ:: [ቅዳሴ ማርያም]
የብዙ ነቢያት ፍጻሜአቸው መከራን መቀበል ነው:: እውነትን ስለ ተናገሩ: አንዳንዶቹም በእሳት: አንዳንዶቹም በሰይፍ: አንዳንዶቹም በመጋዝ ተፈትነዋል:: ሌሎቹ ለአናብስት ሲጣሉ ቀሪዎቹ ደግሞ በድንጋይ ተወግረዋል::
ስለዚህም መከራቸው ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ተብለዋል:: ጌታም ለደቀ መዛሙርቱ "ሌሎች ደከሙ:: እናንተ በድካማቸው ገባችሁ::" ብሎ የነቢያቱን መከራ ተናግሯል:: [ዮሐ.፬፥፴፮]
ነቢያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እና ድንግል እናቱን ለማየት ብዙ ጥረዋል:: ሽተዋልም:: "ብዙ ነቢያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ሹ" እንዳለ ጌታ በወንጌል:: [ማቴ.፲፫፥፲፮, ፩ጴጥ.፩፥፲] ዛሬ ግን በሰማያት ጸጋ በዝቶላቸው: ክብር ተሰጥቷቸው ሐሴትን ያደርጋሉ::
ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት "አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት" : "አራቱ ዐበይት ነቢያት" : "አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት" እና "ካልአን ነቢያት" ተብለው በ4 ይከፈላሉ::
† "አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት" ማለት :-
፩. ቅዱስ አዳም አባታችን
፪. ሴት
፫. ሔኖስ
፬. ቃይናን
፭. መላልኤል
፮. ያሬድ
፯. ኄኖክ
፰. ማቱሳላ
፱. ላሜሕ
፲. ኖኅ
፲፩. አብርሃም
፲፪. ይስሐቅ
፲፫. ያዕቆብ
፲፬. ሙሴ እና
፲፭. ሳሙኤል ናቸው::
† " አራቱ ዐበይት ነቢያት "
፩. ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል
፪. ቅዱስ ኤርምያስ
፫. ቅዱስ ሕዝቅኤል እና
፬. ቅዱስ ዳንኤል ናቸው::
† " አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት "
፩. ቅዱስ ሆሴዕ
፪. አሞጽ
፫. ሚክያስ
፬. ዮናስ
፭. ናሆም
፮. አብድዩ
፯. ሶፎንያስ
፰. ሐጌ
፱. ኢዩኤል
፲. ዕንባቆም
፲፩. ዘካርያስ እና
፲፪. ሚልክያስ ናቸው::
† " ካልአን ነቢያት " ደግሞ :-
- እነ ኢያሱ
- ሶምሶን
- ዮፍታሔ
- ጌዴዎን
- ዳዊት
- ሰሎሞን
- ኤልያስ እና
- ኤልሳዕ . . . ሌሎችም ናቸው::
† ነቢያት በከተማም ይከፈላሉ::
- የይሁዳ [ ኢየሩሳሌም ] :
- የሰማርያ [ እሥራኤል ] እና
- የባቢሎን [ በምርኮ ጊዜ ] ተብለው ይጠራሉ::
† በዘመን አከፋፈል ደግሞ :-
- ከአዳም እስከ ዮሴፍ [ የዘመነ አበው ነቢያት ] :
- ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ነቢዩ ሳሙኤል [ የዘመነ መሳፍንት ነቢያት ]
- ከቅዱስ ዳዊት እስከ ዘሩባቤል ያሉት [ የዘመነ ነገሥት ነቢያት ] :
- ከዘሩባቤል ዕረፍት እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ያሉት ደግሞ [ የዘመነ ካህናት ነቢያት ] ይባላሉ::
† ስለ ቅዱሳን ነቢያት በጥቂቱ ይህንን ካልን ወደ ዕለቱ በዓል እንመለስ::
† ቅዱስ ዘካርያስ ቁጥሩ ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን ዘመነ ትንቢቱም ቅ/ል/ክርስቶስ በ፬፻፶ [450] ዓ/ዓ አካባቢ ነው:: "ደቂቀ ነቢያት" ማለት በጥሬው "የነቢያት ልጆች" ማለት ነው:: አንድም የጻፏቸው ትንቢቶች ሲበዙ ፲፬ [14] ምዕራፍ: ሲያንስ አንድ ምዕራፍ ያላቸው ናቸውና ደቂቅ ይላቸዋል::
† ነቢዩ ቅዱስ ዘካርያስ :-
- ከክርስቶስ ልደት ፬፻፶ [450] ዓመታት በፊት የነበረ::
- በጻድቅነቱ የተመሰከረለት::
- ፲፬ [14] ምዕራፎች ያሉት ሐረገ - ትንቢት የተናገረ::
- ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ በስፋት የተነበየ ነቢይ ሲሆን ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያትም አንዱ ነው::
† የአባታችን በረከት ይደርብን::
🕊
[ † የካቲት ፲፭ [ 15 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዘካርያስ ነቢይ [ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ]
፪. ቅዱስ አባ በፍኑትዮስ ገዳማዊ [ከጻድቅነቱ ባሻገር በግብጽ በርሃ የሚኖሩ የብዙ ቅዱሳንን ዜና ሕይወት የጻፈ አባት ነው::]
፫. ቅዱሳን አርብዐ ሐራ ሰማይ [፵ [40] የሰማይ ጭፍሮች] ለ፵ [40] ቀናት ሰብስጥያ በምትባል ሃገር መከራ ተቀብለው በሰማዕትነት ያለፉ ክርስቲያን ጓደኛሞች::
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ
፪. ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ [አፈ በረከት]
፫. ቅዱስ ሚናስ ግብጻዊ
፬. ቅድስት እንባ መሪና
፭. ቅድስት ክርስጢና
† ". . . የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:: 'ወደ እኔ ተመለሱ . . . እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ::' " † [ዘካርያስ ፩፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍1