#እናንተስ_ስትፆሙ እንደግብዝ አትሁኑ
ፆም ማለት በኦርቶዶክስ ሀይማኖት ትልቅ ቦታ የምንሰጠው ከ3ቱ ቀኖና ውስጥ አንዱነው ሰዎች የሚኖሩት መዝሙረኛው ዳዊት ከፈቃዴ እሰዋልሀለሁ እንዳለ እኛምፈቃዳችንን ሁሉ ለአምላካችን የምናስገዛበት እግዚአብሔር የምንጠላውን ጠልተን የምንወደው አምላክ አይደለም የምንወደውንና የሚያስፈልገንን ትተንና ጠልተን የምናመልከው የምንከተለው አምላክ ነው ምግባችንን ባሎች ሚስቶቻቹን ሚስቶች እንቅልፋችሁን ትታችሁ #ኪዳን እያደረሳቹ የሚያስፈልገንንና የምንወደውን ፍላጎታችንን ሁሉ ለእግዚአብሔር እየሰወዋን የምንፆመው ፆም ነው በእግዚአብሔር ፊትሞገስ የሚያገኘው፡፡ ሊቁ ማር ይህሳቅ "ከመብል ከመጠጥ የሚፆም አንድ በሐሜት የሰውን ስጋ የሚበላ ከሆነ ይህ ፆም #የግብዞች_ፆም ነው እንዳለ ከሐሜትም ተጠበቁ፡፡
#ፆም_የስራ_መጀመሪያ_ናት
#የዝምታን_የምታስተምር_ናት
#ለጸሎት_ምክንያት_ናት
#የወንጌል_ስራ_መጀመሪያ_ናት
#ዝሙትን_መውጊያ_ጦር_ናት
#_ሰናይ__ቀን 🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
ፆም ማለት በኦርቶዶክስ ሀይማኖት ትልቅ ቦታ የምንሰጠው ከ3ቱ ቀኖና ውስጥ አንዱነው ሰዎች የሚኖሩት መዝሙረኛው ዳዊት ከፈቃዴ እሰዋልሀለሁ እንዳለ እኛምፈቃዳችንን ሁሉ ለአምላካችን የምናስገዛበት እግዚአብሔር የምንጠላውን ጠልተን የምንወደው አምላክ አይደለም የምንወደውንና የሚያስፈልገንን ትተንና ጠልተን የምናመልከው የምንከተለው አምላክ ነው ምግባችንን ባሎች ሚስቶቻቹን ሚስቶች እንቅልፋችሁን ትታችሁ #ኪዳን እያደረሳቹ የሚያስፈልገንንና የምንወደውን ፍላጎታችንን ሁሉ ለእግዚአብሔር እየሰወዋን የምንፆመው ፆም ነው በእግዚአብሔር ፊትሞገስ የሚያገኘው፡፡ ሊቁ ማር ይህሳቅ "ከመብል ከመጠጥ የሚፆም አንድ በሐሜት የሰውን ስጋ የሚበላ ከሆነ ይህ ፆም #የግብዞች_ፆም ነው እንዳለ ከሐሜትም ተጠበቁ፡፡
#ፆም_የስራ_መጀመሪያ_ናት
#የዝምታን_የምታስተምር_ናት
#ለጸሎት_ምክንያት_ናት
#የወንጌል_ስራ_መጀመሪያ_ናት
#ዝሙትን_መውጊያ_ጦር_ናት
#_ሰናይ__ቀን 🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6👍2
†
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል አንድ ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ ምላካችንና ንጉሣችን እግዚአብሔር መልካም ፣ እጅግ መልካምና ከሁሉ ይልቅ መልካም ነው፡፡ [ ለአምላክ አገልጋዮች ስለ እግዚአብሔር በመጻፍ መጀመር ማለፊያ [ደግ] ነው]፡፡
በእርሱ ከተፈጠሩ አዋቂ ከሆኑና በነጻ ፈቃድ ከከበሩ ፍጥረታት አንዳንዶቹ ወዳጆቹ ናቸው ፣ ሌሎቹ እውነተኛ አገልጋዮቹ ናቸው ፣ አንዳንዶቹ የማይጠቅሙ ናቸው ፣ [ ሉቃ.፲፯፥፲ ] [ 17 ፥ 10 ] አንዳንዶቹ ፈጽሞ ከእግዚአብሔር የተለዩ ናቸው ፣ ሌሎቹም ደካማ ፍጥረት ሆነው ሳሉ ጠላቶቹ ናቸው፡፡
በትክክል ለመናገር የእግዚአብሔር ወዳጆች የምንላቸው በእግዚአብሔር ዙሪያ ያሉ አዋቂና ረቂቃን የሆኑ ፍጥረታትን ነው፡፡
የእግዚአብሔር እውነተኛ አገልጋዮች የምንላቸው ያለ ድካምና ያለ ማቋረጥ ሆነው ፈቃዱን የሚያደርጉና የሚፈጽሙትን ነው፡፡
ረብ የለሽ አገልጋዮች ማለታችን ፣ ራሳቸውን እንደ ተጠመቁ የሚቆጥሩ ፣ ሆኖም ግን ለእግዚአብሔር የገቡትን ቃል ኪዳን ለመጠበቅ ያልታመኑ ናቸው፡፡ ከእርሱ የራቁና የተለዩ የምንላቸው ኢአማንያን እና መናፍቃን ናቸው፡፡ በመጨረሻም የእግዚአብሔር ጠላቶች የሚባሉት የጌታን ትእዛዝ ለራሳቸው ያልተቀበሉና ከእርሱ የሸሹ ብቻ ሳይሆኑ ነገር ግን ይህን የሚፈጽሙትን አጥብቀው የሚዋጉም ጭምር ናቸው፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል አንድ ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ ምላካችንና ንጉሣችን እግዚአብሔር መልካም ፣ እጅግ መልካምና ከሁሉ ይልቅ መልካም ነው፡፡ [ ለአምላክ አገልጋዮች ስለ እግዚአብሔር በመጻፍ መጀመር ማለፊያ [ደግ] ነው]፡፡
በእርሱ ከተፈጠሩ አዋቂ ከሆኑና በነጻ ፈቃድ ከከበሩ ፍጥረታት አንዳንዶቹ ወዳጆቹ ናቸው ፣ ሌሎቹ እውነተኛ አገልጋዮቹ ናቸው ፣ አንዳንዶቹ የማይጠቅሙ ናቸው ፣ [ ሉቃ.፲፯፥፲ ] [ 17 ፥ 10 ] አንዳንዶቹ ፈጽሞ ከእግዚአብሔር የተለዩ ናቸው ፣ ሌሎቹም ደካማ ፍጥረት ሆነው ሳሉ ጠላቶቹ ናቸው፡፡
በትክክል ለመናገር የእግዚአብሔር ወዳጆች የምንላቸው በእግዚአብሔር ዙሪያ ያሉ አዋቂና ረቂቃን የሆኑ ፍጥረታትን ነው፡፡
የእግዚአብሔር እውነተኛ አገልጋዮች የምንላቸው ያለ ድካምና ያለ ማቋረጥ ሆነው ፈቃዱን የሚያደርጉና የሚፈጽሙትን ነው፡፡
ረብ የለሽ አገልጋዮች ማለታችን ፣ ራሳቸውን እንደ ተጠመቁ የሚቆጥሩ ፣ ሆኖም ግን ለእግዚአብሔር የገቡትን ቃል ኪዳን ለመጠበቅ ያልታመኑ ናቸው፡፡ ከእርሱ የራቁና የተለዩ የምንላቸው ኢአማንያን እና መናፍቃን ናቸው፡፡ በመጨረሻም የእግዚአብሔር ጠላቶች የሚባሉት የጌታን ትእዛዝ ለራሳቸው ያልተቀበሉና ከእርሱ የሸሹ ብቻ ሳይሆኑ ነገር ግን ይህን የሚፈጽሙትን አጥብቀው የሚዋጉም ጭምር ናቸው፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
❤7👍2
†
† 🕊 ዘ ወ ረ ደ 🕊 †
[ የጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት ! ]
💖
[ ክፍል ሁለት ]
❝ እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ምእመናን ሆይ ! ከኹሉም በፊት እነዚህን ነገሮች በስፋት እንነጋገርባቸው ዘንድ ፤ ዳግመኛም አንዳች የሚረባንን ነገር ይዘን ወደ ቤታችን እንመለስ ዘንድ ቃላችንን በታላቅ ትጋትና ጉጉት ሆናችሁ ትቀበሉት ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡
ኹላችንም ወደዚህ ጉባኤ ስንመጣ እንዲሁና ያለ ዓላማ አይደለም፡፡ ወሬ ለማውራት ፣ ምን እንደተባለ እንኳን ሳንሰማ ለማጨብጨብ ፣ ከዚያም ምንም የሚረባ ነገርን ሳንይዝ ወደ ቤታችን ለመመለስ ወደዚህ ጉባኤ አልመጣንም፡፡ እኔ የመጣሁት ለነፍሳችሁ ድኅነት የሚጠቅም አንዳች ነገርን ለመናገር ነው ፤ እናንተም ስትመጡ በእኔ በባሪያው አድሮ እግዚአብሔር የሚናገረውን ነገር አድምጣችሁ ለመጠቀምና አንዳች የሚረባ ነገርን ይዛችሁ ወደ ቤታችሁ ለመመለስ ነው፡፡
ተመልከቱ ! ቤተክርስቲያን ማለት ቤተ ድኅነት ናት፡፡ ወደ እርሷ የሚመጡትም ለችግራቸው ተገቢውን መድኃኒት አግኝተው መሔድ አለባቸው፡፡ ተግባራዊ የኾነ ለውጥ ሳያመጡ ቃለ እግዚአብሔርን መማር ብቻ ምንም ጥቅም እንደሌለው ሲናገርም ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ እንዲህ ብሏል ፦
"በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁት ሕግን የሚያደርጉት እንጂ ሕግን የሚሰሙ አይደሉም፡፡" [ሮሜ.፪፥፲፫]
በቃል መነገሩ ፣ በልብ መታሰቡ ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት መዘገቡ ከፍ ከፍ ይበልና አምላካችን ክርስቶስም ሲያስተምር ፦
"በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡" ብሏል [ማቴ.፯፥፳፩] ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ ! ቃሉን በመስማታችን ብቻ አንዳች የምንጠቀመው ነገር ስለሌለ የሰማነውን የምናደርግ እንጂ የምንሰማ ብቻ አንሁን፡፡ እንዲህ ከሆነም እምነታችን ሕይወት ያለው እምነት ይሆናል፡፡
