🛑 || ብቻችንን አንችልም || እጅግ...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
✝ብቻችንን አንችልም✝
Size:-59.4MB
Length:-1:04:12
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Size:-59.4MB
Length:-1:04:12
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
#እመቤታችን_ጥንተ_አብሶ_ከሌለባት_ለምን_ሞተች?
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኩሉ"
"ሞት ለሟች ይገባል
የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል!!!" ፤ ደራሲ፡፡
ሞት በአዳም በደል ምክንያት የመጣ ዕዳ ነው፤ባህርያዊ ሳይሆን ባህርያዊ መስሎ ከባህርያችን ጋር ተስማምቶ የሚኖር ፍዳ ነበር፡፡ ሞት ጌታችን ሳይገድለው/ሳይሽረው በፊት ወደ ሲኦል መውረጃ መንገድ ነበር፤
ለአጋንንት እግር እርግጫ፤ ለመንጸፈ ደይን ተመቻቻተን የምንሰጥበት ሂደት፤ሥጋ በመቃብር የሚፈርስበት፤ነፍስ በሲኦል የምትሰቃይበት ክስተት ነበር፡፡
👉ክርስቶስ ሲመጣ ግን ይህ ሞት የሚለው ንባብ ሳይቀየር ትርጉሙና ምሥጢሩ ተቀየረ፤መጠጫው ጽዋው ሳይቀየር መጠጡን እንደመቀየር ነው፤መሞት በሐዲስ ኪዳን መሻገር ነው፤ወደ ዘለዓለም ሕይወት መጠራት፤መቃብርም ለትንሣኤ ዘጉባኤ መቆያ ስፍራ ነው፡፡
👉እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለምን ሞተች? ሞት የጥንተ አብሶ ውጤት ከሆነ እመቤታችንም የሞተችው ጥንተ አብሶ ስላለባት ነው ብለው የሚከራከሩ ወገኖች አሉ፤
አነዚህ ሰዎች በሐዲስ ኪዳን ሞት ምን እንደሆነ ያለመረዳታቸውና እንዲሁም የእመቤታችን ሞት ምክንያቱ ምንድነው የሚለውን ባለማወቃቸው ምክንያት የሚናገሩት ነው፡፡
ሞት ጥንተ አብሶ ያለበት ብቻ ነው የሚሞተው ከተባለ ጌታችን ራሱ መሞቱ ጥንተ አብሶ ስላለበት ነው ያሰኛል፤ ይህ ደግሞ እርሱ ንጹሕ ሆኖ ሳለ ስለእኛ ሞተ የምንለውን የድኅነት ፅንሰ ሀሳብ ከንቱ ያደርግብናል፤ስለዚህ ሞት ከክርስቶስ በኋላ የመብቀል ሂደታችን መሆኑን እንመርምር፡፡
ይህን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይነግረናል:—
"አንተ ሞኝ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም"፤ይላል 1ኛ ቆሮ 15፡36፡፡
ሰለዚህ ሞት በሐዲስ ኪዳን ሕያው ለመሆን የምናልፍበት ሂደት (process) ነው፡፡
ራሱ ጌታችንም ሲያስተምረን:—
"እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው፤ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም"፤ዮሐ 5፡24፡፡
ዳግመኛም ፦ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘለዓለም ሞትን አያይም" ብሏል፤ዮሐ 8፡51፡፡
ይህም ማለት ነፍስ ከሥጋ አትለይም ማለት አይደለም፤እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ነፍስ በገነት እንደምትኖር፤ ከዚያም በትንሣኤ ዘጉባኤ ጊዜ ነፍሳችን ከሥጋችን ጋር ተዋሕዳ ተነሥተን ከመላእክት ጋር እያመሰገንን የምንኖረውን ዘላለማዊ ሕይወት ለመግለጽ እንጂ፡፡
👉እመቤታችን ቃሉን በመስማትና በማመን በመጠበቅ የመጀመሪያዋና ተወዳዳሪም የሌላት ናት፤ ማንም ሊሰማው የማይችለውን "ቃል ሥጋ ኮነ" ን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማች መስማት ብቻ ሳይሆን ያመነች ናት፤ቅድስት ኤልሳቤጥ "ወብፅዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ከመ ይከውን ቃል ዘነገሩኪ እምኀበ እግዚአብሔር ፤
(ከእግዚአብሔር የተነገረሽ ቃል እንደሚፈጸም ያመንሽ አንቺ ብፅዕት ነሽ) ብላ እንዳመሰገነቻት (ሉቃ 1፡45) "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብላ ስታምን ነበር ሞትን ያለፈችው፤ትንሣኤ ልቡናን ቀድማ የተነሣችው፤ ይህ ምሥጢር የተከናወነባት ናት፤እያንዳንዱን የጌታን ቃል በልብዋ ትጠብቀውና ታስበው እንደነበር ተጽፏል፤ሉቃ 2፡51፡፡
እንዲህ ከሆነ ሕይወት የሆነውን ጌታ ፀንሳ፤ወልዳ የድንግልና ጡት ያጠባች ሆና እንዴት ትሞታለች?
