#___ወዳጆቼ
የንጉሥ ሥልጣን #በሥጋ ላይ ነው፤ የካህን ሥልጣን ግን #በነፍስ ላይ ነው፡፡
ንጉሥ ይቅር ቢል #የገንዘብን ዕዳ ነው፤ ካህን ይቅር ሲል ግን #የበደል_የኃጢአት ዕዳን ነው፡፡
ንጉሥ #ያዝዛል፤ ካህን ግን #ያስተምራል ይዘክራል፡፡
ንጉሥ #ያስገድዳል፤ ካህን ግን #ነጻ ፈቃድን ያያል፡፡
ንጉሥ ቁሳዊ #የጦር ዕቃ መሣሪያ አለው፤ ካህን ግን ረቂቅ (#መንፈሳዊ) የጦር ዕቃ መሣሪያ አለው፡፡
ንጉሥ የጦር ዕቃ መሣሪያውን ቢሰብቅ አንገዛም ብለው ባመፁት (እንዲሁም #ከወራሪዎች ሥጋውያን ደማውያን) ላይ ነው፤ ካህን ግን ውጊያው ከጨለማ አበጋዞች #ከአጋንንት ጋር ነው፡፡
ስለዚህ ሥልጣነ ክህነት ከሥልጣነ #መንግሥት ይበልጣል፡፡ እንዲህም በመኾኑ ንጉሥ #አንገቱን ለካህናት እጅ ያጎነብሳል፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ድርሳን ፬ በተረጎመበት ድርሳኑ)
#ሰናይ__ቀን🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
የንጉሥ ሥልጣን #በሥጋ ላይ ነው፤ የካህን ሥልጣን ግን #በነፍስ ላይ ነው፡፡
ንጉሥ ይቅር ቢል #የገንዘብን ዕዳ ነው፤ ካህን ይቅር ሲል ግን #የበደል_የኃጢአት ዕዳን ነው፡፡
ንጉሥ #ያዝዛል፤ ካህን ግን #ያስተምራል ይዘክራል፡፡
ንጉሥ #ያስገድዳል፤ ካህን ግን #ነጻ ፈቃድን ያያል፡፡
ንጉሥ ቁሳዊ #የጦር ዕቃ መሣሪያ አለው፤ ካህን ግን ረቂቅ (#መንፈሳዊ) የጦር ዕቃ መሣሪያ አለው፡፡
ንጉሥ የጦር ዕቃ መሣሪያውን ቢሰብቅ አንገዛም ብለው ባመፁት (እንዲሁም #ከወራሪዎች ሥጋውያን ደማውያን) ላይ ነው፤ ካህን ግን ውጊያው ከጨለማ አበጋዞች #ከአጋንንት ጋር ነው፡፡
ስለዚህ ሥልጣነ ክህነት ከሥልጣነ #መንግሥት ይበልጣል፡፡ እንዲህም በመኾኑ ንጉሥ #አንገቱን ለካህናት እጅ ያጎነብሳል፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ድርሳን ፬ በተረጎመበት ድርሳኑ)
#ሰናይ__ቀን🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤11
🕊 † 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ እኛ በማሕፀን መፀነስን ወደደ ! ]
🕊 💖 🕊
❝ በሥጋ ከመጀመሪያው ሰው ከአዳም : ከአብርሃም ከዳዊት ከተገኘ ባሕርይዋም ኃጢአት የሌለበት ፤ በነፍስ በሥጋ ፍጹም የሚሆን አካልን ሊዋሐደው ፈጠረ ፤ ከማርያም የነሣውን ሥጋ ከኃጢአት ፤ ከዘር የራቀ አደረገው ከማሕፀን ጀምሮ በማይመረመር ግብር በአንድ ባሕርየ መለኮት ከእርሱ ጋር አንድ አደረገው። [ዕብ.፪፥፲፮ ]
በማይመረመር ምሥጢር እንደ እኛ በማሕፀን መፀነስን ወደደ። እርሱ ሰው እንደ መሆኑ በማሕፀን ሳለ በባሕርየ መለኮቱ በሰማይ በምድር ከምድርም በታች ምሉእ ነው። በማይመረመር ፥ በማይነገር ጌትነቱም በአብ ዕሪና ይኖር ነበር።
የሕይወት እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ በላይ በታች ያሉ ፍጡራንም ሁሉ በመሀል እጁ ናቸው። አቸናፊ ፤ ፈጣሪ እርሱ እንደ ከሀሊነቱ ሁሉን ያዝዛቸዋል። [ ሉቃ.፩፥፵፪ ና ፶፩ ። ዕብ.፩፥፪፬ ]
ወልድ በድንግል ማሕፀን ሳለ ፤ በሰማይም በምድርም ከአባቱ ጋር በአንድ ባሕርየ መለኮት ህልው ነውና ከኃጢአት በቀር በድንግል ማሕፀን ሥጋ ሆኖ ከተፈጠረ ከፍጹም ትስብእት ጋርም በማይመረመር ባንድ ባሕርየ መለኮት መቸም መች አንድ ነውና። [ ዮሐ.፲፬፥፲ ]
እርሷም በሥጋ ወለደችው ዳግመኛም በሥጋ ጨርቅ ያለበሱት እርሱን ነው። ከሰው የተወለደ ትንሽ ልጅ እንደ መሆኑ በበረት ጣሉት። ዳግመኛ ከልዕልናው ከጌትነቱ የማይለወጥ አምላክ ሲሆን ከድንግል ጡት ወተትን የጠባ እርሱ ነው። [ ሚል.፫፥፮ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ እኛ በማሕፀን መፀነስን ወደደ ! ]
🕊 💖 🕊
❝ በሥጋ ከመጀመሪያው ሰው ከአዳም : ከአብርሃም ከዳዊት ከተገኘ ባሕርይዋም ኃጢአት የሌለበት ፤ በነፍስ በሥጋ ፍጹም የሚሆን አካልን ሊዋሐደው ፈጠረ ፤ ከማርያም የነሣውን ሥጋ ከኃጢአት ፤ ከዘር የራቀ አደረገው ከማሕፀን ጀምሮ በማይመረመር ግብር በአንድ ባሕርየ መለኮት ከእርሱ ጋር አንድ አደረገው። [ዕብ.፪፥፲፮ ]
በማይመረመር ምሥጢር እንደ እኛ በማሕፀን መፀነስን ወደደ። እርሱ ሰው እንደ መሆኑ በማሕፀን ሳለ በባሕርየ መለኮቱ በሰማይ በምድር ከምድርም በታች ምሉእ ነው። በማይመረመር ፥ በማይነገር ጌትነቱም በአብ ዕሪና ይኖር ነበር።
የሕይወት እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ በላይ በታች ያሉ ፍጡራንም ሁሉ በመሀል እጁ ናቸው። አቸናፊ ፤ ፈጣሪ እርሱ እንደ ከሀሊነቱ ሁሉን ያዝዛቸዋል። [ ሉቃ.፩፥፵፪ ና ፶፩ ። ዕብ.፩፥፪፬ ]
ወልድ በድንግል ማሕፀን ሳለ ፤ በሰማይም በምድርም ከአባቱ ጋር በአንድ ባሕርየ መለኮት ህልው ነውና ከኃጢአት በቀር በድንግል ማሕፀን ሥጋ ሆኖ ከተፈጠረ ከፍጹም ትስብእት ጋርም በማይመረመር ባንድ ባሕርየ መለኮት መቸም መች አንድ ነውና። [ ዮሐ.፲፬፥፲ ]
እርሷም በሥጋ ወለደችው ዳግመኛም በሥጋ ጨርቅ ያለበሱት እርሱን ነው። ከሰው የተወለደ ትንሽ ልጅ እንደ መሆኑ በበረት ጣሉት። ዳግመኛ ከልዕልናው ከጌትነቱ የማይለወጥ አምላክ ሲሆን ከድንግል ጡት ወተትን የጠባ እርሱ ነው። [ ሚል.፫፥፮ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
❤5
†
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
[ ክፍል ሠላሳ አምስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ አንድ ሰው ኑዛዜ ለማድረግ ከወሰነ ፣ በዚህ ምክንያት ነፍስ ኃጢአትን ከመፈጸም በልጓም እንደ ተያዘ ትያዛለች፡፡ በድፍረት እያደረግነው ሳንናዘዝ የምንተወው ከሆነ በጨለማ እንዳለ እንሆናለንና፡፡
የበላዩ በማይኖርበት ጊዜ ፊቱን በዓይነ ሕሊና መሳልና ዘወትር በፊታችን እንደ ቆመ በማሰብ ፣ መሰባሰብንም ሁሉ ፣ ወይም ንግግር ወይም ምግብ ፣ ወይም መኝታ ፣ ወይም እርሱ ይጠላዋል ብለን የምናስበውን ማንኛውንም ሌላ ነገር ሁሉ ካስወገድን ፣ እንኪያስ በእውነት እውነተኛ መታዘዝን ተምረናል፡፡ ዲቃላ ልጆች የመምህራቸውን መቅረት [ አለመኖር ] እንደ ደስታ ይቆጥሩታል ፣ በሕግ የተወለዱት ግን እንደ ጉዳት ይቆጥሩታል፡፡
አንድ ጊዜ እጅግ ልምዱ ካላቸው አባቶች አንዱን ትሕትና እንዴት በመታዘዝ እንደሚገኝ ይነግረኝ ዘንድ አጥብቄ ጠየቅሁት፡፡ እርሱም ፦ ለይቶ ለይቶ የማወቅ ጸጋ ያለው ታዛዥ ሰው ፣ ሙት የሚያስነሣና የአንብዕ ጸጋ የተሰጠው ፣ እንዲሁም ከፀብእ [ ከፀብአ አጋንንት ] ነጻ ቢሆን እንኳ ፣ ያን ያደረገው የመንፈሳዊ አባቱ ጸሎት እንደ ሆነ አድርጎ የሚያስብ ነው ፣ ከከንቱና ባዕድ አሳብም የተለየ ሆኖ ይኖራል፡፡ እርሱም ራሱ እንዳመነው ስለ ተደረገው ነገር በአባቱ እርዳታ እንጂ በራሱ ጥረት እንደ ሆነ አድርጎ እንዴት ራሱን ሊያስታብይ ይችላል? አለኝ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
[ ክፍል ሠላሳ አምስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ አንድ ሰው ኑዛዜ ለማድረግ ከወሰነ ፣ በዚህ ምክንያት ነፍስ ኃጢአትን ከመፈጸም በልጓም እንደ ተያዘ ትያዛለች፡፡ በድፍረት እያደረግነው ሳንናዘዝ የምንተወው ከሆነ በጨለማ እንዳለ እንሆናለንና፡፡
የበላዩ በማይኖርበት ጊዜ ፊቱን በዓይነ ሕሊና መሳልና ዘወትር በፊታችን እንደ ቆመ በማሰብ ፣ መሰባሰብንም ሁሉ ፣ ወይም ንግግር ወይም ምግብ ፣ ወይም መኝታ ፣ ወይም እርሱ ይጠላዋል ብለን የምናስበውን ማንኛውንም ሌላ ነገር ሁሉ ካስወገድን ፣ እንኪያስ በእውነት እውነተኛ መታዘዝን ተምረናል፡፡ ዲቃላ ልጆች የመምህራቸውን መቅረት [ አለመኖር ] እንደ ደስታ ይቆጥሩታል ፣ በሕግ የተወለዱት ግን እንደ ጉዳት ይቆጥሩታል፡፡
አንድ ጊዜ እጅግ ልምዱ ካላቸው አባቶች አንዱን ትሕትና እንዴት በመታዘዝ እንደሚገኝ ይነግረኝ ዘንድ አጥብቄ ጠየቅሁት፡፡ እርሱም ፦ ለይቶ ለይቶ የማወቅ ጸጋ ያለው ታዛዥ ሰው ፣ ሙት የሚያስነሣና የአንብዕ ጸጋ የተሰጠው ፣ እንዲሁም ከፀብእ [ ከፀብአ አጋንንት ] ነጻ ቢሆን እንኳ ፣ ያን ያደረገው የመንፈሳዊ አባቱ ጸሎት እንደ ሆነ አድርጎ የሚያስብ ነው ፣ ከከንቱና ባዕድ አሳብም የተለየ ሆኖ ይኖራል፡፡ እርሱም ራሱ እንዳመነው ስለ ተደረገው ነገር በአባቱ እርዳታ እንጂ በራሱ ጥረት እንደ ሆነ አድርጎ እንዴት ራሱን ሊያስታብይ ይችላል? አለኝ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
❤4
🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
† እንኳን አደረሳችሁ †
[ † ግንቦት ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
🕊 † አርዋ ቅድስት † 🕊
እናታችን ቅድስት አርዋ በስነ ገድላቸው ከደመቁ የቀደመው ዘመን ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት:: በሕጻንነቷ የሚገባውን የክርስትና ትምሕርት ተምራለችና ምርጫዋ ሰማያዊው ሙሽርነት ሆነ::
ለሰዎች ሕይወት እንቅፋት እየሆኑ ከሚያስቸግሩ ነገሮች አንዱ መልክ ነው:: እግዚአብሔር የፈጠረውን ደም ግባት [ቁንጅና] በማይገባ ተጠቅመው የአጋንንት ራት የሆኑ: ሌሎችንም አብረው ያጠፉ ሰዎች ቁጥራቸው እጅግ ብዙ ነው:: አርዋ ግን ይሕ ቀረሽ የማይሏት ውብ ብትሆንም እርሷ ለዚሕ ቦታ አልነበራትም:: በለጋ እድሜዋ በክርስቶስና በድንግል እናቱ ፍቅር ተጠመደች እንጂ::
ቅድስት አርዋ ሁሉ ያላት ስትሆን ስለ መንግስተ ሰማያት ሁሉን ንቃለች:: በተለይ ደግሞ ሥጋዊ ፍትወትን ትገድል ዘንድ ያሳየችው ተጋድሎ በዜና ቤተ ክርስቲያን የተደነቀ በመሆኑ "መዋኢተ ፍትወት" [የሥጋን ፍላጎት ድል የነሳች] አስብሏታል::
የሚገርመው የቅድስቷ እናታችን ሕይወት በጾምና በጸሎት ብቻ የተወሰነ አልነበረም:: በሰው ሁሉ ፊት ብርሃን መሆን የቻለ የደግነት: ርሕራሔ: የፍቅርና የምጽዋት ሕይወትም ነበራት እንጂ::
አንድ ቀን በተንኮለኞች የሐሰት ምስክር ያለ ጥፋቷ ለፍርድ ቀረበች:: ፍርደ ገምድል ዳኛ ሞት ፈረደባት:: በአደባባይ በጭካኔ ቅድስት እናታችንን ገደሏት:: እግዚአብሔር ግን ድንቅ ነውና ከሞት አስነስቷት ገዳዮቿ እንዲጸጸቱ አድርጓል:: ከዚሕ በኋላም በንጹሕ አኗኗሯ ቀጠለች::
አንድ ቀን ግን ከባድ ፈተና መጣባት:: አንድ በደም ግባቷ ተማርኮ ሲፈልጋት የኖረ ጐልማሳ አሳቻ ሰዓትና ቦታ ላይ አገኛት:: የሥጋ ፈቃዱን ይፈጽም ዘንድ አስገደዳት::
እርሱን መታገሉ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት እርሱ ልብሱን እያወለቀ እርሷ ከወደቀችበት ሆና ወደ ፈጣሪዋ ለመነች :- "ጌታየ ሆይ! የእኔንም ድንግልና ጠብቅ: እርሱንም ኃጢአት ይሠራ ዘንድ አትተወው:: ስለዚሕም ነፍሴን ተቀበላት" ብላ አለቀሰች::
እመቤታችን እንደ ዐይን ጥቅሻ ወርዳ ነፍሷን አሳረገች:: ጐልማሳው ወደ ጣላት ቅድስት ዘወር ቢል ሙታ አገኛት:: እርሱም ተጸጸተ:: ወገኖቿ በዝማሬ እናታችን ቅድስት አርዋን ቀብረዋታል::
🕊 † ቅዱስ ቆሮስ ሐዋርያ † 🕊
ዳግመኛ በዚህች ቀን ሐዋርያው ቅዱስ ቆሮስ አርፏል::
ቅዱስ ቆሮስ ከ72ቱ [ ፸፪ቱ ] አርድእት አንዱ ሲሆን ከጌታችን እግር የተማረ: ለስብከተ ወንጌል ብዙ ሃገራትን የዞረ ታላቅ ሐዋርያ ነው:: ባስተማረባቸው ቦታዎች ብዙ ሕማማትን ተቀብሏል::
ብዙ አሕዛብንም ወደ አሚነ ክርስቶስ መልሷል:: በተለይ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር ለዓመታት አገልግሏል:: ቅዱስ ዻውሎስ ሲታሠር መልዕክቶችንም ይወስድለት ነበር::
† ወርኀ ግንቦትን በሰላም ላስፈጸመን እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን:: አምላካችን ከወዳጆቹ በረከትን ይክፈለን:: †
🕊
[ † ግንቦት ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት አርዋ እናታችን
፪. ቅዱስ ቆሮስ ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ዲማዲስ ሰማዕት
፬. አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
፪፡ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
፫፡ አባ ሣሉሲ ክቡር
፬፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት
፭፡ ቅድስት ሶፍያና ሰማዕታት ልጆቿ
" መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ:: አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ:: ውበት ሐሰት ነው:: ደም ግባትም ከንቱ ነው:: እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች:: ከእጇ ፍሬ ስጧት:: ሥረዎቿም በሸንጐ ያመስግኗት:: " [ምሳሌ.፴፩፥፳፱] (31:29)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
† እንኳን አደረሳችሁ †
[ † ግንቦት ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
🕊 † አርዋ ቅድስት † 🕊
እናታችን ቅድስት አርዋ በስነ ገድላቸው ከደመቁ የቀደመው ዘመን ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት:: በሕጻንነቷ የሚገባውን የክርስትና ትምሕርት ተምራለችና ምርጫዋ ሰማያዊው ሙሽርነት ሆነ::
ለሰዎች ሕይወት እንቅፋት እየሆኑ ከሚያስቸግሩ ነገሮች አንዱ መልክ ነው:: እግዚአብሔር የፈጠረውን ደም ግባት [ቁንጅና] በማይገባ ተጠቅመው የአጋንንት ራት የሆኑ: ሌሎችንም አብረው ያጠፉ ሰዎች ቁጥራቸው እጅግ ብዙ ነው:: አርዋ ግን ይሕ ቀረሽ የማይሏት ውብ ብትሆንም እርሷ ለዚሕ ቦታ አልነበራትም:: በለጋ እድሜዋ በክርስቶስና በድንግል እናቱ ፍቅር ተጠመደች እንጂ::
ቅድስት አርዋ ሁሉ ያላት ስትሆን ስለ መንግስተ ሰማያት ሁሉን ንቃለች:: በተለይ ደግሞ ሥጋዊ ፍትወትን ትገድል ዘንድ ያሳየችው ተጋድሎ በዜና ቤተ ክርስቲያን የተደነቀ በመሆኑ "መዋኢተ ፍትወት" [የሥጋን ፍላጎት ድል የነሳች] አስብሏታል::
የሚገርመው የቅድስቷ እናታችን ሕይወት በጾምና በጸሎት ብቻ የተወሰነ አልነበረም:: በሰው ሁሉ ፊት ብርሃን መሆን የቻለ የደግነት: ርሕራሔ: የፍቅርና የምጽዋት ሕይወትም ነበራት እንጂ::
አንድ ቀን በተንኮለኞች የሐሰት ምስክር ያለ ጥፋቷ ለፍርድ ቀረበች:: ፍርደ ገምድል ዳኛ ሞት ፈረደባት:: በአደባባይ በጭካኔ ቅድስት እናታችንን ገደሏት:: እግዚአብሔር ግን ድንቅ ነውና ከሞት አስነስቷት ገዳዮቿ እንዲጸጸቱ አድርጓል:: ከዚሕ በኋላም በንጹሕ አኗኗሯ ቀጠለች::
አንድ ቀን ግን ከባድ ፈተና መጣባት:: አንድ በደም ግባቷ ተማርኮ ሲፈልጋት የኖረ ጐልማሳ አሳቻ ሰዓትና ቦታ ላይ አገኛት:: የሥጋ ፈቃዱን ይፈጽም ዘንድ አስገደዳት::
እርሱን መታገሉ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት እርሱ ልብሱን እያወለቀ እርሷ ከወደቀችበት ሆና ወደ ፈጣሪዋ ለመነች :- "ጌታየ ሆይ! የእኔንም ድንግልና ጠብቅ: እርሱንም ኃጢአት ይሠራ ዘንድ አትተወው:: ስለዚሕም ነፍሴን ተቀበላት" ብላ አለቀሰች::
እመቤታችን እንደ ዐይን ጥቅሻ ወርዳ ነፍሷን አሳረገች:: ጐልማሳው ወደ ጣላት ቅድስት ዘወር ቢል ሙታ አገኛት:: እርሱም ተጸጸተ:: ወገኖቿ በዝማሬ እናታችን ቅድስት አርዋን ቀብረዋታል::
🕊 † ቅዱስ ቆሮስ ሐዋርያ † 🕊
ዳግመኛ በዚህች ቀን ሐዋርያው ቅዱስ ቆሮስ አርፏል::
ቅዱስ ቆሮስ ከ72ቱ [ ፸፪ቱ ] አርድእት አንዱ ሲሆን ከጌታችን እግር የተማረ: ለስብከተ ወንጌል ብዙ ሃገራትን የዞረ ታላቅ ሐዋርያ ነው:: ባስተማረባቸው ቦታዎች ብዙ ሕማማትን ተቀብሏል::
ብዙ አሕዛብንም ወደ አሚነ ክርስቶስ መልሷል:: በተለይ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር ለዓመታት አገልግሏል:: ቅዱስ ዻውሎስ ሲታሠር መልዕክቶችንም ይወስድለት ነበር::
† ወርኀ ግንቦትን በሰላም ላስፈጸመን እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን:: አምላካችን ከወዳጆቹ በረከትን ይክፈለን:: †
🕊
[ † ግንቦት ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት አርዋ እናታችን
፪. ቅዱስ ቆሮስ ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ዲማዲስ ሰማዕት
፬. አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
፪፡ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
፫፡ አባ ሣሉሲ ክቡር
፬፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት
፭፡ ቅድስት ሶፍያና ሰማዕታት ልጆቿ
" መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ:: አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ:: ውበት ሐሰት ነው:: ደም ግባትም ከንቱ ነው:: እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች:: ከእጇ ፍሬ ስጧት:: ሥረዎቿም በሸንጐ ያመስግኗት:: " [ምሳሌ.፴፩፥፳፱] (31:29)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤3
#ወዳጄ!!
#ጠላቶች_ስንሆን፣በደለኛ ስንሆን በልጁ ይቅርታ ያደረገልን ማን እንደ #እግዚአብሔር አለ።
ሰው ሲበድል ተበዳዩን ካሳ ሰጥቶ ይቅርታ ይጠይቃል፣ እግዚአብሔር ግን በደለኞች ስንሆን ፣እርሱ እራሱ ካሳውን ከፍሎ #ይቅርታ_አደረገልን🙏 እንዴት ያለ #ፍቅር ነው
"፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ #እግዚአብሔር_አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። "
(የዮሐንስ ወንጌል 3: 16)
#_ሰናይ__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ጠላቶች_ስንሆን፣በደለኛ ስንሆን በልጁ ይቅርታ ያደረገልን ማን እንደ #እግዚአብሔር አለ።
ሰው ሲበድል ተበዳዩን ካሳ ሰጥቶ ይቅርታ ይጠይቃል፣ እግዚአብሔር ግን በደለኞች ስንሆን ፣እርሱ እራሱ ካሳውን ከፍሎ #ይቅርታ_አደረገልን🙏 እንዴት ያለ #ፍቅር ነው
"፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ #እግዚአብሔር_አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። "
(የዮሐንስ ወንጌል 3: 16)
#_ሰናይ__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤9
†
[ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ]
🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒
[ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊
[ " ቅ ዱ ሳ ት መ ጻ ሕ ፍ ት " ]
[ ክፍል አምስት ]
❝ ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም ፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና ፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። ❞ [ ፪ጴጥ.፩፥፳ ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
💖 ድንቅ ትምህርት 💖
[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]
❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
👇
[ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ]
🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒
[ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊
[ " ቅ ዱ ሳ ት መ ጻ ሕ ፍ ት " ]
[ ክፍል አምስት ]
❝ ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም ፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና ፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። ❞ [ ፪ጴጥ.፩፥፳ ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
💖 ድንቅ ትምህርት 💖
[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]
❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
👇
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 [ በዓለ ዸራቅሊጦስ ] 🕊
† እንኩዋን ለበዓለ ዸራቅሊጦስ [ መንፈስ ቅዱስ ] በሰላም አደረሳችሁ †
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው ፦ " ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ፣ ለዘለዓለም ከእናንተ ጋር የሚኖር የእውነት መንፈስ እሰጣችኋለሁ። [ ሐዋርያትም ] ' አንተ ካረግህ እንዳንተ ያለ ከዴት እናገኛለን!? ፣ ስለ ትንሣኤህስ [ ብንሰብክ ] ማን ያምነናል !? ' አሉት። ኢየሱስም " እናንተ በእኔ ናችሁ እኔም በአባቴ ነኝ ፣ መንፈሴን ተቀበሉ እና ትንሣኤየን ስበኩ " አላቸው። ❞ [ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊
❝ ሃይማኖት ከአብ ዘንድ የተገኘች ናት ፣ ወደ ወልድ የምታደርስ ናት ፣ በመንፈስ ቅዱስም የምትፈጸም [ ፍጽምት የምትሆን ] ናት። ❞ [ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊 የቤተክርስቲያን የልደት ቀን 🕊
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 [ በዓለ ዸራቅሊጦስ ] 🕊
† እንኩዋን ለበዓለ ዸራቅሊጦስ [ መንፈስ ቅዱስ ] በሰላም አደረሳችሁ †
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው ፦ " ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ፣ ለዘለዓለም ከእናንተ ጋር የሚኖር የእውነት መንፈስ እሰጣችኋለሁ። [ ሐዋርያትም ] ' አንተ ካረግህ እንዳንተ ያለ ከዴት እናገኛለን!? ፣ ስለ ትንሣኤህስ [ ብንሰብክ ] ማን ያምነናል !? ' አሉት። ኢየሱስም " እናንተ በእኔ ናችሁ እኔም በአባቴ ነኝ ፣ መንፈሴን ተቀበሉ እና ትንሣኤየን ስበኩ " አላቸው። ❞ [ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊
❝ ሃይማኖት ከአብ ዘንድ የተገኘች ናት ፣ ወደ ወልድ የምታደርስ ናት ፣ በመንፈስ ቅዱስም የምትፈጸም [ ፍጽምት የምትሆን ] ናት። ❞ [ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊 የቤተክርስቲያን የልደት ቀን 🕊
🕊 💖 🕊