Telegram Web
🔴 ተዓምረ ማርያም || አዲስ እጅግ ...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
ተአምረ ማርያም
             
Size:-120.6MB
Length:-2:10:16

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
🔴 ትዳር ክቡር ነው || አትፋቱ || ...
Enqo silassie
ትዳር ክቡር ነው አትፋቱ
             
Size:-64.2MB
Length:-1:09:17

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@Mezigebehayimanot
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጾመ ነነዌን አስመልክተው አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል !

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

ሰኞ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጀመረውን የፈጾመ ነነዌን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት  የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሙሉ መልእክቱ እንደሚከተለው ቀርቧል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባኤ፡-

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)።

ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤

•  የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !

እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን።

እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው።

በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን  እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ  ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን።

   “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ...
ማኅበረ ጽዮን
የጸናውን አስቡ
             
Size:-63.4MB
Length:-1:08:26

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
"ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ ፡-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ስምዖን አረጋዊ

#የካቲት_8  ፤ የጌታችን  ከከበርች ልደት በኋላ  ወደ ቤተመቅደስ የገባበት ዕለት ኾነ ፡፡ በዓሉ ከጌታችን ንዑስ በዓሎች መኻከል አንዱ ነው ፡፡
++++
የካቲት 8 ፤ ልደተ ስምዖን አረጋዊው  ፣ ካህን ፣ ጻድቅ ፣ ነቢይ ፡፡

+ በዓሉ የመድኀኔዓለም ቢሆንም ስምዖን አረጋዊ አማናዊ ድኅነት አግኝቶበታልና ፣  በእርጅና ምክንያት ከአልጋ ላይ ተጣብቆ ሲኖር ታድሶበታልና እንደ 30 ዓመት ጎልማሳም ዘሏልና  በዓሉ ይከብራል ። ስምዖን ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ሁሉ የድኅነት ባለቤት ኾኖበታልና በዓሉ ይከብራል ።

++++

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በተወለደ በ40 ቀኑ የኦሪትን ሕግ ለመፈጸም ወደ ቤተ መቅደስ ገባ ። ይህም ሕግን ሊፈጽም እንጂ ሊያፈርስ አለመምጣቱን በቃልም ፣ በግብርም የገለጠበት በዓል መኾኑን ያስረዳናል። ሥርዓቱን ለመፈጸም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ጌታቸውን ይዘው፣ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ ጨምረው ወደ ቤተ መቅደስ ሔዱ ።

++++

የስምዖን አረጋዊ ነገርም እንዲኽ ነው ..
ዓለም በተፈጠረ በ5,200 ዓመታት በጥሊሞስ የተባለ ንጉሥ በግሪክ ነግሦ ነበር። ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጦ፣ እንደ ገል ቀጥቅጦ የገዛው መሆኑን ገልጦ፣ የቀረው ነገር አለመኖሩን ሲናገር ባለሟሎቹ በእሥራኤል ጥበብ የመላባቸው 46 መጻሕፍት ስላሉ እነርሱን አላስተረጎምክም አሉት። እስራኤልን አስገብሮ ስለነበር 46ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ72 የአይሁድ ሊቃውንት ጋር አስመጣ። አይሁድ ተንኮለኛ መኾናቸውን ስለሚያውቅ 36 ድንኳን እንዲዘጋጅ አድርጎ ኹለት ኹለቱን መድቦ፣ የየድንኳኑን ሊቃውንት የሚቆጣጠሯቸው አንዳንድ ጠባቂዎች ጨምሮ  እንዲተረጕሙ አዘዛቸው።

በዚህ ምክንያት በ284 ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት 46ቱ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ወደ ልሳነ ጽርዕ (ግሪክ) በ70ው ሊቃናት ተተረጐሙ። ከ70 ሊቃናት በመኻከል አንዱ የነበረው #ስምዖን ምሁረ ኦሪት ነበር። ይተረጕም ዘንድ መጽሐፈ ኢሳይያስ ደረሰው። ታዲያ ይህ ሊቅ የትንቢቱን መጽሐፍ እየተረጎመ ሳለ ምዕራፍ ፯ ላይ ሲደርስ የሕይወቱን አቅጣጫ ወደ ዘላለማዊ በረከት የሚያሳድግ ልዩ ገጸ ንባብ ገጠመው ።  እርሱም
“ ስለዚኽ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነኾ ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” ኢሳ 7፥14 የሚል ነበር።
ስምዖንም "እንዴት ድንግል ትፀንሳለች?" ብሎ "ድንግል" የሚለውን "ሴት" ብሎ ቀይሮ " ሴት ትፀንሳለች " ብሎ ለማረም ይሞክርና አመሻሽ ላይ ስለነበር እንቅልፍ ሸለብ አድርጎት ሲነቃ የቀየረው ተቀይሮበት " ድንግል ትጸንሳለች" የሚል ሁኖ ያገኘዋል።  ተሳስቼ ነው ብሎ አሁንም ሊያበላሽ ሲሞክር መልአኩ ሦስት ጊዜ አርሞበት  በሦስተኛው መልአኩ ራሱ ተገልጦለት "ይህችን ድንግል ሳታይና ልጇንም ታቅፈህ ሳትባረክ አትሞትም"
( የተጠራጠርከውን ሳታይ አትሞትም ብሎ ብሎ ነግሮት )  ተሰወረ። አረጋዊ ስምዖንም ከዚያች ዕለት ጀምሮ መድኅን ክርስቶስ እስከሚወለድ ለ284 ዓመታት ከአልጋ ጋር ተጣብቆ ኖረ።
አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በተወለደ በ40 ቀኑ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ወጡ ። በዕለቱም መልአከ እግዚአብሔር አረጋዊ ስምዖንን ቀስቅሶ ተስፋ የሚያደርገው አዳኝ ክርስቶስ መምጣቱን ነገረው። በዚህ ጊዜ አረጋዊ ስምዖን አካሉ ታድሶ፣ እንደ 30 ዓመት ወጣት እምር ብሎ ከአልጋው ተነሣ። በፍጥነትም ወደ መቅደስ ገባ። መድኀኔዓለምን ከድንግል ማርያም ተቀብሎ በመታቀፍ "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ፡-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው"

(" ጌታ ሆይ፥ አን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤
ይኽም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ፳ኤል ክብር ነው።" (ሉቃ 2÷29-32)  )
በማለት ጸለየ። 

አምላኩም ጸሎቱን ሰምቶት በዛሬው ዕለት ዐረፈ። ከበዓሉ በረከት ይክፈለን። አሜን!!

የሊቁ ስምዖን  አረጋዊ በረከት እና ምልጃ አይለየን !
በዓለ ስምዖን በዐይቢይነት  ሜላት ደብረ ገነተ ኢየሱስ  ይከብራል  ፡፡
ጐንደር   -- › አንዳቤቴ ወረደ   -- › ገነተ ኢየሱስ  
በ13ኛ መቶ ክፍለ  ዘመን በአጼ ሰይፈ አርዕድ ዘመነ መንግስት
ልዕልት ሜላተ ወርቅ ያሰተከለችው ደብር ነው ፡፡
+++
በዓሉ በኢየሱስ ስም የተሰየሙ አድባራትና ገዳማት ላይ ይከበራል !

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
🔴 ጊዜ ለምን ? || ጾመ ነነዌ || ...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
ጊዜ ለምን? || ጾመ ነነዌ
             
Size:-82.9MB
Length:-1:29:33

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
፩ኛ፦ ጠንቅቀን በማናውቀው ጉዳይ ላይ መናጆ/አንጃ ሆነን አስተያየት አለመስጠት መልካም ነው።

፪ኛ፦ የዕውቀታችንን ምንጭ መመርመር መልካም ነው። ከልምድ ነው? ከመጽሐፍ ነው? ከመምህር ነው? ከመሰለኝ ነው? ከምንድን ነው?

፫ኛ፦ የሰውን አለማወቅ እንደ Advantage ተጠቅሞ ማታለል አይገባም። ለምሳሌ ማንኛውም ክርስቲያን ንስሓ ገብቶ ሥጋውን ደሙን መቀበል ይገባዋል። ወደ ገጠር ስንሄድ ግን ወጣት አይቆርብም እያሉ አንዳንድ ሰዎች ሲከለክሉ ይስተዋላል። ይህ ስሕተት ነው። አንዱ መምህር ሄዶ ንስሓ እየገባችሁ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ ቢል ሰው ከልምዱ ተነሥቶ ሊጠላው ይችላል። የተናገረው ግን እውነት ነው። ሌላ እወደድ ባይ መምህር አዎ ወጣት መቁረብ የለበትም ብሎ ሕዝቡ የሚያቀርባቸውን አመክንዮዎች ቢያቀርብ ሕዝቡ ደስ ሊለው ይችላል። ሕዝቡም የዚህ ደጋፊ ሊሆን ይችላል። መማር እንደዚህ ነው ሊልህ ይችላል። እውነታው ግን የላይኛው ነው። በዚህ ጊዜ ከሕዝቡ የሐሰት ፈጠራ ይልቅ እግዚአብሔራዊውን እውነት ተናግሮ ከመሸበት ማደር ይገባል።

፬ኛ፦ ፈሪሳዊነትን እናስወግድ። ፈሪሳውያን በእግዚአብሔር ቃል ላይ የራሳቸውን ወግ እየጨመሩ ያስተምሩ ነበር። ለወጋቸው መጽሐፋዊ ወይም ቅዱስ ትውፊታዊ የሆነ ማስረጃ የላቸውም። ግን ሕዝቡ ወጋቸውን እንደ ጽጽቅ እንዲያይላቸው ይጥሩ ነበር።

፭ኛ፦ ክፉ ነገሮችም፣ መልካም ነገሮችም በትውፊት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፉ ይችላሉ። እኛ ቅዱስ ትውፊትን መቀበል አለብን። ቅዱስ ትውፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ የሚቃረን ከሆነ ትውፊት ቢሆንም እንኳ ቅዱስ ትውፊት ስላልሆነ አንቀበለውም።

፮ኛ፦ እግዚአብሔር ልብን የሚመረምር ስለሆነ ከእያንዳንዱ ሐሳባችን፣ ንግግራችን፣ ተግባራችን ጀርባ ያለውን ጉዳይ መመርመር ይገባናል። ከፍቅር ተነሥተን ነው? ከጥላቻ ተነሥተን ነው? ለሃይማኖታችን ከማሰብ ነው? ከአንጃነት ነው? ከምቀኝነት ነው? ከቅንዐት ነው? እግዚአብሔርን ከመውደድ ነው? በጠቅላላው ልባችንን እንፈትሽ። በእያንዳንዱ ንግግራችን፣ በእያንዳንዱ ሐሳባችን፣ በእያንዳንዱ ተግባራችን በእግዚአብሔር ፊት እንመዘንበታለንና።

፯ኛ፦ አንዳንዱ ሊሳደብ፣ ክፉ ስም ሊሰጥ ይችላል። አንዳንዱ ደግሞ ሊዋሽ ይችላል። በዚህ ጊዜ ስድቡን ቸል ብሎ ጉዳዩ ላይ ማተኮር መልካም ነው። ታግሠው ሲቀበሉት የበረከት ምንጭ ነውና። (አንዳንዱ የማስረዳት አቅም ሲያጥረው ስድብን እንደ አማራጭ ሊጠቀም ይችላል። ስለዚህ የሰውየውን ድክመቱን መረዳትና ንቆ መተው መልካም ነው)።

፰ኛ፦ ንግግሮችን፣ ጽሑፎችን ከነዐውዳቸው ለመረዳት መጣር ይገባል።

፱ኛ. ሟች መሆናችንን ለአፍታም ቢሆን መዘንጋት የለብንም። መቼ እንደምንሞት ስለማናውቅ ከመሞታችን በፊት መሥራት አለብን ብለን ያሰብነውን ጉዳይ ለመፈጸም መትጋት ይገባናል።

፲ኛ፦ አጥፍተን ከነበረ ይቅርታ ማለትን እንልመድ። ትሑት ልቡናን ገንዘብ እናድርግ። ፈሪሀ እግዚአብሔርን እናስቀድም።

© በትረ ማርያም አበባው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ስለ ሃይማኖታዊ ውይይት አንዳንድ ነገሮች

