Telegram Web
🙏4
✦✦✦መዝሙረ ዳዊት ፷፪፡፩-፯✦✦✦
✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥

✥አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ።

✥ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ።
✥ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

✥እንዲህ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፥ በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ።

✥ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች፥ ከንፈሮቼም ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ።

✥በመኝታዬም አስብሃለሁ፥ በማለዳም እናገርልሃለሁ፤
✥ረዳቴ ሆነኸኛልና፥ በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና።


#መልካም_ዕለተ_ሰንበት 🙏

የተለያዩ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
🙏54👏1
                       †                       
                    
†   🕊   ክብርት ሰንበት    🕊    †

💖

❝ የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ፥ ለሚያደርጓትም ሁሉ ደኅና ማስተዋል አላቸው ፤ ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል። ❞ [መዝ.፩፻፲፩፥፲]

[ The fear of the LORD [is] the beginning of wisdom: a good understanding have all they that do [his commandments]: his praise endureth for ever. ] [Psalms 111:10]

†                       †                       †       

❝ አቤቱ ፥ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል ? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል ?

በቅንነት የሚሄድ ፥ ጽድቅንም የሚያደርግ ፥ በልቡም እውነትን የሚናገር። በአንደበቱ የማይሸነግል ፥ በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ ፥ ዘመዶቹንም የማይሰድብ።

ኃጢአተኛ በፊቱ የተናቀ ፥ እግዚአብሔርንም የሚፈሩትን የሚያከብር ፥ ለባልንጀራው የሚምል የማይከዳም። ገንዘቡን በአራጣ የማያበድር ፥ በንጹሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል። እንዲህ የሚያደርግ ለዘላለም አይታወክም። ❞ [ መዝ.፲፭፥፩-፭]


💖                    🕊                    💖
1
2
                          †                          

      [   🕊    ማር ሚና      🕊   ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

🕊 † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊

❝ ጻድቃን ስለአንተ ታመሙ [ መከራን ተቀበሉ ] መከራቸውም ደስታ ሆነላቸው ፣ ክብር ይገባቸዋል ፣ በተጋድሎአቸው ሰማዕታት ፣ በትዕግስታቸውም መንግሥተ ሰማያትን ወረሱ። ❞

🕊

[  ቅዱስ ያሬድ   ]

†                       †                       †

የቅዱስ ሚናስ ምልጃና ጸሎቱ ከዘለዓለም እሳት ያድነን:: ጸጋ በረከቱ ይክፈለን::

🍒

†                       †                       †
💖                    🕊                    💖
2
1
                       †                       

  [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]

[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]

🕊             

[    " ቅ ዱ ሳ ት   መ ጻ ሕ ፍ ት  "    ]
             
             [     ክፍል ዘጠኝ     ]

❝ ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም ፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና ፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። ❞ [ ፪ጴጥ.፩፥፳ ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬

       💖   ድንቅ ትምህርት  💖

[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]

የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
                         👇
1
🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

🕊  † ቅዱስ አቡናፍር ገዳማዊ  †  🕊

ጻድቁ ተወልዶ ያደገው በ፭ [5] ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብፅ ነው:: ወቅቱ ሥርዓተ መነኮሳት የሚጠበቅበት:አበው ባሕታውያን እንደ ሰማይ ከዋክብት በዝተው የደመቁበት ነበር:: ታላቁ አቡናፍርም ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: በሥርዓት አድጎ: መጻሕፍትንም ተምሮ ገና በወጣትነቱ መንኗል::

ሥርዓተ መነኮሳትን ከአባ ኤስድሮስ ታላቁ አጥንቶ ገዳሙንና መምሕሩን እየረዳ ለብዙ ዓመታት በጾምና በጸሎት ኑሯል:: መነኮሳቱ ስለ ትሕትናውና ስለ ታዛዥነቱ ፈጽመው ያከብሩት ነበር::

ከዕለታት በአንዱ ቀን አረጋውያን መነኮሳት ጭው ባለ በርሃ ስለሚኖሩ ባሕታውያን ሲጨዋወቱ: ሲያደንቁዋቸውም ሰማ:: እርሱ በዛ ወቅት ባሕታውያን በበርሃ መኖራቸውን አያውቅም ነበርና ሒዶ መምሕሩን አባ ኤስድሮስን ጠየቃቸው:: እርሳቸውም "አዎ ልጄ! ከዚሕ በጣም ርቅው: ንጽሕናቸውን ጠብቀው: ከሰውና ከኃጢአት ተይለው የሚኖሩ ገዳማውያን አሉ" አሉት::

ቅዱስ አቡናፍር "በዚሕ ካሉት መነኮሳትና በበርሃ ካሉት ማን ይበልጣል?" ቢላቸው "እነርሱ በጣም ይበልጣሉ:: ዓለም እንኩዋ ከነ ክብሯ የእግራቸውን ሰኮና አታህልም" አሉት:: ይሕንን የሰማው ቅዱስ አባ አቡናፍር ጊዜ አላጠፋም::

ከመምሕሩ ቡራኬ ተቀብሎ ወደ በርሃ ሔደ:: ለብዙ ቀናት ከተጉዋዘ በኋላ አንድ ባሕታዊ አግኝቶ አብሯቸው ተቀመጠ:: ከእርሳቸው ዘንድም ሥርዓተ ባሕታውያንን ተምሮ እንደገና ወደ ዋናው በርሃ ጉዞውን ቀጠለ::

ከብዙ ቀናት መንገድ በኋላም አንድ ሠፊ ሜዳ ላይ ደረሰ:: አካባቢው የውሃ ጠብታ የማይገኝበት: ይቅርና መጠለያ ዛፍ የሣር ዘር እንኩዋ የሌለበት ወይም በልሳነ አበው "ዋዕየ ፀሐይ የጸናበት: ልምላሜ ሣዕር የሌለበት: ነቅዐ ማይ የማይገኝበት" ቦታ ነበር:: በዚህ ቦታ ይቅርና የሰው ልጅ አራዊትም አይኖሩበትም::

ለአባ አቡናፍር ግን ተመራጭ ቦታ ነበር:: ቅዱሳኑን ይሕ አያሳስባቸውም:: ምክንያቱም ለእነርሱ ምግባቸውም: ልብሳቸውም ፍቅረ ክርስቶስ ነውና:: አባ አቡናፍር ወደ ፈጣሪ ጸለዩ:: በእግዚአብሔር ቸርነት ከጎናቸው አንዲት ዘንባባ [በቀልት] በቀለች:: ከእግራቸው ሥርም ጽሩይ ማይ [ንጹሕ ምንጭ] ፈለቀች::

ጻድቁ ተጋድሏቸውን ቀጠሉ:: ዓመታት አለፉ:: ልብሳቸውን ፀሐይና ብርድ ጨርሶት ቅጠል ለበሱ:: በዚያ ቦታም የሰው ዘርን ሳያዩ ለ፷ [60] ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ:: የሚያርፉበት ጊዜ ሲደርስ እግዚአብሔር አባ በፍኑትዮስን [የባሕታውያንን ዜና የጻፈ አባት ነው] ላከላቸው::

ቃለ እግዚአብሔርን እየተጨዋወቱ ሳለ የአባ አቡናፍር አካሉ ተለወጠ:: እንደ እሳትም ነደደ:: አባ በፍኑትዮስም ደነገጠ:: ታላቁ ገዳማዊ ግን እጆቻቸውን ዘርግተው ጸለዩ: ሰገዱና አማተቡ:: ነፍሳቸውም ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ቅዱሳን መላዕክትም በዝማሬና በማኅሌት አሳረጉዋት:: የሚገርመው ደግሞ አባ በፍኑትዮስ ይሕን ሲያይ ቆይቶ ዘወር ቢል ዛፏ ወድቃለች: ቅርንጯም ደርቃለች::

ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱሳን አበው ባሕታውያን መታሠቢያ ናት::

ከሰው [ ከዓለም ] ርቀው: ንጽሕ ጠብቀው: ዕጸበ ገዳሙን: ግርማ አራዊቱን: ጸብዐ አጋንንትን ታግሠው የኖሩ: ስማቸውን የምናውቀውንም ሆነ የማናውቃቸውን እንድናከብራቸው ቤተ-ክርስቲያን ሥርዓትና በዓል ሠርታለች::

አምላካችን ከአበው ባሕታውያን ጸጋ በረከት ይክፈለን::

🕊

[ † ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. አባ አቡናፍር ገዳማዊ [ስም አጠራሩ የከበረ:
ሽምግልናው ያማረ አባት]
፪. አበው ቅዱሳን ባሕታውያን [ ዛሬ የሁሉም ቅዱሳን ባሕታውያን [በተለይም የስውራኑ] ዓመታዊ በዓል ነው::

- ከሰው: ከዓለምና ከኃጢአት ርቀው
- ንጽሕ ጠብቀው
- ዕጸበ ገዳሙን
- ድምጸ አራዊቱን
- ግርማ ሌሊቱን
- የሌሊቱን ቁር
- የመዓልቱን ሐሩር
- ረሐቡን: ጽሙን: መራቆቱን . . . ሁሉ
ስለ ፍቅረ-ክርስቶስ ሲሉ ታግሠውታልና::

"ዛሬም በየበርሃው የወደቁ: ስለ ዓለም ምሕረትን
የሚማጸኑ አሉ::"

አምላካቸው በረከታቸውን ያድለን።

፫. የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ከግብጽ እንዲመለስ የነገረበት [ተዝካረ ሚጠታ ለእግዝእትነ ማርያም]
፬. አፄ ይኩኖ አምላክ [ንጉሠ ኢትዮዽያ]

[ †  ወርኃዊ በዓላት ]

፩፡ ኪዳነ ምሕረት ማርያም
፪፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ
፫፡ አባ ዳንኤል ገዳማዊ
፬፡ ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሠ ሮሜ
፭፡ አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
፮፡ ቅዱስ ሐርቤ ንጉሠ ኢትዮጵያ

" . . . ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ: ከዚሕም በላይ በእሥራትና በወኅኒ ተፈተኑ . . . ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ: የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ:: ዕብ.፲፩፥፴፮] (11:36) "

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
2
5
#ኪዳነምህረት_እናቴ 16 🙏🙏

#የብርሃን_እናቱ_ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡ መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድህነታችን ተሰራ #ድንግል_ሆይ እውነተኛው የህይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ አማናዊው የፅድቅ ብርሀን የፈነጠቀብሽ ነሽና ከትውልድ መሀል #ብፅዕናሽን እንናገራለን ጥማችንን የቆረጠ ጥዑም ወይን ረሀባችንን ያጠፋ እውነተኛው መብል ካንቺ ወጥቶልናልና #እንወድሻለን ምስራቃዊት በራችን ሆይ ከሴቶች አንችን የሚመስል የለም፡ ባንቺ ላይ ስለተደረገልን ታላቅ ነገር ዛሬም ለዘላለምም ስምሽን እናገናለን፡፡

#ዝምተኛይቱ_ድንግል_ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ።

#አንችን_ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው #ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ #እናመሰግንሻለን። ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ አሜን🙏

           #_ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
10🙏2
🕊                      †                        🕊

[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[   በቦታው ሁሉ ምሉ ነውና !  ]

🕊                    💖                       🕊


❝ ነፍሱን በሲኦል አልተወም ፥ ሥጋውም ሙስና መቃብርን አላየም። መለኮት ከሁለቱ [ ከነፍስ ከሥጋ ] አልተለየም ፤ ሁለንተናው ከነፍስ ጋር በሲኦል ነበረ። በሲኦልም ለጻድቃን የምሥራችን አበሠረ። ሁለንተናውም ከሥጋ ጋር በመቃብር ነበረ እንጂ። በቦታው ሁሉ ምሉ ነውና መለኮት በሕማም ድል አይነሣም ለሕማም አይገኝም። [ መዝ.፲፮ [፲፭]፥፲ ፤ ፹፰ [፹፯]፥፫-፮ ። ግብ ሐዋ.፪፥፳፯ ። ፩ጴጥ.፫፥፲፱ ና ፳ ]

ሌሎችም ባለማወቃቸው ቃል ሰው ስለመሆኑ ሲናገሩ 'ነፍስን ሥጋን አልነሣም እግዚአብሔር ቃል እንደ ዕሩቅ ብእሲ መርጦ አደረበት እንጂ' ይላሉ። ዳግመኛም ቃል በባሕርዩ እንደ ታመመ እንደ ሞተ  አብም እንደ አስነሣው ይናገራሉ ፥ ይህንን የሚናገሩ ሦስቱ ሞቱ እንዲያሰኝባቸው አያውቁም።

እግዚአብሔር ቃል በባሕርዩ ከሞተስ እነሆ አብም ዳግመኛ ሞተ እርሱ ራሱ [ ወልድ ] እኔ በአብ ህልው ነኝ አብም በእኔ ህልው ነው እኛ አንድ ነን ብሏልና።

ዳግመኛ እኔን ያየ አባቴን አየ ብሏልና ፤ ይህም እኔ የነገርኳችሁ ቃል እኔ ከራሴ አንቅቼ የነገርኳችሁ አይደለም ፤ በእኔ ህልውና ያለ አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል እንጂ ብሏልና።

እኛ ግን ፦

ከእኛ ባሕርይ በነሣው ሥጋ እንደ ታመመ እንደ ሞተ እናምናለን
። እርሱ እግዚአብሔር ቃልም የተዋሐደውን ሥጋ ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ፤ ያስነሣውም ሌላ እንዳይደለ እናምናለን ፤ ቅዱሳን አባቶቻችን ያስተማሩትን ትምህርት ትተው ክርስቶስ ፈጽሞ እንዳልታመመ እንዳልሞተ እንዳልተነሣ የሚናገሩ አሉ ፤ ይህንንም በመናገራቸው መለኮት ያጻፋቸውን መጻሕፍት ሁሉ ይለውጣሉ ፤ ሐሰትም ያደርጓቸዋል። [ ፪ጴጥ.፪፥፫-፲፮ ]

ለእኛ ግን ፦

እግዚአብሔር ያጻፋቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ትምህርታችን ናቸው። መንፈስ ቅዱስም ክርስቶስ የማይታመም ፍጹም አምላክ ፤ የሚታመም ፍጹም ሰው ያለመለየትም አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው ብሎ በሐዋርያት አድሮ ተናገረ ፤ በሊቃውንት አድሮ አስተማረ ፤ ካልታመመ ካልሞተ ፤ ካልተነሣ ሌሎችን እንደምን ያስነሣል ?
[ ፩ቆሮ.፲፪፥፫ ፤ ፩ጴጥ.፩፥፲፩ ]

አልሞተም አልተነሣም የሚሉ ግን መለኮት ያጻፋቸው መጻሕፍትን ሐሰተኞች ያደርጓቸዋል ፤ ባለማወቃቸውም አምላክ የለም ፤ ትንሣኤም ቢሆን ፤ መንግሥተ ሰማያትም ቢሆን ወቀሳም ቢሆን ፍርድም ሲሆን የለም ይላሉ እርሱ ግን እንደ ከሀሊነቱ የወደደውን ሁሉ ያደርጋል። ❞

[    🕊   ቅዱስ ቄርሎስ   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።


†                         †                         †
💖                     🕊                      💖
4
1
                         †                         


እግዚአብሔር ያጽናናሽ ቅድስት ቤተክርስቲያን !

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

❝ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የፈሰሰው የነቢያት ሁሉ ደም ፥ ከአቤል ደም ጀምሮ በመሠዊያውና በቤተ መቅደስ መካከል እስከ ጠፋው እስከ [ ካህኑ ] ዘካርያስ ደም ድረስ ፥ ከዚህ ትውልድ እንዲፈለግ አዎን እላችኋለሁ ፥ ከዚህ ትውልድ ይፈለጋል። ❞

[ ሉቃ.፲፩፥፶ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
😢7
2025/07/08 20:07:06
Back to Top
HTML Embed Code: