ጌታ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውሃ ወጣ።
እነሆም ሰማያት ተከፈቱ። የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ፡ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ። እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ ፦'በእርሱ ደስ
የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
📖ማቴ ፫፡፲፮
#በወንጌሉ_ላመናችሁ_እንኳን_
#ለብርሃነ_ጥምቀቱ_አደረሳችሁ🙏🙏🙏
#መልካም_የጥምቀት_በዓል🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
እነሆም ሰማያት ተከፈቱ። የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ፡ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ። እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ ፦'በእርሱ ደስ
የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
📖ማቴ ፫፡፲፮
#በወንጌሉ_ላመናችሁ_እንኳን_
#ለብርሃነ_ጥምቀቱ_አደረሳችሁ🙏🙏🙏
#መልካም_የጥምቀት_በዓል🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤9
#እንኳን_አደረሳቹ_በዓለ_ጥምቀት...
ጌታችንም በባርያው እጅ
ትኅትናው ይነገርለታል። ጌታችን #በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም። ምክንያቱም እርሱ እከብር አይል ክቡር፣ እጸድቅ አይል ጻድቅ
ነውና። ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን ምን እያለ እንደሚያጠምቅ አልገባውም
ነበር፡ በዚህም ምከንያት ጌታችንን “ጌታ ሆይ ሌላውን በአንተ ስም በባሕርይ አባትህ በአብ ስም፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱሰ ስም አጠምቃለሁ። አንተንስ የማጠምቀው
በማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። ጌታችንም “ወልዱ ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ እግዚኦ፣ አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከጼዴቅ፣ የቡሩክ አብ ልጅ ቡሩክ ወልድ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን። እንደ መልከጼዴቅ ክህነት አንተ
ለዘለዓለም ካህን ነህ” እያልክ አጥምቀኝ ብሎታል።
#ጌታችን_በተጠመቀ ጊዜ ምሥጢረ ሥላሴ ተገልጧል። መንፈስ
ቅዱስ በተለየ አካሉ በርግብ አምሳል ወረደ፤ አብም በተለየ አካሉ በደመና ሆኖ በማዕከለ ዮርዳኖስ የቆመውን ኢየሱስ
ክርስቶስን መለኮትን ከሥጋ ሳይለያይ አንድ አድርጎ “የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” አለ። ምክንያቱም በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ በዮርዳኖስ የቆመው ኢየሲስ ክርስቶስ በተዋሕዶ አንድ
አካል አንድ ባሕርይ ሆኖአልና። ተገልጦ የማያውቅ ምሥጢር ተገልጧል። የመንግሥተ ሰማያት በር ይከፈትላችኋል ማለት ነው።
#እንኳን_ለጌታችን_ለመድሃኒታችን
ለእየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ🙏
#መልካም_የጥምቀት_በዓል🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
ጌታችንም በባርያው እጅ
ትኅትናው ይነገርለታል። ጌታችን #በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም። ምክንያቱም እርሱ እከብር አይል ክቡር፣ እጸድቅ አይል ጻድቅ
ነውና። ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን ምን እያለ እንደሚያጠምቅ አልገባውም
ነበር፡ በዚህም ምከንያት ጌታችንን “ጌታ ሆይ ሌላውን በአንተ ስም በባሕርይ አባትህ በአብ ስም፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱሰ ስም አጠምቃለሁ። አንተንስ የማጠምቀው
በማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። ጌታችንም “ወልዱ ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ እግዚኦ፣ አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከጼዴቅ፣ የቡሩክ አብ ልጅ ቡሩክ ወልድ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን። እንደ መልከጼዴቅ ክህነት አንተ