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታዊ ክርክሮች በረከት እያሉ መጥተዋል። እነርሱን ተከትሎ ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ ባሉትም መካከል ውይይቶች አለፍ ሲልም መነቃቀፎች አንዳንድ ጊዜም ደግሞ በእወቀትም ይሁን ያለዕውቀት መጠላለፍ የሚመስሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታያል። በእንዲህ ያለው ጊዜ ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚሉ ድምፆችም ይሰማሉ። የምናደርገው ነገር በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ የሚባልበት መሆኑ ባይቀርም በእኔ እምነት በአግባቡ ከተጠቀምንበት እና ከተማርንበት ከሁሉም ልንጠቀም እና መንገዳችንን ትክክል የሆነልን እርሱኑ ልናጸና ፈንገጥ ያልነው ወይም የመንገድ ጠርዝ በመርገጥ የተንሸራተትን ካለንም ልንመለስ እና በመሐል መንገድ እንድንጓዝ ሊጠቅመን ይችላል። እጅግ በትንሹ ከሰማኋቸው ተነሥቼ አጠቃላይ መርሕ ተኮር ሁኔታዎች በዚህ ጽሑፍ ልጠቁምና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ በመከራከሪያ ነጥቦቹም ላይ ላክል እችላለሁ። ከዚህ በፊት “አድማሱ ጀንበሬ ሕይወቱ እና ትምህርቱ” የሚለው መጽሐፍ ሲታተም በመቅድምነት የወጣ አጭር ጽሑፍ ላይ ከንባቦቼ ከቀራረምኩት የተወሰኑ ሀሳቦችን ማጋራቴ ይታወቃል። እነዚያን ያላየ ቢያያቸው አንድ ነገር እንኳ የሚጠቅም ሊያገኝ ይችላል ብዬ አምናለሁ። እነዚያን ያነሣሁበት ምክንያት ግን እነዚህን ጉዳዮች የእነዚያ ቀጣይ አድርጋችሁ እንድትወስዷቸው ለማሳሰብ ያህል ነው።

በውይይትም ሆነ በክርክር ውስጥ ያለን አገልጋዮች ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡን ጉዳዮች መካከል

1) በራስ ማስተዋል አለመደገፍ

በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ከተጻፉት ታሪኮች፣ ምክሮች እና ትርጓሜዎች መካከል አንደኛው በራሳቸን መረዳት፣ ማስተዋል (reasoning) ላይ እንዳንደገፍ እና በዚህ ምክንያት ወደ ፈተና እናዳንገባ መጠበቅን የሚመለከት ነው። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን የወሰደበትን ሒደት ስንመለከተው በምንም ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመክንዮ ይሠራል ይሆናል ለማለት የሚቻል አይደለም። የአብርሃምና ሣራ እንዲሁም የዘካርያስ እና የኤልሳቤጥ በዕርጅና ልጅ መውለድ የሚያስተምረንም ይህንኑ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን እግዚአብሔር እርሱ ባወቀ ኤሳው ቀድሞ እንዳይወለድ እና ያዕቆብ ቀድሞ እንዲወለድ ማድረግ እየቻለ ከተወለደ በኋላ በኩርናውን እንዲወስድ ለምን አደረገ? ለእነ አብርሃም እና ለእነ ዘካርያስ ልጆችን ቀድሞ ለምን አልሰጣቸውም ብለን ብንጠይቅ ዋናው መልስ እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው ከተፈጥሮ ሕግ እና ከየትኛውም አመክንዮ ወይም የሰው የሕሊና መረዳት የሚያልፉ ነገሮችን የሚያደርግ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጽሐፍም “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” /ምሳ 3 ፡ 5/ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው።

በርግጥ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ ነው። ከመረዳታችን እና ከሎጂካችን ባሻገር እግዚአብሔር የሠራውንና የሚሠራውን ማመን። ጌታችን ከእመቤታችን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተጸነሰበት፣ የተወለደበት፣ የሞተበት፣ ድኅነታችን የፈጸመበት፣ የእመቤትችን በሁለንተና ንጽሕት መሆን እና የመሳሰሉትን ነገሮች መረዳት የሚቻለው ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን በወሰደበት መንገድ ብቻ ነው። ይህም ማለት ከሎጂክና ከአመክንዮ ተላልቅቆ እግዚአብሔር አምላክነቱን በየዘመኑ ትውልድ እግዚአብሔርነቱን የገለጸባቸውንና በአእምሮ ከመታሰብ፣ በሎጂክ ከመረዳት በላይ የሆኑትን በመቀበል ነው። ያዕቆብ ብኩርናን የወሰደበት መንገድ በእምነት የምንቀበለው ብቻ ነውና። እነዚህ ነገሮች የተፈጸሙት፣ እና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡበት ዋና ዓላማም የአካላዊ ቃል ሰው መሆን ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ አስቀድመው የተዘጋጁ መልሶች እንዲሆኑ ነው።