በመኾኑም ስለ ጾም የሚሰጠውን ስብከት ለማዳመጥ እዝነ ልቦናችሁን ክፈቱ፡፡ ከትሕትና እና ዓይናፋር ሙሽሪት ጋር ለማነጻጸር ያህል ፦ ሙሽሪቱን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች አስቀድመው ቤቱን ያስጌጡታል ፡ ይጠርጉታል፡፡ የቆሸሸ ልብስን የለበሰ ሰው ወደ ሰርጉ አዳራሽ እንዳይገባ ያደርጉታል፡፡ ወደ አዳራሹ መግባት የሚችለው የሰርግ ልብስ የለበሰ ሰው ብቻ ነው፡፡
እናንተም እንዲሁ ልታደርጉ ይገባችኋል ፦ ልቡናችሁን በማንጻት ፣ አብዝቶ ከመብላትና ራስን ካለመግዛት በመራቅ - የምግባር እናት ፣ የማስተዋልና የሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትሆን ጾምን ደጀ ልቡናችሁን በመክፈት ልትቀበሏት ይገባችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደሆነ ታላቅ ሐሴት ታደርጋላችሁ ፤ እርሷም ቁስለ ነፍሳችሁን ትፈውስላችኋለች፡፡
ሌላ ምሳሌ መስዬ ብነግራችሁ ፦ ሐኪሞች በህሙማን ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻና መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ ሕሙማኑ ምግበ ሥጋን ከመውሰድ እንዲቆጠቡ ያደርጓቸዋል፡፡ ሕሙማኑ ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከሉ ግን ሐኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት የተፈለገውን ያህል ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም የነፍስንና የሥጋን ቁስል የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚህ በላይ ልንሆን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡ ድህነትን የምንሻ ከሆነ ልቡናችንን ንጹህና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል ፤ እንዲህ ካልሆነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡ ❞
[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
† 🕊 ዘ ወ ረ ደ 🕊 †
[ የጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት ! ]
💖
[ ክፍል ሁለት ]
❝ እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ምእመናን ሆይ ! ከኹሉም በፊት እነዚህን ነገሮች በስፋት እንነጋገርባቸው ዘንድ ፤ ዳግመኛም አንዳች የሚረባንን ነገር ይዘን ወደ ቤታችን እንመለስ ዘንድ ቃላችንን በታላቅ ትጋትና ጉጉት ሆናችሁ ትቀበሉት ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡
ኹላችንም ወደዚህ ጉባኤ ስንመጣ እንዲሁና ያለ ዓላማ አይደለም፡፡ ወሬ ለማውራት ፣ ምን እንደተባለ እንኳን ሳንሰማ ለማጨብጨብ ፣ ከዚያም ምንም የሚረባ ነገርን ሳንይዝ ወደ ቤታችን ለመመለስ ወደዚህ ጉባኤ አልመጣንም፡፡ እኔ የመጣሁት ለነፍሳችሁ ድኅነት የሚጠቅም አንዳች ነገርን ለመናገር ነው ፤ እናንተም ስትመጡ በእኔ በባሪያው አድሮ እግዚአብሔር የሚናገረውን ነገር አድምጣችሁ ለመጠቀምና አንዳች የሚረባ ነገርን ይዛችሁ ወደ ቤታችሁ ለመመለስ ነው፡፡
ተመልከቱ ! ቤተክርስቲያን ማለት ቤተ ድኅነት ናት፡፡ ወደ እርሷ የሚመጡትም ለችግራቸው ተገቢውን መድኃኒት አግኝተው መሔድ አለባቸው፡፡ ተግባራዊ የኾነ ለውጥ ሳያመጡ ቃለ እግዚአብሔርን መማር ብቻ ምንም ጥቅም እንደሌለው ሲናገርም ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ እንዲህ ብሏል ፦
"በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁት ሕግን የሚያደርጉት እንጂ ሕግን የሚሰሙ አይደሉም፡፡" [ሮሜ.፪፥፲፫]
በቃል መነገሩ ፣ በልብ መታሰቡ ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት መዘገቡ ከፍ ከፍ ይበልና አምላካችን ክርስቶስም ሲያስተምር ፦
"በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡" ብሏል [ማቴ.፯፥፳፩] ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ ! ቃሉን በመስማታችን ብቻ አንዳች የምንጠቀመው ነገር ስለሌለ የሰማነውን የምናደርግ እንጂ የምንሰማ ብቻ አንሁን፡፡ እንዲህ ከሆነም እምነታችን ሕይወት ያለው እምነት ይሆናል፡፡
በመኾኑም ስለ ጾም የሚሰጠውን ስብከት ለማዳመጥ እዝነ ልቦናችሁን ክፈቱ፡፡ ከትሕትና እና ዓይናፋር ሙሽሪት ጋር ለማነጻጸር ያህል ፦ ሙሽሪቱን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች አስቀድመው ቤቱን ያስጌጡታል ፡ ይጠርጉታል፡፡ የቆሸሸ ልብስን የለበሰ ሰው ወደ ሰርጉ አዳራሽ እንዳይገባ ያደርጉታል፡፡ ወደ አዳራሹ መግባት የሚችለው የሰርግ ልብስ የለበሰ ሰው ብቻ ነው፡፡
እናንተም እንዲሁ ልታደርጉ ይገባችኋል ፦ ልቡናችሁን በማንጻት ፣ አብዝቶ ከመብላትና ራስን ካለመግዛት በመራቅ - የምግባር እናት ፣ የማስተዋልና የሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትሆን ጾምን ደጀ ልቡናችሁን በመክፈት ልትቀበሏት ይገባችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደሆነ ታላቅ ሐሴት ታደርጋላችሁ ፤ እርሷም ቁስለ ነፍሳችሁን ትፈውስላችኋለች፡፡
ሌላ ምሳሌ መስዬ ብነግራችሁ ፦ ሐኪሞች በህሙማን ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻና መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ ሕሙማኑ ምግበ ሥጋን ከመውሰድ እንዲቆጠቡ ያደርጓቸዋል፡፡ ሕሙማኑ ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከሉ ግን ሐኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት የተፈለገውን ያህል ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም የነፍስንና የሥጋን ቁስል የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚህ በላይ ልንሆን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡ ድህነትን የምንሻ ከሆነ ልቡናችንን ንጹህና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል ፤ እንዲህ ካልሆነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡ ❞
[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤2
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 ዐ ቢ ይ ጾ ም 🕊
▷ ❝ ዘ ወ ረ ደ ❞
[ [ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ ] ]
[ 🕊 ]
-----------------------------------------------
❝ በመለኮት ሞት ሳይኖርበት በሥጋ ሞትን ገንዘብ አደረገ ፤ በመለኮት መወሰን ሳይኖርበት በሥጋ ተወሰነ ፥ የማይመረመር ሰማያዊ እርሱ ሥጋን ተዋሕዶ በምድር ተገለጠ ፤ የማይታየው ታየ ፥ በኃጢአት ወድቆ የነበረ የቀደመ ሰው አዳምን ዳግመኛ ያከብረው ዘንድ እግዚአብሔር ፍጹም ሥጋን ነፍስንም ተዋሕዶአልና። ❞
[ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ]
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 ዐ ቢ ይ ጾ ም 🕊
▷ ❝ ዘ ወ ረ ደ ❞
[ [ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ ] ]
[ 🕊 ]
-----------------------------------------------
❝ በመለኮት ሞት ሳይኖርበት በሥጋ ሞትን ገንዘብ አደረገ ፤ በመለኮት መወሰን ሳይኖርበት በሥጋ ተወሰነ ፥ የማይመረመር ሰማያዊ እርሱ ሥጋን ተዋሕዶ በምድር ተገለጠ ፤ የማይታየው ታየ ፥ በኃጢአት ወድቆ የነበረ የቀደመ ሰው አዳምን ዳግመኛ ያከብረው ዘንድ እግዚአብሔር ፍጹም ሥጋን ነፍስንም ተዋሕዶአልና። ❞
[ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ]
🕊 💖 🕊
❤1👍1
🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። †
🕊 † ታላቁ አባ መርትያኖስ † 🕊
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ዐሥራ ዘጠኝ በዚች ዕለት የተጋዳይ መነኰስ የአባ መርትያኖስ ሥጋው ከአቴና አገር ወደ አንጾኪያ የፈለሰበት ሆነ። እርሱም ሽንግላ በኃጢያት ልትጥለው በወደደች ጊዜ ከአመንዝራ ሴት ከተፈተነ በኋላ እርሱ ግን መንኵሳ በገድል እስከ ተጸመደች ድረስ ስቦ ወደ ንስሓ መልሷታል።
ከዚህም በኋላ መኖሪያውን ትቶላት ከሀገር ወደ ሀገር የሚዞር ሆነ ከአቴና አገርም ደርሶ በዚያ ጥቂት ቀን ኖረ ጥቂትም ታመመና በሰላም አገፈ ዜናው በግንቦት በሃያ አንድ ቀን እንደተጻፈ።
የከበረ ቴዎድሮስም ለአንጾኪያ ሀገር በከሀዲው የፋርስ ንጉሥ ዘመን ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ ይህ አባት የካህናት አለቆችንና ምእመናንን ልኮ ሥጋውን ከአቴና አፍልሰው ወደ አንጾኪያ ከተማ አመጡት በምስጋናም እየዘመሩ አክብረው ተቀበሉት ሊቀ ጳጳሳቱም ተሳለመው በሣጥንም አድርጐ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖረው። በዚችም ዕለት በዓልን አደረጉለት።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
[ † የካቲት ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ታላቁ አባ መርትያኖስ [በዝሙት ላለመሰናከል እግራቸውን በእሳት ያቃጠሉ አባት]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
፫. አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
፬. አቡነ ስነ ኢየሱስ
፭. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም
" . . . በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ:: በድንጋይ ተወግረው ሞቱ:: ተፈተኑ:: በመጋዝ ተሰነጠቁ:: በሰይፍ ተገድለው ሞቱ:: ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ::" [ዕብ.፲፩፥፴፮]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። †
🕊 † ታላቁ አባ መርትያኖስ † 🕊
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ዐሥራ ዘጠኝ በዚች ዕለት የተጋዳይ መነኰስ የአባ መርትያኖስ ሥጋው ከአቴና አገር ወደ አንጾኪያ የፈለሰበት ሆነ። እርሱም ሽንግላ በኃጢያት ልትጥለው በወደደች ጊዜ ከአመንዝራ ሴት ከተፈተነ በኋላ እርሱ ግን መንኵሳ በገድል እስከ ተጸመደች ድረስ ስቦ ወደ ንስሓ መልሷታል።
ከዚህም በኋላ መኖሪያውን ትቶላት ከሀገር ወደ ሀገር የሚዞር ሆነ ከአቴና አገርም ደርሶ በዚያ ጥቂት ቀን ኖረ ጥቂትም ታመመና በሰላም አገፈ ዜናው በግንቦት በሃያ አንድ ቀን እንደተጻፈ።
የከበረ ቴዎድሮስም ለአንጾኪያ ሀገር በከሀዲው የፋርስ ንጉሥ ዘመን ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ ይህ አባት የካህናት አለቆችንና ምእመናንን ልኮ ሥጋውን ከአቴና አፍልሰው ወደ አንጾኪያ ከተማ አመጡት በምስጋናም እየዘመሩ አክብረው ተቀበሉት ሊቀ ጳጳሳቱም ተሳለመው በሣጥንም አድርጐ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖረው። በዚችም ዕለት በዓልን አደረጉለት።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
[ † የካቲት ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ታላቁ አባ መርትያኖስ [በዝሙት ላለመሰናከል እግራቸውን በእሳት ያቃጠሉ አባት]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
፫. አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
፬. አቡነ ስነ ኢየሱስ
፭. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም
" . . . በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ:: በድንጋይ ተወግረው ሞቱ:: ተፈተኑ:: በመጋዝ ተሰነጠቁ:: በሰይፍ ተገድለው ሞቱ:: ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ::" [ዕብ.፲፩፥፴፮]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤1👍1
#_እየጾሙ__አለመጾም ??
#ተወዳጆች_ሆይ! እየጾሙ የጾምን ፍሬ ፃማ የማያገኙበት ሁኔታ እንዳለ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ፡፡ ይህስ እንደ ምን ነው ያላችሁኝ እንደሆነም፦
#ከምግበ_ሥጋ ተከልክለን ከምግበ ኃጢአት ያልተከለከልን እንደ ሆነ፣
#ከጥሉላት_ርቀን ነዳያንን ያልጎበኘን እንደ ሆነ፣
#ወይን_ከመጠጣት ታቅበን በክፉ መሻት ከመስከር ያልራቅን እንደ ሆነ፣
#ጀምበር_እስክትጠልቅ ድረስ ከእህል ከውኃ ርቀን በዓይናችን መልካም ያልሆኑ መመልከት
#ትዕይንቶችን ከማየት ያልጦምን እንደሆነ ነው ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እመልስላችኋለሁ፡፡ ስለዚህ #እየጾሙ እንዲህ #አለመጾም እንዳለ ዕወቁ፤ ተረዱም፡፡
#አምላከ_ቅዱሳን_እየጾሙ_ካለመጾም_ይሰውረን!
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ተወዳጆች_ሆይ! እየጾሙ የጾምን ፍሬ ፃማ የማያገኙበት ሁኔታ እንዳለ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ፡፡ ይህስ እንደ ምን ነው ያላችሁኝ እንደሆነም፦
#ከምግበ_ሥጋ ተከልክለን ከምግበ ኃጢአት ያልተከለከልን እንደ ሆነ፣
#ከጥሉላት_ርቀን ነዳያንን ያልጎበኘን እንደ ሆነ፣
#ወይን_ከመጠጣት ታቅበን በክፉ መሻት ከመስከር ያልራቅን እንደ ሆነ፣
#ጀምበር_እስክትጠልቅ ድረስ ከእህል ከውኃ ርቀን በዓይናችን መልካም ያልሆኑ መመልከት
#ትዕይንቶችን ከማየት ያልጦምን እንደሆነ ነው ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እመልስላችኋለሁ፡፡ ስለዚህ #እየጾሙ እንዲህ #አለመጾም እንዳለ ዕወቁ፤ ተረዱም፡፡
#አምላከ_ቅዱሳን_እየጾሙ_ካለመጾም_ይሰውረን!
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤14👍7🔥2