ለዘለዓለም ካህን ነህ” እያልክ አጥምቀኝ ብሎታል።
#ጌታችን_በተጠመቀ ጊዜ ምሥጢረ ሥላሴ ተገልጧል። መንፈስ
ቅዱስ በተለየ አካሉ በርግብ አምሳል ወረደ፤ አብም በተለየ አካሉ በደመና ሆኖ በማዕከለ ዮርዳኖስ የቆመውን ኢየሱስ
ክርስቶስን መለኮትን ከሥጋ ሳይለያይ አንድ አድርጎ “የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” አለ። ምክንያቱም በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ በዮርዳኖስ የቆመው ኢየሲስ ክርስቶስ በተዋሕዶ አንድ
አካል አንድ ባሕርይ ሆኖአልና። ተገልጦ የማያውቅ ምሥጢር ተገልጧል። የመንግሥተ ሰማያት በር ይከፈትላችኋል ማለት ነው።
#እንኳን_ለጌታችን_ለመድሃኒታችን
ለእየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ🙏
#መልካም_የጥምቀት_በዓል🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤8
† † †
❝ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ። ❞ — [ ማቴዎስ ፫፥፲፫ ]
🕊 💖 🕊
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ
Congratulations on the baptism of our Lord and Savior Jesus Christ in peace and health
Baga gooftaa fi fayyisaa keenya Iyyasuus Kiristoos nagaa fi fayyaan cuuphame
እንኳዕ ጥምቀት ጎይታናን መድሓኒናን ኢየሱስ ክርስቶስ ብሰላምን ብጥዕናን ኣብጽሓና።
تهانينا على معمودية ربنا ومخلصنا يسوع المسيح بسلام وصحة
Félicitations pour le baptême de notre Seigneur et Sauveur Jésus-Christ dans la paix et la santé
Herzlichen Glückwunsch zur Taufe unseres Herrn und Erlösers Jesus Christus in Frieden und Gesundheit
[ TMC ]
🕊
[ 🕊 ተ ዋ ሕ ዶ ሰ ማ ያ ዊ ት 🕊 ]
[ O R T H O D O X Y ! ]
† † †
💖 🕊 💖
❝ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ። ❞ — [ ማቴዎስ ፫፥፲፫ ]
🕊 💖 🕊
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ
Congratulations on the baptism of our Lord and Savior Jesus Christ in peace and health
Baga gooftaa fi fayyisaa keenya Iyyasuus Kiristoos nagaa fi fayyaan cuuphame
እንኳዕ ጥምቀት ጎይታናን መድሓኒናን ኢየሱስ ክርስቶስ ብሰላምን ብጥዕናን ኣብጽሓና።
تهانينا على معمودية ربنا ومخلصنا يسوع المسيح بسلام وصحة
Félicitations pour le baptême de notre Seigneur et Sauveur Jésus-Christ dans la paix et la santé
Herzlichen Glückwunsch zur Taufe unseres Herrn und Erlösers Jesus Christus in Frieden und Gesundheit
[ TMC ]
🕊
[ 🕊 ተ ዋ ሕ ዶ ሰ ማ ያ ዊ ት 🕊 ]
[ O R T H O D O X Y ! ]
† † †
💖 🕊 💖
❤5👍1
#የጭንቀት_ቀን ሳይመጣ #በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ። ደስ አያሰኙም የምትላቸው አመታት ሳይደርሱ፣ ፀሀይ ጨረቃ ከዋክብት ሳይጨልሙ... አፈርም ወደነበረበት ምድር ሳይመለስ፣ ነፍስም ወደሰጠው ወደ #እግዚአብሔር ሳትመለስ ፈጣሪህን አስብ
መክ 12፡ 1-9
#በወንጌሉ_ላመናችሁ_እንኳን_ለብርሃነ
ጥምቀቱ_አደረሳችሁ🙏🙏🙏🙏🙏
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
መክ 12፡ 1-9
#በወንጌሉ_ላመናችሁ_እንኳን_ለብርሃነ
ጥምቀቱ_አደረሳችሁ🙏🙏🙏🙏🙏
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤17👍1
🕊
[ 💖 ORTHODOXY 💖 ]
† † †
ፕሬዝዳንት ፑቲንን ጨምሮ በርካታ ሩሲያውያን ጥምቀትን በተለያዩ ስፍራዎች አክብረዋል
ከ ፺ [ 90 ] ሚሊዮን በላይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ያሏት ሩሲያም የጥምቀት በዓልን በድምቀት ከሚያከብሩ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ነች።
የሩሲያ ኦርቶዶክስ [ ምስራቃውያን ] እምነት ተከታዮች ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ መጠመቅን እና ምስጢረ ሥላሴን መሠረት በማድረግ በበረዶ ውሃ ውስጥ ራሳቸውን ሶስት ጊዜ ይነከራሉ።
† † †
💖 🕊 💖
[ 💖 ORTHODOXY 💖 ]
† † †
ፕሬዝዳንት ፑቲንን ጨምሮ በርካታ ሩሲያውያን ጥምቀትን በተለያዩ ስፍራዎች አክብረዋል
ከ ፺ [ 90 ] ሚሊዮን በላይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ያሏት ሩሲያም የጥምቀት በዓልን በድምቀት ከሚያከብሩ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ነች።
የሩሲያ ኦርቶዶክስ [ ምስራቃውያን ] እምነት ተከታዮች ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ መጠመቅን እና ምስጢረ ሥላሴን መሠረት በማድረግ በበረዶ ውሃ ውስጥ ራሳቸውን ሶስት ጊዜ ይነከራሉ።
† † †
💖 🕊 💖
❤3
🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
🕊 † እንኳን አደረሰን † 🕊
ጥር ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
🕊 † ቃና ዘገሊላ † 🕊
'ቃና' የሚለው ቃል በሃገራችን ልሳን [ በአማርኛ ] የምግብን: የመጠጥን ጥፍጥና ወይም በጐ መዓዛን የሚያመለክት ነው:: ምንአልባትም ከዚህ በዓል ምሥጢር የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም::
- በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ግን ቃና ከገሊላ አውራጃዎች አንዷ ናት:: ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚህች ሥፍራ ተገኝቶ በድንግል እናቱ ምልጃ ታላቅ ተአምርን በዚህች ዕለት ሠርቷል::
- ተአምር የሚለውን ቃል በቁሙ 'ምልክት' ብሎ መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ [ በላይ ] : ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ [ ሲፈጸም ] ተአምር ይባላል:: ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው::
- ስለዚህም ነው 'ኤልሻዳይ [ ከሐሌ ኩሉ ] ሁሉን ቻይ' እያልን የምንጠራው:: እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ [ ኦሪትን ተመልከት ] እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ [ ፩ኛ ነገሥትን ተመልከት ] እንደ ነበር
ይታወቃል::
- እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: [ ማቴ.፲፥፰ , ፲፯፥፳ , ማር.፲፮፥፲፯ , ሉቃ.፲፥፲፯ ]
- እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: [ሐዋ.፫፥፮ , ፭፥፩ , ፭፥፲፪ , ፰፥፮ , ፱፥፴፫-፵፫ , ፲፬፥፰ , ፲፱፥፲፩ ]
- ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በወንጌሉ ምዕራፍ ፪ ላይ እንዳስቀመጠው የቃና ዘገሊላው ተአምር የመጀመሪያው ነው:: "ወዝንቱ ቀዳሜ ተአምር ዘገብረ . . ." እንዲል:: [ዮሐ.፪፥፲፩] ያ ማለት ግን ጌታ ከዚያ በፊት ተአምራትን አልሠራም ማለት አይደለም::
ይልቁኑ ራሱን ከገለጠና ከተጠመቀ በኋላ የሠራው የመጀመሪያው ተአምር ነው ሲል ነው እንጂ:: ምክንያቱም መድኃኒታችን እንደ ተጠመቀ ዕለቱኑ ገዳመ ቆረንቶስ ገብቷልና:: [ማቴ.፬፥፩] አንድም በቃና ሌሎች ተአምራትን የሚሠራ ነውና ይህ ተአምር በቃና የመጀመሪያው ሆነ::
- ትክክለኛው የቃና ዘገሊላ ቀን የካቲት ፳፫ ነው:: ጥር ፲፩ ተጠምቆ : የካቲት ፳፩ ቀን ከጾም ተመልሷል:: ከዚያም የካቲት ፳፫ ቀን ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ ሒዷል:: ነገር ግን አበው መንፈስ ቅዱስ እንደ መራቸው የውሃ በዓል ከውሃ በዓል ጋር ይስማማል ብለው ጥር ፲፪ ቀን አድርገውታል::
- በቃና ዘገሊላ ሙሽራው ዶኪማስ ሲሆን ባለ ሠርጉ ደግሞ አባቱ ዮአኪን ነው:: ይህም ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል አጐቱ ነው:: የልጁ ጋብቻ የተቀደሰ ይሆን ዘንድም ጌታ ክርስቶስን: ድንግል እናቱንና ባለሟሎቹ ሐዋርያትን ወደ ሠርጉ ጠራ::
- ምንም እንኳ መድኃኒታችንና እመቤታችን ከድግሱ የማይበሉ ቢሆኑም [በትሕርምት ኗሪዎች ነበሩና] ጠሪውን ደስ ለማሰኘት ሠርጉን [ብቻውን] ለመቀደስና የጋብቻን ክቡርነት ለማሳየት አብረው ታደሙ::
