#ወዳጆቼ
#ይህ_ብርድ አንድ ታላቅ ውለታ አያስታውስህም
ብርድ ሲበርድህ የብርድ መከላከያ ነገር ትፈልጋለህ (ብርድ ልብስ) #ለስጋህ እንዲህ አደረክ
#ነፍስህ ስትበረድስ ምን ታለብሳት?
አዳምና ሔዋን #በኀጢአት ብርድ በወደቁ ጊዜ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ #የኀጢአት_ብርድን አስወገደላቸው።
ታዲያ ወዳጄ በነፍስ ተበርደህ ከሆነ መፍትሄው #ክርስቶስን መልበስ ነው
"፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን #ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም #ለሥጋ አታስቡ።
(ወደ ሮሜ ሰዎች 13: 14)
#መልካም__ቀን 🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ይህ_ብርድ አንድ ታላቅ ውለታ አያስታውስህም
ብርድ ሲበርድህ የብርድ መከላከያ ነገር ትፈልጋለህ (ብርድ ልብስ) #ለስጋህ እንዲህ አደረክ
#ነፍስህ ስትበረድስ ምን ታለብሳት?
አዳምና ሔዋን #በኀጢአት ብርድ በወደቁ ጊዜ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ #የኀጢአት_ብርድን አስወገደላቸው።
ታዲያ ወዳጄ በነፍስ ተበርደህ ከሆነ መፍትሄው #ክርስቶስን መልበስ ነው
"፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን #ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም #ለሥጋ አታስቡ።
(ወደ ሮሜ ሰዎች 13: 14)
#መልካም__ቀን 🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤12🙏5
†
🕊 💖 ዼጥሮስ ወዻውሎስ 💖 🕊
🕊
[ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ]
❝ ስማቸው ጴጥሮስና እንድርያስ ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ፣ ፊልጶስና በርተሎሜዎስ ፣ ቶማስና ማቴዎስ ፣ ታዴዎስና ናትናኤል ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብና ማትያን በመባል ለሚጠሩ ለ ፲፪ ቱ የመድኅን ሐዋርያት ሰላምታ ይገባል። ❞
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ አቤቱ በስምኽ የሰበኩ ፤ በታላቅ መከራ በረኀብና በጥም ፤ በብርድና በመራቆት ፤ በመውዛትና በመድከም ፤ ከነገሥታትና ከመኳንንት ዘንድ ተፈርዶባቸው መከራን በመቀበል በምድር ኹሉ ውስጥ የቃልኽን መዝገብ ስለዘሩ ስለነዚኽ ደቀ መዛሙርትኽ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ በእሳት በመከራ የተቀበለ አለ ፤ በጦርም የተወጋ አለ ፤ በሰይፍም የተቆረጠ አለ ፤ በመንኰራኲርም የተፈጨ አለ ፤ በደንጊያም የተወገረ ፤ በበትርም የተቀጠቀጠ አለ ፤ ስለነርሱ ብለኽ ማረኝ አስበኝም ፤ ስለሥቃያቸው ስለመቸገራቸውና ስለደማቸው ብለኽ የእኔን የአገልጋይኽን የዕዳ መጽሐፌን ቅደድ ፤ አሜን። ❞
[ ተአምኆ ቅዱሳን ]
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን ፣
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ።
† 🕊 እንኳን አደረሰን 🕊 †
🕊 💖 🕊
🕊 💖 ዼጥሮስ ወዻውሎስ 💖 🕊
🕊
[ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ]
❝ ስማቸው ጴጥሮስና እንድርያስ ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ፣ ፊልጶስና በርተሎሜዎስ ፣ ቶማስና ማቴዎስ ፣ ታዴዎስና ናትናኤል ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብና ማትያን በመባል ለሚጠሩ ለ ፲፪ ቱ የመድኅን ሐዋርያት ሰላምታ ይገባል። ❞
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ አቤቱ በስምኽ የሰበኩ ፤ በታላቅ መከራ በረኀብና በጥም ፤ በብርድና በመራቆት ፤ በመውዛትና በመድከም ፤ ከነገሥታትና ከመኳንንት ዘንድ ተፈርዶባቸው መከራን በመቀበል በምድር ኹሉ ውስጥ የቃልኽን መዝገብ ስለዘሩ ስለነዚኽ ደቀ መዛሙርትኽ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ በእሳት በመከራ የተቀበለ አለ ፤ በጦርም የተወጋ አለ ፤ በሰይፍም የተቆረጠ አለ ፤ በመንኰራኲርም የተፈጨ አለ ፤ በደንጊያም የተወገረ ፤ በበትርም የተቀጠቀጠ አለ ፤ ስለነርሱ ብለኽ ማረኝ አስበኝም ፤ ስለሥቃያቸው ስለመቸገራቸውና ስለደማቸው ብለኽ የእኔን የአገልጋይኽን የዕዳ መጽሐፌን ቅደድ ፤ አሜን። ❞
[ ተአምኆ ቅዱሳን ]
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን ፣
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ።
† 🕊 እንኳን አደረሰን 🕊 †
🕊 💖 🕊
🙏2
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ ሐምሌ ፭ ❖
[ 🕊 ✞ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ 🕊 ]
ፍጡር ቢከብር ከእመ ብርሃን ቀጥሎ የእነዚህን ቅዱሳን ያህል የሚከብር አይኖርም:: ለቤተ ክርስቲያን ያልሆኑላት ምንም ነገር የለምና እርሷም "ብርሃኖቼ: ዐይኖቼ: ዕንቁዎቼ" ብላ ትጠራቸዋለች::
🕊 † ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት † 🕊
የዮና ልጅ ስምዖን ዼጥሮስ [ኬፋ] የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው:: ይሔውም ዓለት [መሰረት] እንደ ማለት ነው::
¤ በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሳ በማጥመድ አድጐ
¤ ሚስት አግብቶ ዕድሜው ፶፮ [56] ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው:: በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ: በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል:: ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል:: [ማቴ.፲፮፥፲፯] (16:17) , [ዮሐ.፳፩፥፲፭] (21:15)
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሰራው ስሕተት ንስሃ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል:: ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በሁዋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል:: ምንም የርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል::
በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል:: አሕዛብ ግብራቸው እንደ እንስሳ ነውና በአባታችን ላይ ቀልደዋል:: እርሱ ግን ሁሉንም ታግሷል:: የቅዱሱን ታሪክ ለመናገር ከመብዛቱ የተነሳ ይከብዳልና ልቡና ያለው ሰው ሊቃውንትን ሊጠይቅ እንደሚገባ እመክራለሁ::
ቅዱስ ዼጥሮስ መልካሙን ገድል ተጋድሎ በ፷፮ [66] ዓ/ም የኔሮን ቄሳር ወታደሮች ሲሰቅሉት ለመናቸው:: "እባካችሁን? እኔ እንደ ጌታየ ሆኜ መሰቀል አይገባኝም" አላቸው:: እነሱም ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: በበጐ እረኝነቱም የማታልፈውን ርስት ከነመክፈቻዋ ተቀብሏል:: በሰማዕትነት ሲያርፍም ዕድሜው ወደ ፹፰ [88] አካባብ ደርሶ ነበር::
† የቅዱስ ዼጥሮስ መጠሪያዎች :-
፩. ሊቀ ሐዋርያት
፪. ሊቀ ኖሎት [የእረኞች / ሐዋርያት አለቃ]
፫. መሠረተ ቤተ ክርስቲያን
፬. ኰኩሐ ሃይማኖት [የሃይማኖት ዐለት]
፭. አርሳይሮስ [የዓለም ሁሉ ፓትርያርክ]
🕊 † ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ † 🕊
የቤተ ክርስቲያን መብራቷ ቅዱስ ዻውሎስን እንደ ምን ባለ አማርኛ እንገልጠዋለን?
¤ ስለ እርሱ መናገርና መጻፍ የሚችልስ እንደ ምን ያለ ሰው ነው?
¤ የዓለምን ነገር ሲጽፍ በኖረ እጄስ እንደ ምን እጽፈዋለሁ?
¤ ይልቁኑስ የርሱን ፲፬ [14] ቱን መልዕክታትና ግብረ ሐዋርያትን መመልከቱ ሳይሻል አይቀርም::
ቅዱስ ዻውሎስ ከነገደ ብንያም ሳውል የሚባል የጠርሴስ ሰው ሲሆን ምሑረ ኦሪት: ቀናተኛና ፈሪሳዊ ነበር:: ጌታ በደማስቆ ጐዳና ጠርቶ በ፫ [3] ቀናት ልዩነት ምርጥ ዕቃ አደረገው:: ይህ የሆነው በ፵፪ [42] ዓ/ም: ጌታ ባረገ በ፰ [8] ኛው ዓመት ነበር:: ከዚያማ ብርሃን ሆኖ አበራ:: ጨው ሆኖ አጣፈጠ::
ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም: ከእንግሊዝ እስከ እልዋሪቆን [የዓለም መጨረሻ] ወንጌልን ሰበከ:: ስለ ወንጌል ተደበደበ: ታሠረ: በእሳት ተቃጠለ:: በድንጋይ ተወገረ: በጦር ተወጋ:: ባፍም በመጣፍም ብሎ አገለገለ:: በየቦታውም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ሠራ:: ለ፳፭ [25] ዓመታት ቀንና ሌሊት ያለ መታከት ወንጌልን ሰበከ::
እርሱን የመሰሉ: እርሱንም ያከሉ ብዙ አርድእትን አፍርቶ: በ፷፯ [67] ዓ/ም በኔሮን ቄሳር ትእዛዝ አንገቱ ተቆርጧል:: ከ፲፬ [14] ቱ መልዕክታቱ ባሻገር ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን ሲጽፍ አግዞታል:: ልክ ቅዱስ ዼጥሮስ ማርቆስን እንዳገዘው ማለት ነው::
🕊 † የቅዱስ ዻውሎስ መጠሪያዎች ፦
፩. ሳውል [ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ]
፪. ልሳነ ዕፍረት [አንደበቱ እንደ ሽቱ የሚጣፍጥ]
፫. ልሳነ ክርስቶስ [የክርስቶስ አንደበቱ]
፬. ብርሃነ ዓለም
፭. ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን [የቤተ ክርስቲያን መቅረዝ]
፮. የአሕዛብ መምሕር
፯. መራሒ [ወደ መንግስተ ሰማያት የሚመራ]
፰. አእኩዋቲ [በምስጋና የተሞላ]
፱. ንዋይ ኅሩይ [ምርጥ ዕቃ]
፲. መዶሻ [ለአጋንንትና መናፍቃን]
፲፩. መርስ [ወደብ]
፲፪. ዛኅን [ጸጥታ]
፲፫. ነቅዐ ሕይወት [የሕይወት ትምሕርትን ከአንደበቱ
ያፈለቀ]
፲፬. ዐዘቅተ ጥበብ [የጥበብ ምንጭ / ባሕር]
፲፭. ፈዋሴ ዱያን [ድውያንን የፈወሰ] . . .
ጌታችን እግዚአብሔር የአባቶቻችንን ብርሃን ያብራልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
፫. ቅዱሳን ፸፪ [72] ቱ አርድእት [ዛሬ ሁሉም ይታሠባሉ]
፬. ቅዱስ ሳቁኤል ሊቀ መላእክት
፭. ቅድስት መስቀል ክብራ [የቅዱስ ላሊበላ ሚስት]
፮. ቅዱሳን ዘደብረ ዓሣ
፯. ቅዱሳት አንስት [ዴውርስ: ቃርያ: አቅባማ: አቅረባንያና አክስቲያና-የቅዱስ ዼጥሮስ ተከታዮች]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
፪. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
፫. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
፬. ቅድስት አውጋንያ [ሰማዕትና ጻድቅ]
"ጌታ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው:: "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ! በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይሕንን አልገለጠልህምና ብጹዕ ነህ:: እኔም እልሃለሁ:: አንተ ዼጥሮስ ነህ:: በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ:: የገሃነም ደጆችም አይችሏትም:: የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ:: በምድር የምታሥረው ሁሉ በሰማያት የታሠረ ይሆናል:: በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል::" [ማቴ.፲፮፥፲፯] (16:17)
" በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና:: የምሔድበትም ጊዜ ደርሷል:: መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ:: ሩጫውን ጨርሻለሁ:: ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ:: ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል:: ይሕንም ጻድቅ: ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል:: " [፪ጢሞ.፬፥፮] (4:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ ሐምሌ ፭ ❖
[ 🕊 ✞ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ 🕊 ]
ፍጡር ቢከብር ከእመ ብርሃን ቀጥሎ የእነዚህን ቅዱሳን ያህል የሚከብር አይኖርም:: ለቤተ ክርስቲያን ያልሆኑላት ምንም ነገር የለምና እርሷም "ብርሃኖቼ: ዐይኖቼ: ዕንቁዎቼ" ብላ ትጠራቸዋለች::
🕊 † ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት † 🕊
የዮና ልጅ ስምዖን ዼጥሮስ [ኬፋ] የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው:: ይሔውም ዓለት [መሰረት] እንደ ማለት ነው::
¤ በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሳ በማጥመድ አድጐ
¤ ሚስት አግብቶ ዕድሜው ፶፮ [56] ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው:: በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ: በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል:: ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል:: [ማቴ.፲፮፥፲፯] (16:17) , [ዮሐ.፳፩፥፲፭] (21:15)
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሰራው ስሕተት ንስሃ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል:: ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በሁዋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል:: ምንም የርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል::
በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል:: አሕዛብ ግብራቸው እንደ እንስሳ ነውና በአባታችን ላይ ቀልደዋል:: እርሱ ግን ሁሉንም ታግሷል:: የቅዱሱን ታሪክ ለመናገር ከመብዛቱ የተነሳ ይከብዳልና ልቡና ያለው ሰው ሊቃውንትን ሊጠይቅ እንደሚገባ እመክራለሁ::
ቅዱስ ዼጥሮስ መልካሙን ገድል ተጋድሎ በ፷፮ [66] ዓ/ም የኔሮን ቄሳር ወታደሮች ሲሰቅሉት ለመናቸው:: "እባካችሁን? እኔ እንደ ጌታየ ሆኜ መሰቀል አይገባኝም" አላቸው:: እነሱም ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: በበጐ እረኝነቱም የማታልፈውን ርስት ከነመክፈቻዋ ተቀብሏል:: በሰማዕትነት ሲያርፍም ዕድሜው ወደ ፹፰ [88] አካባብ ደርሶ ነበር::
† የቅዱስ ዼጥሮስ መጠሪያዎች :-
፩. ሊቀ ሐዋርያት
፪. ሊቀ ኖሎት [የእረኞች / ሐዋርያት አለቃ]
፫. መሠረተ ቤተ ክርስቲያን
፬. ኰኩሐ ሃይማኖት [የሃይማኖት ዐለት]
፭. አርሳይሮስ [የዓለም ሁሉ ፓትርያርክ]
🕊 † ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ † 🕊
የቤተ ክርስቲያን መብራቷ ቅዱስ ዻውሎስን እንደ ምን ባለ አማርኛ እንገልጠዋለን?
¤ ስለ እርሱ መናገርና መጻፍ የሚችልስ እንደ ምን ያለ ሰው ነው?
¤ የዓለምን ነገር ሲጽፍ በኖረ እጄስ እንደ ምን እጽፈዋለሁ?
¤ ይልቁኑስ የርሱን ፲፬ [14] ቱን መልዕክታትና ግብረ ሐዋርያትን መመልከቱ ሳይሻል አይቀርም::
ቅዱስ ዻውሎስ ከነገደ ብንያም ሳውል የሚባል የጠርሴስ ሰው ሲሆን ምሑረ ኦሪት: ቀናተኛና ፈሪሳዊ ነበር:: ጌታ በደማስቆ ጐዳና ጠርቶ በ፫ [3] ቀናት ልዩነት ምርጥ ዕቃ አደረገው:: ይህ የሆነው በ፵፪ [42] ዓ/ም: ጌታ ባረገ በ፰ [8] ኛው ዓመት ነበር:: ከዚያማ ብርሃን ሆኖ አበራ:: ጨው ሆኖ አጣፈጠ::
ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም: ከእንግሊዝ እስከ እልዋሪቆን [የዓለም መጨረሻ] ወንጌልን ሰበከ:: ስለ ወንጌል ተደበደበ: ታሠረ: በእሳት ተቃጠለ:: በድንጋይ ተወገረ: በጦር ተወጋ:: ባፍም በመጣፍም ብሎ አገለገለ:: በየቦታውም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ሠራ:: ለ፳፭ [25] ዓመታት ቀንና ሌሊት ያለ መታከት ወንጌልን ሰበከ::
እርሱን የመሰሉ: እርሱንም ያከሉ ብዙ አርድእትን አፍርቶ: በ፷፯ [67] ዓ/ም በኔሮን ቄሳር ትእዛዝ አንገቱ ተቆርጧል:: ከ፲፬ [14] ቱ መልዕክታቱ ባሻገር ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን ሲጽፍ አግዞታል:: ልክ ቅዱስ ዼጥሮስ ማርቆስን እንዳገዘው ማለት ነው::
🕊 † የቅዱስ ዻውሎስ መጠሪያዎች ፦
፩. ሳውል [ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ]
፪. ልሳነ ዕፍረት [አንደበቱ እንደ ሽቱ የሚጣፍጥ]
፫. ልሳነ ክርስቶስ [የክርስቶስ አንደበቱ]
፬. ብርሃነ ዓለም
፭. ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን [የቤተ ክርስቲያን መቅረዝ]
፮. የአሕዛብ መምሕር
፯. መራሒ [ወደ መንግስተ ሰማያት የሚመራ]
፰. አእኩዋቲ [በምስጋና የተሞላ]
፱. ንዋይ ኅሩይ [ምርጥ ዕቃ]
፲. መዶሻ [ለአጋንንትና መናፍቃን]
፲፩. መርስ [ወደብ]
፲፪. ዛኅን [ጸጥታ]
፲፫. ነቅዐ ሕይወት [የሕይወት ትምሕርትን ከአንደበቱ
ያፈለቀ]
፲፬. ዐዘቅተ ጥበብ [የጥበብ ምንጭ / ባሕር]
፲፭. ፈዋሴ ዱያን [ድውያንን የፈወሰ] . . .
ጌታችን እግዚአብሔር የአባቶቻችንን ብርሃን ያብራልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
፫. ቅዱሳን ፸፪ [72] ቱ አርድእት [ዛሬ ሁሉም ይታሠባሉ]
፬. ቅዱስ ሳቁኤል ሊቀ መላእክት
፭. ቅድስት መስቀል ክብራ [የቅዱስ ላሊበላ ሚስት]
፮. ቅዱሳን ዘደብረ ዓሣ
፯. ቅዱሳት አንስት [ዴውርስ: ቃርያ: አቅባማ: አቅረባንያና አክስቲያና-የቅዱስ ዼጥሮስ ተከታዮች]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
፪. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
፫. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
፬. ቅድስት አውጋንያ [ሰማዕትና ጻድቅ]
"ጌታ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው:: "የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ! በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይሕንን አልገለጠልህምና ብጹዕ ነህ:: እኔም እልሃለሁ:: አንተ ዼጥሮስ ነህ:: በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ:: የገሃነም ደጆችም አይችሏትም:: የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ:: በምድር የምታሥረው ሁሉ በሰማያት የታሠረ ይሆናል:: በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል::" [ማቴ.፲፮፥፲፯] (16:17)
" በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና:: የምሔድበትም ጊዜ ደርሷል:: መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ:: ሩጫውን ጨርሻለሁ:: ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ:: ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል:: ይሕንም ጻድቅ: ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል:: " [፪ጢሞ.፬፥፮] (4:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤2🙏1