EOTCLIBILERY Telegram 15581
የማርያም አዳራሽ - መርጡለ ማርያም !

ባሕር ዳር: ጥር 21/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጎጃም ከሚገኙት አያሌ ቅዱሳት ገደማት መካከል አንዷ የታላቋ እና የጥንታዊቷ ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ-ማርያም ገዳም ናት።

ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጎጃም በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መርጡለ-ማርያም ነው።

መርጡለ-ማርያም ትርጉሙ የማርያም አዳራሽ ማለት ነው። ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም አሁን የያዘችውን የስም መጠሪያ ከመያዟ በፊት በተለያዩ ዘመናት አራት ጊዜ የስም መለዋወጦች አጋጥሟታል።

መጀመሪያ ሀገረ ሰላም ቀጥሎ ሀገረ እግዚአብሔር ተብላለች። ከዚያም ጽርሐ አርያም ተብላ ተጠርታለች በመጨረሻም አሁን የምትጠራበትን መርጡለ ማርያም የሚለውን ስያሜ አግኝታለች።

ይች ታላቅ እና ጥንታዊት ገዳም የተመሠረተችው ከእስራኤሉ ንጉሥ ሰሎሞን እና ከኢትዮጵያዊት ንግሥት ሳባ (ማክዳ) የተወለደው ቀዳማዊ ምኒሊክ ይዟቸው በመጣ ፫፻፲፰ (318) የኦሪት ካህናት በ4500 ዓመተ ዓለም ነው።

ወደ ዚች ቦታ የመጡት የኦሪት ካህናት መሥዋዕተ ኦሪትን በመሰዋት የኦሪትን አምልዕኮት ሲፈጽሙ ኖረዋል። መርጡለ ማርያም በኢትዮጵያ መስዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባቸው ከነበሩት አራቱ ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም አክሱም ጽዮን፣ ተድባበ ማርያም እና ጣና ቂርቆስ መካከል አንዷ ነበረች፡፡

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ እና ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እንደሚያስረዱት ሕሩያን ነገሥታት አብርሃ ወ አጽብሃ ከጳጳሱ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጋር በመኾን በ፫፻፴፫ (333) ዓ.ም ዓባይን ተሻግረው ጎጃም ምድር መርጡለ ማርያም ደረሱ።

በዚህ ቦታ ሕዝበ ክርስቲያኑን ወንጌል አስተምረው መክረው ከኦሪት ወደ ሐዲስ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሰው ካጠመቁ በኋላ ሕዝበ ክርስቲያኑ አምልኮቱን የሚፈጽምበት ቤተ ክርስቲያንን ለመሥራት አሰቡ።

ቦታው ላይ የሚያምር ቤተ ምኩራብ ስለ ነበር ይህንን ለታሪክ ትተን ሌላ ቦታ ላይ እንሥራ በማለት በስተምሥራቅ አሻጋሪ ካለው ተራራ አሁን ግንብ ወሬ እየተባለ ከሚጠራው ኮረብታ ላይ ቁፋሮ ጀመሩ።

ነገር ግን መሬቱ የእሳት ትንታግ እየተፋ አልቆፈር አለ። በመኾኑም በዚህ ቦታ ቤተ ክርስቲያን እንሠራ ዘንድ እግዚአብሔር አልፈቀደም። ፈቃደ እግዚአብሔርን እናውቅ ዘንድ ለ፫ (3) ተከታታይ ቀናት ሱባኤ እንግባ በማለት በ፭ (5) በአካባቢው ባሉ የተለያዩ ኮረብታዎች ሱባኤ ገቡ።

ሱባኤ የገቡባቸው ከረብታዎችም፡-
👉የኦሪቱ ሊቀ ካህን አብኒ ኮረብታ
የሐዲሱ ሹም ሐዲስጌ ኮረብታ
👉የጳጳሱ አቡነ ሰላማ ሰላምጌ ኮረብታ
👉በንጉሥ አብርሃ አብርሂ ኮረብታ
👉በንጉሥ አጽብሃ ዜነዎ ኮረብታ ላይ እንደነበሩ ይነገራል

ንጉሥ አጽብሃም ከሁሉም አስቀድሞ ወደ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በመሄድ ያየውን ራዕይ ተናገረ። ሌሎችም መጥተው ያዩትን ሁሉ ተናገሩ አባ ሰላማም ይህንን ራዕይ ያዩ መኾናቸውን ነገሯቸው። ሁሉም በአንዲት ሌሊት አንድ ዓይነት ራዕይ አዩ።

ያዩት ራዕይም « ዐሥራ ሁለት በሮች ያላት አንድ አምደ ብርሃን የቤተ መቅደሱ መሠረት ከተጀመረበት ኮረብታ ተነስታ እያበራች የጥንቱ ቤተ ምኲራብ ከሚገኝበት ጽርሐ አርያም አምባላይ ስታርፍ » ነበር፡፡

ጧት ወደ ቦታው ሲሄዱ የጥንቱ አስደናቂው ቤተ ምኩራብ መሬት ውስጥ ተቀብሮ ለጥያለ አረንጓዴ ሜዳ ኾኖ አገኙት፡፡

ነገሥታቱ አብርሃ ወ አጽብሃ በቦታው ቤተ መቅደስን ይሠሩ ዘንድ ወደዱ። በወርቅ እና በእንቁ አምዶችን እና አረፍቶችን ልዩ አድርገው በማስጌጥ የማርያምን ቤተመቅደስ ሠሩ።

ሥርዓትንም በመደንገግ ካህናትን ዲያቆናትን እንዲሁም ሁሉንም ሊያሥተዳድር የሚችል ሊቀ ካህናት ርዕሰ ርዑሳን ብለው ሾሙ። መቅደሷንም መርጡለ ማርያም ብለው ሰየሟት።

ንጉሥ አብርሃ ወ አጽብሃም እግዚአብሔር በመራቸው መሠረት በጳጳሱ በአባ ሰላማ አስባርከው በጽርሐ አርያም አምባላይ አስደናቂውን ባለ ፲፪ (12) ቤተመቅደስ ባለ ፩ (1) ፎቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው በወርቅ በእንቁ በከበሩ ማዕድናት አስጊጠው ጥር ፳፩ (21) ቀን የእመቤታችንን ጽላት በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስገብተዋል።

ይህ ቤተ ክርስቲያን እጅግ የተለየ በልዩ ልዩ ቅርፅ ያጌጠ በወርቅ እና በእንቁ የተለበጠ አስደናቂ የጥበብ አሻራ ያረፈበት ነበር። ይህ ቤተ መቅደስ በዮዲት ጉዲት ዘመን በ፰፻፵፪ (842) ዓ.ም ተቃጥሏል።

በ፰፻፹፪ (882) ዓ.ም የነገሠው አንበሳ ውድም በዮዲት የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንደገና አሠርቶታል። ይህንን ቤተ ክርስቲያን ዐፄ በእደ ማርያም በ፲፬፻፷ (1460) ዓ.ም አሳድሶታል። ባለቤቱ ንግሥት እሌኒ ደግሞ የአንባውን ዙሪያ አሠርታለች። አሁንም የገዳሟ ዙሪያ የእሌኒ ውድሞ ይባላል።

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ፣ ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተሠራ ዘጋቢ ፕሮግራም እንደሚያስረዳው መርጡለ ማርያም በዋጋ የማይተመን ከፍተኛ የቅርስ ክምችት ያላት ገዳም ናት፡፡

እነዚህ ውድ ቅርሶች በመርጡለ ማርያም ሙዚየም ውስጥ የሚገኙ የአብርሃ ወአጽብሃ የወርቅ መስቀል፣ በ445 ዓ.ም የተጻፈ ግዕዙን በግዕዝ የሚተረጉም አርባዕቱ ወንጌል፣ የአጼ በእደ ማርያም ራስ ቁር እና የወርቅ ለምድ፣ የንግሥት እሌኒ የክብር ካባ እና የብር ዋንጫ፣ የብር እና የወርቅ መስቀሎች፣ የወርቅ አክሊሎች፣ የወርቅ ከበሮ፣ የአጼ ገላውዲዮስ ዳዊት እና ካባ፣ የብራና መጻሕፍት እና የመሳሰሉትን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ጥር 21 የሚከበረው በዓለ አስተርእዮ ማርያም የመርጡለ ማርያም ልዩ የክብረ በዓል ቀን ነው፡፡ አስተርእዮ ማርያም በመርጡለ ማርያም በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች የሚከበር ደማቅ በዓል ነው፡፡

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot



tgoop.com/EotcLibilery/15581
Create:
Last Update:

የማርያም አዳራሽ - መርጡለ ማርያም !

ባሕር ዳር: ጥር 21/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጎጃም ከሚገኙት አያሌ ቅዱሳት ገደማት መካከል አንዷ የታላቋ እና የጥንታዊቷ ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ-ማርያም ገዳም ናት።

ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጎጃም በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መርጡለ-ማርያም ነው።

መርጡለ-ማርያም ትርጉሙ የማርያም አዳራሽ ማለት ነው። ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም አሁን የያዘችውን የስም መጠሪያ ከመያዟ በፊት በተለያዩ ዘመናት አራት ጊዜ የስም መለዋወጦች አጋጥሟታል።

መጀመሪያ ሀገረ ሰላም ቀጥሎ ሀገረ እግዚአብሔር ተብላለች። ከዚያም ጽርሐ አርያም ተብላ ተጠርታለች በመጨረሻም አሁን የምትጠራበትን መርጡለ ማርያም የሚለውን ስያሜ አግኝታለች።

ይች ታላቅ እና ጥንታዊት ገዳም የተመሠረተችው ከእስራኤሉ ንጉሥ ሰሎሞን እና ከኢትዮጵያዊት ንግሥት ሳባ (ማክዳ) የተወለደው ቀዳማዊ ምኒሊክ ይዟቸው በመጣ ፫፻፲፰ (318) የኦሪት ካህናት በ4500 ዓመተ ዓለም ነው።

ወደ ዚች ቦታ የመጡት የኦሪት ካህናት መሥዋዕተ ኦሪትን በመሰዋት የኦሪትን አምልዕኮት ሲፈጽሙ ኖረዋል። መርጡለ ማርያም በኢትዮጵያ መስዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባቸው ከነበሩት አራቱ ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም አክሱም ጽዮን፣ ተድባበ ማርያም እና ጣና ቂርቆስ መካከል አንዷ ነበረች፡፡

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ እና ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እንደሚያስረዱት ሕሩያን ነገሥታት አብርሃ ወ አጽብሃ ከጳጳሱ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጋር በመኾን በ፫፻፴፫ (333) ዓ.ም ዓባይን ተሻግረው ጎጃም ምድር መርጡለ ማርያም ደረሱ።

በዚህ ቦታ ሕዝበ ክርስቲያኑን ወንጌል አስተምረው መክረው ከኦሪት ወደ ሐዲስ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሰው ካጠመቁ በኋላ ሕዝበ ክርስቲያኑ አምልኮቱን የሚፈጽምበት ቤተ ክርስቲያንን ለመሥራት አሰቡ።

ቦታው ላይ የሚያምር ቤተ ምኩራብ ስለ ነበር ይህንን ለታሪክ ትተን ሌላ ቦታ ላይ እንሥራ በማለት በስተምሥራቅ አሻጋሪ ካለው ተራራ አሁን ግንብ ወሬ እየተባለ ከሚጠራው ኮረብታ ላይ ቁፋሮ ጀመሩ።

ነገር ግን መሬቱ የእሳት ትንታግ እየተፋ አልቆፈር አለ። በመኾኑም በዚህ ቦታ ቤተ ክርስቲያን እንሠራ ዘንድ እግዚአብሔር አልፈቀደም። ፈቃደ እግዚአብሔርን እናውቅ ዘንድ ለ፫ (3) ተከታታይ ቀናት ሱባኤ እንግባ በማለት በ፭ (5) በአካባቢው ባሉ የተለያዩ ኮረብታዎች ሱባኤ ገቡ።

ሱባኤ የገቡባቸው ከረብታዎችም፡-
👉የኦሪቱ ሊቀ ካህን አብኒ ኮረብታ
የሐዲሱ ሹም ሐዲስጌ ኮረብታ
👉የጳጳሱ አቡነ ሰላማ ሰላምጌ ኮረብታ
👉በንጉሥ አብርሃ አብርሂ ኮረብታ
👉በንጉሥ አጽብሃ ዜነዎ ኮረብታ ላይ እንደነበሩ ይነገራል

ንጉሥ አጽብሃም ከሁሉም አስቀድሞ ወደ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በመሄድ ያየውን ራዕይ ተናገረ። ሌሎችም መጥተው ያዩትን ሁሉ ተናገሩ አባ ሰላማም ይህንን ራዕይ ያዩ መኾናቸውን ነገሯቸው። ሁሉም በአንዲት ሌሊት አንድ ዓይነት ራዕይ አዩ።

ያዩት ራዕይም « ዐሥራ ሁለት በሮች ያላት አንድ አምደ ብርሃን የቤተ መቅደሱ መሠረት ከተጀመረበት ኮረብታ ተነስታ እያበራች የጥንቱ ቤተ ምኲራብ ከሚገኝበት ጽርሐ አርያም አምባላይ ስታርፍ » ነበር፡፡

ጧት ወደ ቦታው ሲሄዱ የጥንቱ አስደናቂው ቤተ ምኩራብ መሬት ውስጥ ተቀብሮ ለጥያለ አረንጓዴ ሜዳ ኾኖ አገኙት፡፡

ነገሥታቱ አብርሃ ወ አጽብሃ በቦታው ቤተ መቅደስን ይሠሩ ዘንድ ወደዱ። በወርቅ እና በእንቁ አምዶችን እና አረፍቶችን ልዩ አድርገው በማስጌጥ የማርያምን ቤተመቅደስ ሠሩ።

ሥርዓትንም በመደንገግ ካህናትን ዲያቆናትን እንዲሁም ሁሉንም ሊያሥተዳድር የሚችል ሊቀ ካህናት ርዕሰ ርዑሳን ብለው ሾሙ። መቅደሷንም መርጡለ ማርያም ብለው ሰየሟት።

ንጉሥ አብርሃ ወ አጽብሃም እግዚአብሔር በመራቸው መሠረት በጳጳሱ በአባ ሰላማ አስባርከው በጽርሐ አርያም አምባላይ አስደናቂውን ባለ ፲፪ (12) ቤተመቅደስ ባለ ፩ (1) ፎቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው በወርቅ በእንቁ በከበሩ ማዕድናት አስጊጠው ጥር ፳፩ (21) ቀን የእመቤታችንን ጽላት በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስገብተዋል።

ይህ ቤተ ክርስቲያን እጅግ የተለየ በልዩ ልዩ ቅርፅ ያጌጠ በወርቅ እና በእንቁ የተለበጠ አስደናቂ የጥበብ አሻራ ያረፈበት ነበር። ይህ ቤተ መቅደስ በዮዲት ጉዲት ዘመን በ፰፻፵፪ (842) ዓ.ም ተቃጥሏል።

በ፰፻፹፪ (882) ዓ.ም የነገሠው አንበሳ ውድም በዮዲት የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንደገና አሠርቶታል። ይህንን ቤተ ክርስቲያን ዐፄ በእደ ማርያም በ፲፬፻፷ (1460) ዓ.ም አሳድሶታል። ባለቤቱ ንግሥት እሌኒ ደግሞ የአንባውን ዙሪያ አሠርታለች። አሁንም የገዳሟ ዙሪያ የእሌኒ ውድሞ ይባላል።

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ፣ ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተሠራ ዘጋቢ ፕሮግራም እንደሚያስረዳው መርጡለ ማርያም በዋጋ የማይተመን ከፍተኛ የቅርስ ክምችት ያላት ገዳም ናት፡፡

እነዚህ ውድ ቅርሶች በመርጡለ ማርያም ሙዚየም ውስጥ የሚገኙ የአብርሃ ወአጽብሃ የወርቅ መስቀል፣ በ445 ዓ.ም የተጻፈ ግዕዙን በግዕዝ የሚተረጉም አርባዕቱ ወንጌል፣ የአጼ በእደ ማርያም ራስ ቁር እና የወርቅ ለምድ፣ የንግሥት እሌኒ የክብር ካባ እና የብር ዋንጫ፣ የብር እና የወርቅ መስቀሎች፣ የወርቅ አክሊሎች፣ የወርቅ ከበሮ፣ የአጼ ገላውዲዮስ ዳዊት እና ካባ፣ የብራና መጻሕፍት እና የመሳሰሉትን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ጥር 21 የሚከበረው በዓለ አስተርእዮ ማርያም የመርጡለ ማርያም ልዩ የክብረ በዓል ቀን ነው፡፡ አስተርእዮ ማርያም በመርጡለ ማርያም በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች የሚከበር ደማቅ በዓል ነው፡፡

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot

BY EOTC ቤተ መጻሕፍት


Share with your friend now:
tgoop.com/EotcLibilery/15581

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A Hong Kong protester with a petrol bomb. File photo: Dylan Hollingsworth/HKFP. Don’t publish new content at nighttime. Since not all users disable notifications for the night, you risk inadvertently disturbing them. “Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group. Joined by Telegram's representative in Brazil, Alan Campos, Perekopsky noted the platform was unable to cater to some of the TSE requests due to the company's operational setup. But Perekopsky added that these requests could be studied for future implementation. fire bomb molotov November 18 Dylan Hollingsworth yau ma tei
from us


Telegram EOTC ቤተ መጻሕፍት
FROM American