የሠርጉ ሥነ ሥርዓት ሲጀመር በድንኳኑ ውስጥ ጌታ ከመካከል ተቀመጠ:: ድንግል በቀኙ: ዮሐንስ በግራው ሲቀመጡ: ሌሎች ሐዋርያት ግራና ቀኝ ከበው ተቀመጡ:: ሲበላና ሲጠጣ ድንገት የተደገሰው ምግብና መጠጥ አለቀ:: ደጋሾቹ በጭንቅ ላይ ሳሉም አይጠና ሆዷ ድንግል እመ ብርሃን የሆነውን አወቀች:: እንዴት አወቀች ቢሉ :- በጸጋ: አንድም 'ከልጅሽ አማልጂን' ብለው ቢለምኗት ነው ይሏል:: እመቤታችን በዚያ ጊዜ ወደ ልጇ ቀርባ ቸር ልጇን "ወይንኬ አልቦሙ ወይኑኮ አልቆባቸዋል" አለችው::
- ለጊዜው ወይኑም: ምግቡም ስላለቀባቸው እንዲህ አለች:: በምሥጢሩ ግን ወይን ያለችው ፍቅርን: ቅዱስ ቃሉንና ክቡር ደሙን ነው:: ጌታም ይመልሳል :- "ምንት ብየ ምስሌኪ ኦ ብእሲቶ: ዓዲ ኢበጽሐ ጊዜየ-አንቺ ሆይ ! [ እናቴ ሆይ ! ] ያልሺኚን አላደርግ ዘንድ ካንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ ? ነገር ግን ጊዜው ገና አልደረሰም ብየ ነው እንጂ" አላት:: ምክንያቱም ጌታ :-
- የወይን ጋኖቹ እስኪያልቁ ይጠብቅ ነበር:: [ አበረከተ ይሉታልና ]
- አንድም ይሁዳ ወጥቶ ነበርና እርሱ እስኪመለስ ነው:: [ እኔ ስወጣ ጠብቆ ተአምር ሠራ ብሎ ለክፋቱ ምክንያት እንዳያቀርብ ] አንድም "ወይን [ ቅዱስ ደሜን ] የምሰጠው በቀራንዮ አንባ ነው" ሲል "ጊዜየ ገና ነው" ብሏታል:: አንዳንድ ልቡናቸው የጠፋ ወገኖቻችን ጌታ እመቤታችንን እንዳቃለላት [ ሎቱ ስብሐት ! ወላቲ ስብሐት ! ] አስመስለው ይናገራሉ::
- ይህንን ስእንኅን ጌታ ባለጌዎቹ እነሱም አያደርጉት:: "አባትህንና እናትህን አክብር" [ዘጸ.፳] ያለ ጌታ እንዴት ለእናቱ ክብርን ይነፍጋል ? ልቡና ይስጠን !
ወደ ጉዳያችን ስንመለስ መድኃኒታችን እንዲህ ሲል መለስላት:: ተግባብተዋልና እመ ብርሃን አሳላፊዎቹን "ኩሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ -የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው:: [ ዮሐ.፪፤፥፭ ] ጌታም በ፮ቱ ጋኖች ውሃ አስሞልቶ በተአምራት ወይን አደረጋቸው::
- እንጀራውን ወጡን በየሥፍራው ሞላው:: ታላቅ ደስታም ሆነ:: የአሳላፊዎቹ አለቃም [ለአባታችን አብርሃም ምሳሌ ነው] ከወይኑ ጥፍጥና የተነሳ አደነቀ:: በዚህም የድንግል ማርያም አማላጅነት: የመድኃኒታችን ከሃሊነት ታወቀ: ተገለጠ::
🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ርዕሰ አበው † 🕊
- የአባቶች አለቃ የተሰኘ ቅዱስ ያዕቆብ ለ፪ቱ ታላላቅ አባቶቹ እርሱ ፫ተኛቸው ነው:: እነርሱን መስሎ: እነርሱንም አህሎ በጐዳናቸው ተጉዟል:: በፈቃደ እግዚአብሔር ብኩርናን ከኤሳው ተቀብሎ ወደ ሶርያ ሲሸሽ ቤቴል [ ፍኖተ ሎዛ ] ላይ ድንጋይ ተንተርሶ በተኛበት ግሩም ራዕይን አይቷል::
- ይህችውም የወርቅ መሰላል የድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::
"አንቲ ውዕቱ ሰዋስው ዘርእየ ያዕቆብ" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም [ ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ ]
- ተነስቶም "ዛቲ ይእቲ ኈኅታ ለሰማይ: ዝየ ይትሐነጽ ቤተ እግዚአብሔር - ይህች የሰማይ ደጅ ናት: ቤተ እግዚአብሔርም ይታነጽባታል" ብሎ ትንቢት ተናግሯል::
- ይህ ቅዱስ አባት ለድንግል ማርያም ቅድመ አያት ከመሆኑ ባሻገር ነቢያትን: ካህናትን: ነገሥታትንና መሣፍንትን ወልዷል:: ከ፪ቱ ሚስቶቹ [ልያና ራሔል] : ከ፪ቱ ደንገጥሮች ፲፪ ልጆችን ወልዷል::
- ከአጐቱ ከላባ ዘንድ ለ፳፩ ዓመታት አገልግሎ: ሃብት ንብረቱን ጠቅልሎ ወደ ርስቱ ከነዓን ሲመለስ ለብቻው ራቅ ብሎ ይጸልይ ገባ:: በዚያም እግዚአብሔር ሲታገለው አደረ::
[ ይኸውም የፍቅርና የምሥጢር ነው ] ለጊዜው ጌታ ያዕቆብን "ልቀቀኝ" ቢለው "ካልባረከኝ አለቅህም" አለው:: ጌታም ስሙን "እሥራኤል" ብሎ ባርኮታል::
- ቅዱስ ያዕቆብ በስተእርጅና ብዙ መከራ አግኝቶታል:: ልጁን ዮሴፍን ወንድሞቹ ሽጠው "አውሬ በላው" ብለውታልና በለቅሶ ዐይኑ ጠፋ::
- በረሃብ ምክንያትም በ፻፴ ዓመቱ ከ፸፭ ያህል ቤተሰቦቹ ጋር ወደ ግብጽ ወረደ:: በዚያም ለ፯ ዓመታት ኑሮ በ፻፴፯ ዓመቱ ዐርፏል:: ልጆቹም ቀብረውታል::
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
🕊 † እንኳን አደረሰን † 🕊
ጥር ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
🕊 † ቃና ዘገሊላ † 🕊
'ቃና' የሚለው ቃል በሃገራችን ልሳን [ በአማርኛ ] የምግብን: የመጠጥን ጥፍጥና ወይም በጐ መዓዛን የሚያመለክት ነው:: ምንአልባትም ከዚህ በዓል ምሥጢር የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም::
- በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ግን ቃና ከገሊላ አውራጃዎች አንዷ ናት:: ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚህች ሥፍራ ተገኝቶ በድንግል እናቱ ምልጃ ታላቅ ተአምርን በዚህች ዕለት ሠርቷል::
- ተአምር የሚለውን ቃል በቁሙ 'ምልክት' ብሎ መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ [ በላይ ] : ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ [ ሲፈጸም ] ተአምር ይባላል:: ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው::
- ስለዚህም ነው 'ኤልሻዳይ [ ከሐሌ ኩሉ ] ሁሉን ቻይ' እያልን የምንጠራው:: እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ [ ኦሪትን ተመልከት ] እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ [ ፩ኛ ነገሥትን ተመልከት ] እንደ ነበር
ይታወቃል::
- እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: [ ማቴ.፲፥፰ , ፲፯፥፳ , ማር.፲፮፥፲፯ , ሉቃ.፲፥፲፯ ]
- እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: [ሐዋ.፫፥፮ , ፭፥፩ , ፭፥፲፪ , ፰፥፮ , ፱፥፴፫-፵፫ , ፲፬፥፰ , ፲፱፥፲፩ ]
- ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በወንጌሉ ምዕራፍ ፪ ላይ እንዳስቀመጠው የቃና ዘገሊላው ተአምር የመጀመሪያው ነው:: "ወዝንቱ ቀዳሜ ተአምር ዘገብረ . . ." እንዲል:: [ዮሐ.፪፥፲፩] ያ ማለት ግን ጌታ ከዚያ በፊት ተአምራትን አልሠራም ማለት አይደለም::
ይልቁኑ ራሱን ከገለጠና ከተጠመቀ በኋላ የሠራው የመጀመሪያው ተአምር ነው ሲል ነው እንጂ:: ምክንያቱም መድኃኒታችን እንደ ተጠመቀ ዕለቱኑ ገዳመ ቆረንቶስ ገብቷልና:: [ማቴ.፬፥፩] አንድም በቃና ሌሎች ተአምራትን የሚሠራ ነውና ይህ ተአምር በቃና የመጀመሪያው ሆነ::
- ትክክለኛው የቃና ዘገሊላ ቀን የካቲት ፳፫ ነው:: ጥር ፲፩ ተጠምቆ : የካቲት ፳፩ ቀን ከጾም ተመልሷል:: ከዚያም የካቲት ፳፫ ቀን ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ ሒዷል:: ነገር ግን አበው መንፈስ ቅዱስ እንደ መራቸው የውሃ በዓል ከውሃ በዓል ጋር ይስማማል ብለው ጥር ፲፪ ቀን አድርገውታል::
- በቃና ዘገሊላ ሙሽራው ዶኪማስ ሲሆን ባለ ሠርጉ ደግሞ አባቱ ዮአኪን ነው:: ይህም ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል አጐቱ ነው:: የልጁ ጋብቻ የተቀደሰ ይሆን ዘንድም ጌታ ክርስቶስን: ድንግል እናቱንና ባለሟሎቹ ሐዋርያትን ወደ ሠርጉ ጠራ::
- ምንም እንኳ መድኃኒታችንና እመቤታችን ከድግሱ የማይበሉ ቢሆኑም [በትሕርምት ኗሪዎች ነበሩና] ጠሪውን ደስ ለማሰኘት ሠርጉን [ብቻውን] ለመቀደስና የጋብቻን ክቡርነት ለማሳየት አብረው ታደሙ::
የሠርጉ ሥነ ሥርዓት ሲጀመር በድንኳኑ ውስጥ ጌታ ከመካከል ተቀመጠ:: ድንግል በቀኙ: ዮሐንስ በግራው ሲቀመጡ: ሌሎች ሐዋርያት ግራና ቀኝ ከበው ተቀመጡ:: ሲበላና ሲጠጣ ድንገት የተደገሰው ምግብና መጠጥ አለቀ:: ደጋሾቹ በጭንቅ ላይ ሳሉም አይጠና ሆዷ ድንግል እመ ብርሃን የሆነውን አወቀች:: እንዴት አወቀች ቢሉ :- በጸጋ: አንድም 'ከልጅሽ አማልጂን' ብለው ቢለምኗት ነው ይሏል:: እመቤታችን በዚያ ጊዜ ወደ ልጇ ቀርባ ቸር ልጇን "ወይንኬ አልቦሙ ወይኑኮ አልቆባቸዋል" አለችው::
- ለጊዜው ወይኑም: ምግቡም ስላለቀባቸው እንዲህ አለች:: በምሥጢሩ ግን ወይን ያለችው ፍቅርን: ቅዱስ ቃሉንና ክቡር ደሙን ነው:: ጌታም ይመልሳል :- "ምንት ብየ ምስሌኪ ኦ ብእሲቶ: ዓዲ ኢበጽሐ ጊዜየ-አንቺ ሆይ ! [ እናቴ ሆይ ! ] ያልሺኚን አላደርግ ዘንድ ካንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ ? ነገር ግን ጊዜው ገና አልደረሰም ብየ ነው እንጂ" አላት:: ምክንያቱም ጌታ :-
- የወይን ጋኖቹ እስኪያልቁ ይጠብቅ ነበር:: [ አበረከተ ይሉታልና ]