በራስ ማስተዋል ወይም በራስ የመረዳት ችሎታ ላይ መደገፍ ቢያንስ ሁለት ታላላቅ ፈተናዎችን ወደ እኛ ያመጣል። የመጀመሪያው ከእምነት መጉደል ነው። ይህ ደግሞ እንኳን በእኔ ቢጤዎች ይቅርና ጻድቁ ዘካርያስንም ፈትኖታል። ዘካርያስ ቅዱስ ገብርኤልን የተከራከረው ዕውቀት ወይም የተፈጥሮ ሕግ ገድቦት ነውና። ሰው ካረጀ ካፈጀ በኋላ አይወልድም የሚለው ዕውቀቱ ወይም የተፈጥሮ ሕጉ ስሕተት ሆኖ አልነበረም። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ግን ከእነዚህ የሚያልፍ ነበረ። ስለዚህ በመረዳት ወይንም በማስተዋላችን ላይ መደገፍ መጀመሪያ የሚያመጣው ፈተና እንኳን ሰዎች መላእክትም ቢናገሩን እንድንከራከር ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ትናንት ያከበርነው የልደተ ስምዖን ታሪክ የሚያስታውሰንም ይህንኑ ገጠመኝ ነው። ሴት እንጂ ድንግል አትወልድም የሚል ሀሳብ ይዞ ድንግል ትጸንሳለች የሚለውን የነቢዩን የኢሳይያስን ቃል ሴት ወደሚል ለመቀየር ሞክሮ ከእግዚአብሔር ይህን ሳያይ እንዳይሞት የተረዳው የእግዚአብሔር አሠራር ከሰው ማስተዋል እና መረዳት ባሻገር ስለሆነ ነው። በዚህች መንገድ መጓዝ የጀመረ ሰው አይሁድ ከመስቀል ውረድና እንመንብህ እንዳሉት በራስ መረዳት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጦ እግዚአብሔርን መፈተኑ የማይቀር ነው።

ሁለተኛው እና ከባዱ ፈተና ደግሞ ሌሎች ይህን መረዳት እንደማይችሉ በማሰብ የዲያብሎስ ረቂቅ ወጥመድ በሆነው የትዕቢት ወጥመድ ውስጥ መውደቅን ሊያስከትል ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጥፋቶችን አከታትሎ ያመጣብናል። ሰሎሞን “በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም” /ምሳ 16 ፡ 5/ ሲል እንደገለጸው ቅጣቱም ቀጥታ ከእግዚአብሔር ይሆናል። ለሰውየው ግን እያወቀ ወይንም እውቀቱ ትክክል ስለሆነ እንጂ እየታበየ እና እየተጎዳ እንደሆነ አይሰማውም። ለዚህም ነው “ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው” /ምሳ 16 ፡ 25/ ተብሎ የተጻፈው ። ስለዚህ ከሁለቱም ለመጠበቅ በራስ መረዳት ላይ አለመደገፍ ትልቁ መፍትሔ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እና ምክሮች ያረጋገጡልንም ይህንኑ ነው።

2) ከትዕቢት / ካለመሸነፍ መንፈስ መራቅ

የትዕቢት ነገር ከላይም የተጠቆመ ቢሆንም በዓለም ለተፈጠሩት ችግሮች ሁሉ መሠረቱ ትዕቢት ነው። በተለይ በሰው ፊት ተሸናፊ መባልን፣ አያውቅም መባልን መፍራት፣ ተሳስቷል መባልን መሸሽ ወደ ማስረዳት እና ራስን ነጻ ለማውጣት ሲባል ወደ ተለጠጠ ክርክር ይስባል፣ ከዚያም ወደ ባሰው ችግር ወይም ፈተና ሊያደርስ ይችላል። ስለዚህ ጥያቄዎች ሲፈጠሩ ቆም ብሎ ማድመጥ ፣ መጸለይ እና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጠኑ ሊቃውንትን ደጋግሞ መጠየቅ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል። ይልቁንም ልሳሳት እችላለሁ በሚል ትሑት ሰብእና ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚለምን ሰው እግዚአብሔር በፍጥነት ከዚህ ችግር እንደሚያወጣው የታመነ ነው።

3) የምንጮችን ዐውድ በአግባቡ ለመራዳት መጣር

ብዙ ጊዜ ወደ ክርክር ተይዘው የሚወጡት ምንጮች ወይም ማስረጃዎች በራሳቸው ምንም ችግር የለባቸውም። ሆኖም ከተነገሩበት ወይም ከተጻፉበት ዐውድ አውጥተን ከተመለከትናቸው ችግር ውስጥ ልንወድቅ እንችላለን። ለምሳሌ ያህል ጥንተ አብሶን በተመለከተ የሚነሣው ክርክር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል። የጥንት ሊቃውንት ጌታ ሥጋውን ከሰማይ ይዞ ወርዷል፣ በእመቤታችን አደረባት እንጂ ሥጋን ከእርሷ አልነሣም ለሚሉ የዚያ ዘመን መና/ፍቃን የተሰጡ መልሶች ያንኑ የበደለውን ሰው የአዳምን ሥጋ ነው የተዋሐደ ሲሉ ያንን የሳተውን፣ የወደቀውን፣ የጎሰቆለውን የእዳም ሥጋ እንደተዋሐደ ተከራክረው አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ አገላለጾች እመቤታችንን ጥንተ አብሶ አለባት ሊያስብሉ አይችሉም። (ይህን ጉዳይ
እንደ ሁኔታው ለብቻው ልመለስበት እችላለሁ) በጣም የተለያዩ ሀሳቦች ናቸው። እንዲህ ያለው ችግር ቀደም ብሎም የነበረ ችግር ነው። ስለዚህ አሁንም ለመርታት በሚፈልግ ልቡና ውስጥ ሆኖ ጥቅሶችን ከዐውዳቸው ነጥሎ አውጥቶ መጠቀም ችግርን ያባብስ እንደሆን እንጂ መፍትሔ ሊሆን አይችልምና ከዚህም መጠበቅ ተገቢ ነው።

4) ከመጠራጠር አለመጀመር

መና/ፍቃን ሀሳብ እና ጥያቄ ሲያነሱ የእነርሱን አመክንዮ እና ፍረጃ ሰምቶ ነባር ትምህርቶችን ወይም ምንጮቻችን ከመጠራጠር መጀመር በጣም አደገኛ ነገር ነው። ለምሳሌ ሳጥናኤል እኔ ፈጠርኳችሁ ባለ ጊዜ በጥርጥር የጀመሩት እውነት በተገለጠ ጊዜ ከእርሱ ጋር አብረው ወድቀው የሚያስቱ መናፍስት ሆኑ እንጂ ሲመለሱ አላየናቸውም። እውነቱን ባያውቁም በያለንበት እንቁም ባለው በቅዱስ ገብር ኤል ቃል ጥርጥሩን ሳያስገቡ የጸኑት ግ ን በኋላ እግዚአብሔር እውነቱን ገልጾላቸዋል። ይህ የመጀመሪያው የፍጥረት ፈተና የሚያስረዳን ከመጠራጠር መጀመር ምን ያህል አደገኛ መሆኑን ብቻ ሳይሆን መንገዱ ዲያብሎሳዊ መሆኑን ነው። በሳይንስ ከመጠራጠር መጀመር ወደ ዕውቀት ይወስዳል ከሚባለው በተቃራኒ በሃይማኖት በመጠራጠር አለመጀመር መሠረታዊ ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን ማለት ነው።

በዚሁ መንገድ ካየን አንዳንድ የግእዝ ምንጮቻችን ከሌላ ሀገር ምንጮች ስናነጻጽር በቀጥታ ላይገጥሙልን ይችላሉ። ለምሳሌ ያህል ገድለ ጊዮርጊስን ስንመለከት ሰማዕቱን ያሰቃየውን ንጉሥ ዱድያኖስ ይለዋል። በሌላው ሀገር ግን ያሉት ምንጮች በሙሉ ደግሞ ንጉሡን ዲዮቅልጥያኖስ ይሉታል። ይህ በመሆኑ የእኛ ምንጭ ስሐተት ነው ልንል አንችልም። እኔ እንኳ በአቅሜ በአደረግሁት ፍለጋ አንድ ጥናት ላይ የጥንት ምንጮች ዱድያኖስ ይሉ እንደነበር አግኝቻለሁ። ስለዚህ ይህ ስም ምንጫችን ስሐተት መሆኑን ሳይሆን ምንጫችንን ወይም አቀባይ ቋንቋችንን እንድንመረምር እና የእኛ ቅጂ ከቀዳማውያን ምንጮች መሆኑን ይጠቁማል እንጂ ልዩ መሆኑ ስሕተት መሆኑን ሊያሳይ አይችልም ማለት ነው።

በገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ያለው የሞቱበትን በሽታ እንደመስቀሌ እቆጥርልሃለሁ የሚለውን ሀሳብ ስሑታኑ ባነሡበት መንገድ ተመልክቶ ከመጠራጠር ከመጀመር ወደ ገድሉ ጠልቆ ገብቶ ምክንያቱን ከማጥናት መጀመር ከብዙ በሽታ ይፈውሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ገድሉን ስንመለከት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ትልቁ ፍላጎታቸው የደም ሰማዕትነትን ማግኘት ነበር። ዘመኑ ደግሞ ያንን አልፈቀደላቸውም። ስለዚህ ጌታ በበሽታ የገጠማቸውን ተጋድሎ እንደ ሰማዕትነት ወይም መስቀል እንደሚቆጥርላቸው ቃልኪዳን ገባላቸው ይላል እንጂ መና/ፍቃኑ የሚሉትን ወይም ሊሉ የሚፈልጉትን ገድሉ በፍጹም አይልም።

በገድለ ቅዱሳንና በገድለ ቅዱሳን መጽሐፍ መካከል ልዩነት እንኳ ቢኖር ወደ ቀዳማይ ምንጭ በሚደረግ ጥናት ይስተካከላል እንጂ ገድለ ቅዱሳንን ወደ መጠራጠር ሊወስድ አይችልም። በርግጥ የሰው አእምሮ ውሱን ስለሆነ ለእንዲህ ያለ ፈተና ተደጋግሞ ሊወድቅ ይችላል። እንዲህ ያሉትን ነገሮች ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስም ያስረዳል። ለምሳሌ ያህል በሰማርያ እጅ ከባድ ረሀብ ተነሥቶ ሁለት ሴቶች ልጆቻቸውን ቀቅለው ለመብላት ከተስማሙና የአንዲቱን ከበሉ በኋላ ሁለተኛ ልጇን ስትደብቅ በተፈጠረው ክርክር ንጉሡ ስሞቶ በኤልሣዕ ላይ ተቆጥቶ ነበር። በኋላ ላይ ግን “የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነገ በዚህ ጊዜ በሰማርያ በር አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ይሸመታል አለ። ንጉሡም በእጁ ተደግፎ የነበረ አለቃ ለእግዚአብሔር ሰው መልሶ፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በሰማይ መስኮቶች ቢያደርግ ይህ ነገር ይሆናልን? አለው። እርሱም፦ እነሆ፥ በዓይኖችህ ታየዋለህ፥ ከዚያም አትቀምስም አለ” /2ኛ ነገ 7/ ተብሎ እንደተጻፈ ንጉሡ በመጠራጠሩ ምክንያት በሕይወቱ እንዲቀጣ ሆኗል። ስለዚህ ከመጠራጠር መጀመር ውጤቱ አደገኛ መሆኑን መረዳት እና በእምነት ጸንቶ የማያውቁትን ለማውቅ መጣር ተገቢነት ይኖረዋል ማለት ነው። ለዛሬው በእነዚሁ ልፈጸም። ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን

©ዲያቆን ብርሀኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
🔴 እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል ? |...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?
             
Size:-82.9MB
Length:-1:38:35

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@kendilebirihan
@kendilebirihan
@kendilebirihan
Channel photo updated
የ የካቲት 16 የኪዳነ ምረት ስርዓተ ማህለት እነሆ
2025/03/12 18:21:19
Back to Top
HTML Embed Code: