EOTCLIBILERY Telegram 15891
እነዚህ አጋጣሚዎች ለእኔ እጅግ አስተማሪዎች ነበሩ። እውነት ለመናገር ስለሌሎች ከመናገር በፊት እነዚያ አካላት የሚሉትን በትክክል ማወቅ በእጂጉ አስፈላጊ መሆኑንና ስለተለያዩ ብቻ እያነሡ መለጠፍ፣ እንደ ልብ መናገር በጣም አደገኛ መሆኑን የተማርሁት ይህን ከመሰሉ ስለእኛ ከተነገሩ እጂግ የተሳሳቱ ትምህርቶች ፣ ጽሑፎች እና አመለካከቶች ነው። ከዚያም ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ጽሑፎች ውስጥ ሳይቀር ይህን የመሰለውን ስለእኛ ያላቸውን የተሳሳተ እምነታቸውን ሳይ በእጂጉ አዝናለሁ፤ በዚያ ምክንያትም የሥራዎቻቸውን ደኅና ነገር ሁሉ በዚያው ዓይን እያየሁ እንድጠራጠራቸው እሆናለሁ።

ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።

ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot



tgoop.com/EotcLibilery/15891
Create:
Last Update:

እነዚህ አጋጣሚዎች ለእኔ እጅግ አስተማሪዎች ነበሩ። እውነት ለመናገር ስለሌሎች ከመናገር በፊት እነዚያ አካላት የሚሉትን በትክክል ማወቅ በእጂጉ አስፈላጊ መሆኑንና ስለተለያዩ ብቻ እያነሡ መለጠፍ፣ እንደ ልብ መናገር በጣም አደገኛ መሆኑን የተማርሁት ይህን ከመሰሉ ስለእኛ ከተነገሩ እጂግ የተሳሳቱ ትምህርቶች ፣ ጽሑፎች እና አመለካከቶች ነው። ከዚያም ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ጽሑፎች ውስጥ ሳይቀር ይህን የመሰለውን ስለእኛ ያላቸውን የተሳሳተ እምነታቸውን ሳይ በእጂጉ አዝናለሁ፤ በዚያ ምክንያትም የሥራዎቻቸውን ደኅና ነገር ሁሉ በዚያው ዓይን እያየሁ እንድጠራጠራቸው እሆናለሁ።

ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።

ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot

BY EOTC ቤተ መጻሕፍት


Share with your friend now:
tgoop.com/EotcLibilery/15891

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

bank east asia october 20 kowloon Concise ‘Ban’ on Telegram Add up to 50 administrators As five out of seven counts were serious, Hui sentenced Ng to six years and six months in jail.
from us


Telegram EOTC ቤተ መጻሕፍት
FROM American