- አንድም ይሁዳ ወጥቶ ነበርና እርሱ እስኪመለስ ነው:: [ እኔ ስወጣ ጠብቆ ተአምር ሠራ ብሎ ለክፋቱ ምክንያት እንዳያቀርብ ] አንድም "ወይን [ ቅዱስ ደሜን ] የምሰጠው በቀራንዮ አንባ ነው" ሲል "ጊዜየ ገና ነው" ብሏታል:: አንዳንድ ልቡናቸው የጠፋ ወገኖቻችን ጌታ እመቤታችንን እንዳቃለላት [ ሎቱ ስብሐት ! ወላቲ ስብሐት ! ] አስመስለው ይናገራሉ::
- ይህንን ስእንኅን ጌታ ባለጌዎቹ እነሱም አያደርጉት:: "አባትህንና እናትህን አክብር" [ዘጸ.፳] ያለ ጌታ እንዴት ለእናቱ ክብርን ይነፍጋል ? ልቡና ይስጠን !
ወደ ጉዳያችን ስንመለስ መድኃኒታችን እንዲህ ሲል መለስላት:: ተግባብተዋልና እመ ብርሃን አሳላፊዎቹን "ኩሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ -የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው:: [ ዮሐ.፪፤፥፭ ] ጌታም በ፮ቱ ጋኖች ውሃ አስሞልቶ በተአምራት ወይን አደረጋቸው::
- እንጀራውን ወጡን በየሥፍራው ሞላው:: ታላቅ ደስታም ሆነ:: የአሳላፊዎቹ አለቃም [ለአባታችን አብርሃም ምሳሌ ነው] ከወይኑ ጥፍጥና የተነሳ አደነቀ:: በዚህም የድንግል ማርያም አማላጅነት: የመድኃኒታችን ከሃሊነት ታወቀ: ተገለጠ::
🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ርዕሰ አበው † 🕊
- የአባቶች አለቃ የተሰኘ ቅዱስ ያዕቆብ ለ፪ቱ ታላላቅ አባቶቹ እርሱ ፫ተኛቸው ነው:: እነርሱን መስሎ: እነርሱንም አህሎ በጐዳናቸው ተጉዟል:: በፈቃደ እግዚአብሔር ብኩርናን ከኤሳው ተቀብሎ ወደ ሶርያ ሲሸሽ ቤቴል [ ፍኖተ ሎዛ ] ላይ ድንጋይ ተንተርሶ በተኛበት ግሩም ራዕይን አይቷል::
- ይህችውም የወርቅ መሰላል የድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::
"አንቲ ውዕቱ ሰዋስው ዘርእየ ያዕቆብ" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም [ ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ ]
- ተነስቶም "ዛቲ ይእቲ ኈኅታ ለሰማይ: ዝየ ይትሐነጽ ቤተ እግዚአብሔር - ይህች የሰማይ ደጅ ናት: ቤተ እግዚአብሔርም ይታነጽባታል" ብሎ ትንቢት ተናግሯል::
- ይህ ቅዱስ አባት ለድንግል ማርያም ቅድመ አያት ከመሆኑ ባሻገር ነቢያትን: ካህናትን: ነገሥታትንና መሣፍንትን ወልዷል:: ከ፪ቱ ሚስቶቹ [ልያና ራሔል] : ከ፪ቱ ደንገጥሮች ፲፪ ልጆችን ወልዷል::
- ከአጐቱ ከላባ ዘንድ ለ፳፩ ዓመታት አገልግሎ: ሃብት ንብረቱን ጠቅልሎ ወደ ርስቱ ከነዓን ሲመለስ ለብቻው ራቅ ብሎ ይጸልይ ገባ:: በዚያም እግዚአብሔር ሲታገለው አደረ::
[ ይኸውም የፍቅርና የምሥጢር ነው ] ለጊዜው ጌታ ያዕቆብን "ልቀቀኝ" ቢለው "ካልባረከኝ አለቅህም" አለው:: ጌታም ስሙን "እሥራኤል" ብሎ ባርኮታል::
- ቅዱስ ያዕቆብ በስተእርጅና ብዙ መከራ አግኝቶታል:: ልጁን ዮሴፍን ወንድሞቹ ሽጠው "አውሬ በላው" ብለውታልና በለቅሶ ዐይኑ ጠፋ::
- በረሃብ ምክንያትም በ፻፴ ዓመቱ ከ፸፭ ያህል ቤተሰቦቹ ጋር ወደ ግብጽ ወረደ:: በዚያም ለ፯ ዓመታት ኑሮ በ፻፴፯ ዓመቱ ዐርፏል:: ልጆቹም ቀብረውታል::
❤2
🕊 † ኃያል ቴዎድሮስ በናድሌዎስ † 🕊
- በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ [በአንጾኪያ] ያበራ:
- ድንግልናውን በንጹሕ የጠበቀ:
- ቅዱሳን መላእክት የሚያነጋግሩት:
- የአንጾኪያ ሠራዊት ሁሉ አለቃ የነበረ:
- በጦርነት ተሸንፎ የማያውቅ:
- አሕዛብ ስሙን ሲሰሙ የሚንቀጠቀጡለት:
- ከአማልክት ወን ነው እያሉ የሚፈሩት
- እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ የሚያመልክ የወቅቱ ወጣት ክርስቲያን ነው::
- ዲዮቅልጢያኖስ በካደ ጊዜም ጌታ ከባልንጀሮቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ጋር መላእክት ወደ ሰማይ አሳርገውታል:: በዚያም መድኃኒታችን ክርስቶስን ፊት ለፊት አይቶ: በእሳት ባሕርም ተጠምቁዋል:: በዚህች ቀንም ከቅዱሳን ለውንድዮስና ኒቆሮስ: እንዲሁ ከ፪.፭ ሚሊየን ሰራዊቱ ጋር ለመከራ ተሰጥቷል:: እርሱንም በ፻፶፫ ችንካር ወግተው ገድለውታል::
አምላከ ቅዱሳን ወይነ ቃና ፍቅሩን ያሳድርብን::
ከድንግል እናቱ ምልጃና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
🕊
[ † ጥር ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
፩. ቃና ዘገሊላ
፪. ቅዱስ ያዕቆብ እሥራኤል
፫. ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ
፬. ቅዱሳን ለውንድዮስ እና ኒቆሮስ
፭. "፪.፭ ሚሊየን" ሰማዕታት [ የቅዱስ ቴዎድሮስ ማሕበር ]
[ † ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
፫. ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ድሜጥሮስ
፭. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
፮. ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ [ ሰማዕት ]
፯. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፰. አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
" አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ:: ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም:: ውሃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር:: አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ :- 'ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል:: ከሰከሩም በኋላ መናኛውን:: አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል' አለው:: " [ዮሐ.፪፥፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
- በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ [በአንጾኪያ] ያበራ:
- ድንግልናውን በንጹሕ የጠበቀ:
- ቅዱሳን መላእክት የሚያነጋግሩት:
- የአንጾኪያ ሠራዊት ሁሉ አለቃ የነበረ:
- በጦርነት ተሸንፎ የማያውቅ:
- አሕዛብ ስሙን ሲሰሙ የሚንቀጠቀጡለት:
- ከአማልክት ወን ነው እያሉ የሚፈሩት
- እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ የሚያመልክ የወቅቱ ወጣት ክርስቲያን ነው::
- ዲዮቅልጢያኖስ በካደ ጊዜም ጌታ ከባልንጀሮቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ጋር መላእክት ወደ ሰማይ አሳርገውታል:: በዚያም መድኃኒታችን ክርስቶስን ፊት ለፊት አይቶ: በእሳት ባሕርም ተጠምቁዋል:: በዚህች ቀንም ከቅዱሳን ለውንድዮስና ኒቆሮስ: እንዲሁ ከ፪.፭ ሚሊየን ሰራዊቱ ጋር ለመከራ ተሰጥቷል:: እርሱንም በ፻፶፫ ችንካር ወግተው ገድለውታል::
አምላከ ቅዱሳን ወይነ ቃና ፍቅሩን ያሳድርብን::
ከድንግል እናቱ ምልጃና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
🕊
[ † ጥር ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
፩. ቃና ዘገሊላ
፪. ቅዱስ ያዕቆብ እሥራኤል
፫. ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ
፬. ቅዱሳን ለውንድዮስ እና ኒቆሮስ
፭. "፪.፭ ሚሊየን" ሰማዕታት [ የቅዱስ ቴዎድሮስ ማሕበር ]
[ † ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
፫. ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ድሜጥሮስ
፭. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
፮. ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ [ ሰማዕት ]
፯. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፰. አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
" አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ:: ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም:: ውሃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር:: አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ :- 'ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል:: ከሰከሩም በኋላ መናኛውን:: አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል' አለው:: " [ዮሐ.፪፥፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊2
#ቃና____ዘገሊላ
#____ዮሐንስ 2
¹ በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
² ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
³ የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።
⁴ ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።
⁵ እናቱም ለአገልጋዮቹ፦ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።
⁶ አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
⁷ ኢየሱስም፦ ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
⁸ አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
⁹ አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ፦
¹⁰ ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው።
¹¹ ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።
#መልካም_በዓል🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#____ዮሐንስ 2
¹ በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
² ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
³ የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።
⁴ ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።
⁵ እናቱም ለአገልጋዮቹ፦ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።
⁶ አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
⁷ ኢየሱስም፦ ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
⁸ አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
⁹ አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ፦
¹⁰ ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው።
¹¹ ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።
#መልካም_በዓል🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6👍2👏1
†
💖 [ ቅ ዱ ስ ሚ ካ ኤ ል ! ] 💖
🕊 💖 🕊
❝ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም። ❞
[ ዳን.፲፥፳፩ ]
🕊
❝ የተጨነቀውን የተጨቆነውን ነፃ የምታወጣው ሚካኤል ሆይ ፦ ሰላም ላንተ ይሁን ፡ ሠራተኛው ሠርቶ እንዲበላ ውሎ እንዲገባ የምትጠብቀው ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፡፡
ችግረኛውን ለመርዳት ከልዑል ዘንድ የምትላክ ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን አዳኝነትህን በማመን የለመነህን በክንፈ ረድኤትህ የምትሠውረው ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፡፡
በኀዘን በትካዜ ላይ ወድቆ የሚፍገመገመውን የሚንፈራገጠውን ፈጥነህ ደርሰህ ደግፈህ የምታጽናናው ሚካኤል ሆይ ፤ አንገትህን ዘንበል ቀለስ አድርገህ በፈጣሪ ፊት ሰግደህ እኛ ባሮቹን በቸርነቱ ይጎበኘን ዘንድ የማናዊት እጁን ዘርግቶ ይባርከን ዘንድ ለምን አማልድ ለዘላለሙ አሜን፡፡ ❞
[ መልክአ ሚካኤል ]
🕊 💖 🕊
💖 [ ቅ ዱ ስ ሚ ካ ኤ ል ! ] 💖
🕊 💖 🕊
❝ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም። ❞
[ ዳን.፲፥፳፩ ]
🕊
❝ የተጨነቀውን የተጨቆነውን ነፃ የምታወጣው ሚካኤል ሆይ ፦ ሰላም ላንተ ይሁን ፡ ሠራተኛው ሠርቶ እንዲበላ ውሎ እንዲገባ የምትጠብቀው ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፡፡
ችግረኛውን ለመርዳት ከልዑል ዘንድ የምትላክ ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን አዳኝነትህን በማመን የለመነህን በክንፈ ረድኤትህ የምትሠውረው ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፡፡
በኀዘን በትካዜ ላይ ወድቆ የሚፍገመገመውን የሚንፈራገጠውን ፈጥነህ ደርሰህ ደግፈህ የምታጽናናው ሚካኤል ሆይ ፤ አንገትህን ዘንበል ቀለስ አድርገህ በፈጣሪ ፊት ሰግደህ እኛ ባሮቹን በቸርነቱ ይጎበኘን ዘንድ የማናዊት እጁን ዘርግቶ ይባርከን ዘንድ ለምን አማልድ ለዘላለሙ አሜን፡፡ ❞
[ መልክአ ሚካኤል ]
🕊 💖 🕊
❤3