ሕይወትን የዳሰሱ እጆች፤ሕይወትን የተመለከቱ ዓይኖች፤ሕይወትን ያቀፉ ጉልበቶች እንዴት ለሞት ይሰጣሉ? ብለን ስንጠይቅ የሚከተሉት ምላሾች ይኖሩናል፡፡
➊ ከተገፋችበት ፤ከተንከራተተችበትና የኀዘንና የመከራ ሰይፍን ካስታናገደችበት ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ወደመንግሥተ ሰማያት መጠራቷን፤የማያልፈውን ዋጋ እንደተቀበለች ለማሳየት እንጂ የሞት ሞት የሚባለውን መፍረስና መበስበስን፤ወደ ሲኦል መውረድን የሚያሳይ እንዳልሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል።
ይህንንም ቅዱስ ያሬድ "ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ ፈለሰት እምዘ ይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤ዳዊት አቡሃ በመሰንቆሁ እንዘ የኀሊ፤የሰው እጅ ያልሰራት ድንኳን ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረላት እመቤታችን አባቷ ዳዊት በመሰንቆው እያመሰገናት ከሚያረጀው ዓለም ወደማያረጀው/ወደማያልፈው ሄደች"
በማለት እነደነገረን ነው፡፡
➋ ከሰማይ የወረደች (ኃይል አርያማዊት) ናት የሚሉ አሉና ሰው እንደሆነች እና ከምድር እንደተገኘች፤ሙሉ የሰውነት ማንነት ያላት መሆኑን ለማጠየቅ ነው፤ እመቤታችንን ሞት ባያገኛት ካልዕ ፍጥረት (ልዩ ፍጥረት) ስለሆነች ነው ብለው ብዙዎች በተከራከሩ ነበር፤ይህም ደግሞ ክርስቶስ የነሣውን ሥጋና ነፍስ (ምሥጢረ ተዋሕዶን) ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይከተው ነበርና በዚህ ምክንያት በሕገ ሰብእ በሩካቤ ብእሲ ወብእሲት ስለተገኘች በሕገ ሰብእ ሞት ተጠርታለች፤ ይህ ሞቷ እሷን ሌላ ፍጥረት የጌታን ተዋሕዶ ምትሐት ከማለት የሚታደግ መድኃኒትም ጭምር ነው፡፡
➌ ፍትሑ ርቱዕ (ፍርዱ ቅን የሆነ) እግዚአብሔር ለማንም እንደማያዳላ ያጠይቃል፤ እመቤታችን እንደማንኛውም ሰው ሞትን ባታይና ባትቀምስ ፍርዱ ትክክል አይደለም፤ አንዱን በሞት ይወስዳል ሌላውን ይተዋል፤ወዲህም ልጅዋ አምላክ ነውና ሞትን ያልቀመሰችው በልጅዋ ምክንያት እንጂ እርሷ የተለየ ቅድስና ስላላት አይደለም በተባለ ነበርና ሞትን እንድትቀምስ ፈቅዷል፤ሞትን መቅመሷ በክብር ላይ ክብር ቢጨምርላት እንጂ ቅንጣት ታህል ክብር አይቀንስባትምና፡፡
ይህንንም ደራሲው፦
"ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ክርስቶስ ሥጋውን ለነሳበት አካል በሞት አላዳላም" በማለት ተናግሯል፡፡
ቅዱስ ያሬድም ፦
"እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ከመ ኢያደሉ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኩሉ
አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ"
(በፍርድ እንደማያዳላ ስለዚህ ነገር ዕወቁ፤የእርሱ እናት፤የሁሉ እናት እመቤታችን ሞትን ትቀምስ ዘንድ ወልድ በማይሻር ቃሉ አዘዘ) በማለት አስረግጦ ተናግሯል። (ቅዱስ.ያሬድ)፡፡
👉መልኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ
ቅድስት ኤልሳቤጥ ከምድር በተባበረ ቃል እንዲህ ብለዋል👇
"ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ"
ሉቃ 1፥28 ፤ ሉቃ 1፥42
👉የተባረክሽ ማለት መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ ማለት ነው!
በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እያማለደች የምታሰጥ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ምድራችንን በበረከት ትጎብኝልን!!!!!
መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኩሉ"
"ሞት ለሟች ይገባል
የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል!!!" ፤ ደራሲ፡፡
ሞት በአዳም በደል ምክንያት የመጣ ዕዳ ነው፤ባህርያዊ ሳይሆን ባህርያዊ መስሎ ከባህርያችን ጋር ተስማምቶ የሚኖር ፍዳ ነበር፡፡ ሞት ጌታችን ሳይገድለው/ሳይሽረው በፊት ወደ ሲኦል መውረጃ መንገድ ነበር፤
ለአጋንንት እግር እርግጫ፤ ለመንጸፈ ደይን ተመቻቻተን የምንሰጥበት ሂደት፤ሥጋ በመቃብር የሚፈርስበት፤ነፍስ በሲኦል የምትሰቃይበት ክስተት ነበር፡፡
👉ክርስቶስ ሲመጣ ግን ይህ ሞት የሚለው ንባብ ሳይቀየር ትርጉሙና ምሥጢሩ ተቀየረ፤መጠጫው ጽዋው ሳይቀየር መጠጡን እንደመቀየር ነው፤መሞት በሐዲስ ኪዳን መሻገር ነው፤ወደ ዘለዓለም ሕይወት መጠራት፤መቃብርም ለትንሣኤ ዘጉባኤ መቆያ ስፍራ ነው፡፡
👉እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለምን ሞተች? ሞት የጥንተ አብሶ ውጤት ከሆነ እመቤታችንም የሞተችው ጥንተ አብሶ ስላለባት ነው ብለው የሚከራከሩ ወገኖች አሉ፤
አነዚህ ሰዎች በሐዲስ ኪዳን ሞት ምን እንደሆነ ያለመረዳታቸውና እንዲሁም የእመቤታችን ሞት ምክንያቱ ምንድነው የሚለውን ባለማወቃቸው ምክንያት የሚናገሩት ነው፡፡
ሞት ጥንተ አብሶ ያለበት ብቻ ነው የሚሞተው ከተባለ ጌታችን ራሱ መሞቱ ጥንተ አብሶ ስላለበት ነው ያሰኛል፤ ይህ ደግሞ እርሱ ንጹሕ ሆኖ ሳለ ስለእኛ ሞተ የምንለውን የድኅነት ፅንሰ ሀሳብ ከንቱ ያደርግብናል፤ስለዚህ ሞት ከክርስቶስ በኋላ የመብቀል ሂደታችን መሆኑን እንመርምር፡፡
ይህን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይነግረናል:—
"አንተ ሞኝ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም"፤ይላል 1ኛ ቆሮ 15፡36፡፡
ሰለዚህ ሞት በሐዲስ ኪዳን ሕያው ለመሆን የምናልፍበት ሂደት (process) ነው፡፡
ራሱ ጌታችንም ሲያስተምረን:—
"እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው፤ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም"፤ዮሐ 5፡24፡፡
ዳግመኛም ፦ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘለዓለም ሞትን አያይም" ብሏል፤ዮሐ 8፡51፡፡
ይህም ማለት ነፍስ ከሥጋ አትለይም ማለት አይደለም፤እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ነፍስ በገነት እንደምትኖር፤ ከዚያም በትንሣኤ ዘጉባኤ ጊዜ ነፍሳችን ከሥጋችን ጋር ተዋሕዳ ተነሥተን ከመላእክት ጋር እያመሰገንን የምንኖረውን ዘላለማዊ ሕይወት ለመግለጽ እንጂ፡፡
👉እመቤታችን ቃሉን በመስማትና በማመን በመጠበቅ የመጀመሪያዋና ተወዳዳሪም የሌላት ናት፤ ማንም ሊሰማው የማይችለውን "ቃል ሥጋ ኮነ" ን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማች መስማት ብቻ ሳይሆን ያመነች ናት፤ቅድስት ኤልሳቤጥ "ወብፅዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ከመ ይከውን ቃል ዘነገሩኪ እምኀበ እግዚአብሔር ፤
(ከእግዚአብሔር የተነገረሽ ቃል እንደሚፈጸም ያመንሽ አንቺ ብፅዕት ነሽ) ብላ እንዳመሰገነቻት (ሉቃ 1፡45) "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብላ ስታምን ነበር ሞትን ያለፈችው፤ትንሣኤ ልቡናን ቀድማ የተነሣችው፤ ይህ ምሥጢር የተከናወነባት ናት፤እያንዳንዱን የጌታን ቃል በልብዋ ትጠብቀውና ታስበው እንደነበር ተጽፏል፤ሉቃ 2፡51፡፡
እንዲህ ከሆነ ሕይወት የሆነውን ጌታ ፀንሳ፤ወልዳ የድንግልና ጡት ያጠባች ሆና እንዴት ትሞታለች?
ሕይወትን የዳሰሱ እጆች፤ሕይወትን የተመለከቱ ዓይኖች፤ሕይወትን ያቀፉ ጉልበቶች እንዴት ለሞት ይሰጣሉ? ብለን ስንጠይቅ የሚከተሉት ምላሾች ይኖሩናል፡፡
➊ ከተገፋችበት ፤ከተንከራተተችበትና የኀዘንና የመከራ ሰይፍን ካስታናገደችበት ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ወደመንግሥተ ሰማያት መጠራቷን፤የማያልፈውን ዋጋ እንደተቀበለች ለማሳየት እንጂ የሞት ሞት የሚባለውን መፍረስና መበስበስን፤ወደ ሲኦል መውረድን የሚያሳይ እንዳልሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል።
ይህንንም ቅዱስ ያሬድ "ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ ፈለሰት እምዘ ይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤ዳዊት አቡሃ በመሰንቆሁ እንዘ የኀሊ፤የሰው እጅ ያልሰራት ድንኳን ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረላት እመቤታችን አባቷ ዳዊት በመሰንቆው እያመሰገናት ከሚያረጀው ዓለም ወደማያረጀው/ወደማያልፈው ሄደች"
በማለት እነደነገረን ነው፡፡
➋ ከሰማይ የወረደች (ኃይል አርያማዊት) ናት የሚሉ አሉና ሰው እንደሆነች እና ከምድር እንደተገኘች፤ሙሉ የሰውነት ማንነት ያላት መሆኑን ለማጠየቅ ነው፤ እመቤታችንን ሞት ባያገኛት ካልዕ ፍጥረት (ልዩ ፍጥረት) ስለሆነች ነው ብለው ብዙዎች በተከራከሩ ነበር፤ይህም ደግሞ ክርስቶስ የነሣውን ሥጋና ነፍስ (ምሥጢረ ተዋሕዶን) ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይከተው ነበርና በዚህ ምክንያት በሕገ ሰብእ በሩካቤ ብእሲ ወብእሲት ስለተገኘች በሕገ ሰብእ ሞት ተጠርታለች፤ ይህ ሞቷ እሷን ሌላ ፍጥረት የጌታን ተዋሕዶ ምትሐት ከማለት የሚታደግ መድኃኒትም ጭምር ነው፡፡
➌ ፍትሑ ርቱዕ (ፍርዱ ቅን የሆነ) እግዚአብሔር ለማንም እንደማያዳላ ያጠይቃል፤ እመቤታችን እንደማንኛውም ሰው ሞትን ባታይና ባትቀምስ ፍርዱ ትክክል አይደለም፤ አንዱን በሞት ይወስዳል ሌላውን ይተዋል፤ወዲህም ልጅዋ አምላክ ነውና ሞትን ያልቀመሰችው በልጅዋ ምክንያት እንጂ እርሷ የተለየ ቅድስና ስላላት አይደለም በተባለ ነበርና ሞትን እንድትቀምስ ፈቅዷል፤ሞትን መቅመሷ በክብር ላይ ክብር ቢጨምርላት እንጂ ቅንጣት ታህል ክብር አይቀንስባትምና፡፡
ይህንንም ደራሲው፦
"ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ክርስቶስ ሥጋውን ለነሳበት አካል በሞት አላዳላም" በማለት ተናግሯል፡፡
ቅዱስ ያሬድም ፦
"እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ከመ ኢያደሉ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኩሉ
አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ"
(በፍርድ እንደማያዳላ ስለዚህ ነገር ዕወቁ፤የእርሱ እናት፤የሁሉ እናት እመቤታችን ሞትን ትቀምስ ዘንድ ወልድ በማይሻር ቃሉ አዘዘ) በማለት አስረግጦ ተናግሯል። (ቅዱስ.ያሬድ)፡፡
👉መልኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ
ቅድስት ኤልሳቤጥ ከምድር በተባበረ ቃል እንዲህ ብለዋል👇
"ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ"
ሉቃ 1፥28 ፤ ሉቃ 1፥42
👉የተባረክሽ ማለት መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ ማለት ነው!
በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እያማለደች የምታሰጥ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ምድራችንን በበረከት ትጎብኝልን!!!!!
መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ከዚህም ብዙ ቁምነሮችን የምናገኝ ይመስለኛል። ይኸኛው እንደ ቅዱስ ቄርሎስ ሳይጠነቀቅ እዚያው ፊት ለፊት ካህኑን ገጥሞታል። መልአኩ ደግሞ ምን ያህል ጊዜ እንደታገሰው እና እንደጠበቀ እናስተውል። መልአኩ እንዳለው ሰዎች ከስሐተታቸው በሌሎች ሰዎች ሲታረሙ ማየት እግዚአብሔርንም መላእክትንም የሚያስደስት መሆኑ አስገራሚ ነው። ያም በመሆኑ ደግሞ እግዚአብሔር ለመጀመሪያው አባት ቅዱስ ቄርሎስን ለዚህ ካህን ደግሞ አዋቂ ዲያቆን አዘጋጀ። ስሕተት ደግሞ የማትገባበት ጊዜ እና ቦታም እንደሌለ የምትምረውም የሰው ዓይነት እንደሌለ ከታሪኮቹ መረዳት ይቻላል። ከዚህ ታሪክ ሌሎች ብዙ ነጥቦችንም መውሰድ እንችላለን። እንደላይኛው ሁሉ መልአክ ተገልጾለት የሚነጋገር አባት ሳይቀር ሊስት የኑፋ/ቄ ቃላትንም ሊጠቀም መቻሉ እንደተጠበቀ ሆኖ ነገረ ግን ሰውየው ውስጡ እምነቱና ሀሳቡ ኑፋቄና ተንኮል ከሌለው እግዚአብሔርም ይታገሰዋል። ቀኑንም ጠብቆ የሚያርመውንና የሚያስተምረውን ሰው ይልክለታል። ከሁሉም በላይ ደግሞ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኘው በሌላ ሰው ስንስተካከል ነው። ለዚህ አባት የተላከለትም ከእርሱ በላይ የበቃ አባት ሳይሆን ከእርሱ በሥልጣነ ክህነትም የሚያንስ ዲያቆን ነው። ዲያቆኑን ተጠራጥሮ አልቀበለም ሲል ደግሞ መልአኩ ተገልጾ ማረጋገጫ የሰጠው ከእኛ ያንሳሉ ብለን ከምናስባቸው ሰዎችም ቢሆን ሰምተን እንድንታረምና እንድንሰተካከል ጭምር ነው።
በሰው መታረምን በተመለከተ ደግሞ ሌላ ታሪክ ልጨምር። ቃለ እግዚአብሔርን ከምጠያየቃቸው እና ከምጫወታቸው አንዱ የሆነው መምህር በረከት አዝመራው ካነበበው የትርጓሜ መጽሐፍ የነገረኝ ነው። ሙሴ ደብረ ሲና ወጥቶ ሲመለስ እሥራኤል ጣዖት አቁመው ሲሰግዱ አግኝቷቸው እነዚያን ጣዖት የሚያመልኩትን እንዲገደሉ አዝዞ በወገኖቻቸው ተገድለዋል። እርሱ እንደነገረኝ መተርጉማኑ አንድ ጥያቄ አንሥተው ይመልሳሉ። እግዚአብሔር እነዚያን ጣዖት አምላኪዎች እንደ ፈርዖን ለምን ራሱ አላጥፋቸውም ወይም ለምን ራሱ አልቀሰፋቸውም? በሙሴ ትዕዛዝ በራሳቸው ወገኖች እንዲገደሉ ለምን አደረገ የሚል ጥያቄ ያነሡና ይመልሳሉ።
እግዚአብሔር ራሱ ሳያጠፋቸው በራሳቸው ወገኖች እንዲገደሉ ያደረገው ስለሁለት ምክንያት ነው። የመጀመሪያው እሥራኤል ታሪካቸው እግዚአብሔርን ክዶ ጣዖት ማምለክ ብቻ ሳይሆን ጣዖት አምላኪዎችንም የማጥፍት ታሪክ እንዳላቸው እንድናውቅ ነው። ሁለተኛም ከላይ እንዳልነው የሰው ስሐተት በሰው ሲታረም እግዚአብሔር ደስ ስለሚለው ነው የሚል ነው። ከላይ ባየነው ታሪክ መልአኩም ያለው ይህንኑ ነው።
ከዚህም ጋር በሁለቱም አባቶች ታሪክ ላይ አንድ ሌላ መሠራታዊ ትምህርት እናገኛለን። ይኸውም ሰዎች በሚሳሳቱ ጊዜ በሁለንተናቸው ኦርቶዶክሳዊ ሆነው የሆነ ኑፋቄያዊ ቃላት እና ሀሳብ ባገኘንባቸው ጊዜ መማማሩ እንዳለ ሆኖ ልናደርገው የሚገባን ጥንቃቄ ፣ ከበሬታ ፣ ልናሳያቸው የሚገባው ፍቅር ተገልጾልናል። ያን አባት ያረመው ያ ዲያቆን በእኛ ዘመን ቢሆን ኖሮ እንኳን በዚያ አባት በመልአኩም ሊናደድ የሚችል ይመስለኛል። ለምን ሳይቀስፈው ብሎም መልአኩንም የሀሳቡ ተባባሪ አድርጎ ሊቆጥረው ይችላል። (ይህን የምለው ስለእኛ ሕሊና መሆኑ ሳይረሳ) ምክንያቱም የእኛ ዘመን አንዱ ትልቁ ድክመታችን የመጨረሻ ፍርድ ሁሉ ሰጭዎች መሆናችን ነውና።
ማጠቃለያ
እንዲህ ያሉ ነገሮች ለምን ተነሡ? ምን ሲል እንዲህ ተባለ? ለምን እነእገሌ እንዲህ ይላሉ? ... ለምን ዝም ይባላል? የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ማቆም ይኖርብናል። በየትኛውም ዘመን በየትኛውም መዓርግ ባለ መንፈሳዊ ሰውም ላይ ብዙ የምናውቃቸውም የማናውቃቸውም ስሐተቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ መረዳት ተገቢ ነው። እባብ ያዬ በልጥ በረዬ የሚባልላቸው መሆንም የለብንም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነት ታሪኮች ሁልጊዜም ማስተማሪዎች በመሆን አንዱ የእግዚአብሔር የመግቦት መገለጫዎች፣ የየዘመኑን ሰው ማንቂያዎች፣ ወዳጆቹንም መጠበቂያዎች (በተለይ ከትዕቢትና ኩነኔ ከሚያመጣ ጥፋት) ናቸው። ዋናው የሚያስፈልገን ነገር ከሁሉም ነገር እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው፣ እኛ ውስጥ ሊያርመው የፈለገው ነገር ምንድን ነው የሚለው ጥያቄ መሆን አለበት ። ካስተዋልን ሁላችንም የየራሳችንን ስሐተቶች የማየት እና የመታረም ዕድል እናገኝበታለን።
ማር ይስሐቅ መላእክትን ለማየት ከበቃ ሰው ይልቅ የራሱን ስሕተት ለማየት የበቃ ሰው የበለጠ ብቃት ደረጃ ላይ ደርሷል ይላል። ቅዱሱ አባት መላእክትን የሚያይ የውጭ ዐይኑ የተከፈተለት ነው፣ የራሱን ስሕተት የሚያይ ግን የውስጥ ዓይኑ የተከፈተለት ነውና እርሱ የበለጠ በቅቷል እንዳለ ወደ ሰው ስሕተት ከማየት ይልቅ ወደራሳችን ስሐተት ማየት ኦርቶዶክሳዊም መንፈሳዊም መንገድ መሆኑን እናስተውል። በዚህ ጽሑፍ ላነሣቸው ያልፈልኳቸው ብዙ ድክመቶች እንዳሉብን ይሰማኛል። ለሁላችንም የሚጠቅመን ግን የራሳችን ስሐተት ማየት እንጂ የሌሎቹ ላይ ማፍጠጥ እና ከፍ ዝቅ አድርጎ መናገርም ሆነ መጻፍ አይደለምና አጥብቀን እንታረም። ይልቁንም ያለነው በዐቢይ ጾም ዋዜማ ላይ ስለሆነ በቀሩን ቀናት ይቅርታ ተጠያይቀን ከቡድነኝነት፣ ከተሳሳቱ ግምቶች እና ግምታዊ ንግግሮች፣ ከፍረጃ እና ከአጸፋዊ ፍረጃ፣ በማናውቀው እና በማይገባን ነገር ከመነጋገር ወጥተን ወደ መንፈሳዊ ድንኳናችን እንሰብሰብ። ያን ጊዜ ስሕተቶቻቸን ይታዩናል። ለሰዎችም ፍቅር ሐዘኔታ የተመላ የማስተካከያ መንገድ ይገለጽልናል። እግዚአብሔር ቢፈቅድ ስለኦርቶዶክሳዊ ነገር ዕውቀት ትንሽዬ ማስታወሻ ለጾም ቅበላችን እጨምራለሁ፤ መልካም ጾም ያድርግልን። ልዑል እግዚአብሔር ከሚታወቅም ከማይታወቅም ስሐተት ሁላችንንም በቸርነቱ ይጠብቀን፤ አሜን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
በሰው መታረምን በተመለከተ ደግሞ ሌላ ታሪክ ልጨምር። ቃለ እግዚአብሔርን ከምጠያየቃቸው እና ከምጫወታቸው አንዱ የሆነው መምህር በረከት አዝመራው ካነበበው የትርጓሜ መጽሐፍ የነገረኝ ነው። ሙሴ ደብረ ሲና ወጥቶ ሲመለስ እሥራኤል ጣዖት አቁመው ሲሰግዱ አግኝቷቸው እነዚያን ጣዖት የሚያመልኩትን እንዲገደሉ አዝዞ በወገኖቻቸው ተገድለዋል። እርሱ እንደነገረኝ መተርጉማኑ አንድ ጥያቄ አንሥተው ይመልሳሉ። እግዚአብሔር እነዚያን ጣዖት አምላኪዎች እንደ ፈርዖን ለምን ራሱ አላጥፋቸውም ወይም ለምን ራሱ አልቀሰፋቸውም? በሙሴ ትዕዛዝ በራሳቸው ወገኖች እንዲገደሉ ለምን አደረገ የሚል ጥያቄ ያነሡና ይመልሳሉ።
እግዚአብሔር ራሱ ሳያጠፋቸው በራሳቸው ወገኖች እንዲገደሉ ያደረገው ስለሁለት ምክንያት ነው። የመጀመሪያው እሥራኤል ታሪካቸው እግዚአብሔርን ክዶ ጣዖት ማምለክ ብቻ ሳይሆን ጣዖት አምላኪዎችንም የማጥፍት ታሪክ እንዳላቸው እንድናውቅ ነው። ሁለተኛም ከላይ እንዳልነው የሰው ስሐተት በሰው ሲታረም እግዚአብሔር ደስ ስለሚለው ነው የሚል ነው። ከላይ ባየነው ታሪክ መልአኩም ያለው ይህንኑ ነው።
ከዚህም ጋር በሁለቱም አባቶች ታሪክ ላይ አንድ ሌላ መሠራታዊ ትምህርት እናገኛለን። ይኸውም ሰዎች በሚሳሳቱ ጊዜ በሁለንተናቸው ኦርቶዶክሳዊ ሆነው የሆነ ኑፋቄያዊ ቃላት እና ሀሳብ ባገኘንባቸው ጊዜ መማማሩ እንዳለ ሆኖ ልናደርገው የሚገባን ጥንቃቄ ፣ ከበሬታ ፣ ልናሳያቸው የሚገባው ፍቅር ተገልጾልናል። ያን አባት ያረመው ያ ዲያቆን በእኛ ዘመን ቢሆን ኖሮ እንኳን በዚያ አባት በመልአኩም ሊናደድ የሚችል ይመስለኛል። ለምን ሳይቀስፈው ብሎም መልአኩንም የሀሳቡ ተባባሪ አድርጎ ሊቆጥረው ይችላል። (ይህን የምለው ስለእኛ ሕሊና መሆኑ ሳይረሳ) ምክንያቱም የእኛ ዘመን አንዱ ትልቁ ድክመታችን የመጨረሻ ፍርድ ሁሉ ሰጭዎች መሆናችን ነውና።
ማጠቃለያ
እንዲህ ያሉ ነገሮች ለምን ተነሡ? ምን ሲል እንዲህ ተባለ? ለምን እነእገሌ እንዲህ ይላሉ? ... ለምን ዝም ይባላል? የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ማቆም ይኖርብናል። በየትኛውም ዘመን በየትኛውም መዓርግ ባለ መንፈሳዊ ሰውም ላይ ብዙ የምናውቃቸውም የማናውቃቸውም ስሐተቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ መረዳት ተገቢ ነው። እባብ ያዬ በልጥ በረዬ የሚባልላቸው መሆንም የለብንም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነት ታሪኮች ሁልጊዜም ማስተማሪዎች በመሆን አንዱ የእግዚአብሔር የመግቦት መገለጫዎች፣ የየዘመኑን ሰው ማንቂያዎች፣ ወዳጆቹንም መጠበቂያዎች (በተለይ ከትዕቢትና ኩነኔ ከሚያመጣ ጥፋት) ናቸው። ዋናው የሚያስፈልገን ነገር ከሁሉም ነገር እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው፣ እኛ ውስጥ ሊያርመው የፈለገው ነገር ምንድን ነው የሚለው ጥያቄ መሆን አለበት ። ካስተዋልን ሁላችንም የየራሳችንን ስሐተቶች የማየት እና የመታረም ዕድል እናገኝበታለን።
ማር ይስሐቅ መላእክትን ለማየት ከበቃ ሰው ይልቅ የራሱን ስሕተት ለማየት የበቃ ሰው የበለጠ ብቃት ደረጃ ላይ ደርሷል ይላል። ቅዱሱ አባት መላእክትን የሚያይ የውጭ ዐይኑ የተከፈተለት ነው፣ የራሱን ስሕተት የሚያይ ግን የውስጥ ዓይኑ የተከፈተለት ነውና እርሱ የበለጠ በቅቷል እንዳለ ወደ ሰው ስሕተት ከማየት ይልቅ ወደራሳችን ስሐተት ማየት ኦርቶዶክሳዊም መንፈሳዊም መንገድ መሆኑን እናስተውል። በዚህ ጽሑፍ ላነሣቸው ያልፈልኳቸው ብዙ ድክመቶች እንዳሉብን ይሰማኛል። ለሁላችንም የሚጠቅመን ግን የራሳችን ስሐተት ማየት እንጂ የሌሎቹ ላይ ማፍጠጥ እና ከፍ ዝቅ አድርጎ መናገርም ሆነ መጻፍ አይደለምና አጥብቀን እንታረም። ይልቁንም ያለነው በዐቢይ ጾም ዋዜማ ላይ ስለሆነ በቀሩን ቀናት ይቅርታ ተጠያይቀን ከቡድነኝነት፣ ከተሳሳቱ ግምቶች እና ግምታዊ ንግግሮች፣ ከፍረጃ እና ከአጸፋዊ ፍረጃ፣ በማናውቀው እና በማይገባን ነገር ከመነጋገር ወጥተን ወደ መንፈሳዊ ድንኳናችን እንሰብሰብ። ያን ጊዜ ስሕተቶቻቸን ይታዩናል። ለሰዎችም ፍቅር ሐዘኔታ የተመላ የማስተካከያ መንገድ ይገለጽልናል። እግዚአብሔር ቢፈቅድ ስለኦርቶዶክሳዊ ነገር ዕውቀት ትንሽዬ ማስታወሻ ለጾም ቅበላችን እጨምራለሁ፤ መልካም ጾም ያድርግልን። ልዑል እግዚአብሔር ከሚታወቅም ከማይታወቅም ስሐተት ሁላችንንም በቸርነቱ ይጠብቀን፤ አሜን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ስለሌሎች ስንናገር
ስለኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት የገባሁትን ቃል አልረሳሁትም። ነገር ግን ይህች ብትቀደም ወደድኩ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ወደ ግሪክ በሔዱበት ወቅት የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የእኛ ፓትርያርክ ቀድሰው አማኞቻቸውን ያቆርቡበት ዘንድ አንድ ቤተ ክርስቲያን በውሰት ይሰጣሉ። የታሰበው አገልግሎት የተፈጸመበትን ይህን ቤተ መቅደስ ግን ግሪኮች ከዚያ በኋላ አልተጠቀሙበትም። እንደተዘጋ ትተውት ቀሩ እንጂ። ይህን ያደረጉበት ምክንያት ደግሞ ኦሪንታል ኦርቶዶክሶች አውጣኪያውያን ናቸው፤ ስለዚህ እነርሱ አርክሰውታል ብለው በማመን ነው። ይህን የሰማሁት የዛሬ 16 ዓመት ወደ ግሪክ ለአገልግሎት ብቅ ባልኩበት ወቅት እዚያው ግሪክ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ነበር።
ግሪኮች ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች ስለኦሬንታል ኦርቶዶክሶች የነበራቸው አመለካከት ወይም እምነት ይህ ነበር። ይህ የሆነበት ምክንያትም በ448 ዓ.ም. በአውሳብዮስ ከሳሽነት በፍላብያኖስ ዘቁስጥንጠንያ መሪነት ወደ 40 የሚጠጉ ሊቃነ ጳጳሳት ተሰብስበው ነበር። ክስሱ አውጣኬን ባሕርየ መለኮት ባሕርየ ሥጋን ዋጠው መጠጠው ስለዚህ አንድ ንጥል ባሕርይ (Monophysite) ነው ብሎ አስተምሯል የሚል ነበር። በርግጥ ቀጥታ የተጠየቃቸው ጥያቄዎች ሌሎች ነበሩ። በጉባኤው ላይም አውጣኬ በአካል አልተገኘም ነበር። ላቲኖች እንደሚሉት ከሆነ ያልተገኘው የገዳም አበምኔት እንደመሆኑ መጠን በዓቴን ለቅቄ አልወጣም በማለቱ ነበር። በዚህም ምክንያት ይህን ታምናለህ አታምንም እየተባለ የተጠየቀው በመልእክተኞች ሲሆን መልእክተኞቹም ዮሐንስ የሚባል ቄስ እንድርያስ እና አትናቴዎስ የሚባሉ ዲያቆናት እንደነበሩ መዝግበዋል። እነርሱን ወደዚህ ድምዳሜ የወሰዳቸው ግን ጌታ ሰው ከሆነ በኋላ ሁለት ባሕርይ መሆኑን ታምናለህ? ተብሎ ሲጠይቅ እኔ እንዲህ አልልም ቅድመ ተዋሕዶ እንጂ ደኅረ ተዋሕዶ እንደ ቄርሎስ አንድ ባሕርይ እላለሁ እንጂ ሁለት አልልም በማለቱ እነርሱ ሁለት አልልም አንድ እንጂ ካለ አንደኛው ባሕርይ ጠፍቷል ማለቱ ነው የሚል ትርጉም ራሳቸው ሰልሰጡ ነበር። በዚህም ላይ የጌታ ሰውነት እንደ እኛ አይደለም ብሏል ብለው ዲያቆናቱ የሰጡትን ምስክርነት ይዘው ነበር ያወገዙት፤ እንዳነበብኩት።
አውጣኬ ደግሞ እኔ እንደዚህ ብዬ አላስተማርኩም፤ ያወገዙኝ ያለአግባብ ነው ብሎ ለንጉሡ ቴዎዶስዮስ ካልዓይ ክስ አቀረበ። ንጉሡም የእስክንድርያው ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ባለበት እንዲታይለት እርሱን በማወገዝ ግንባር ቀደም የነበሩት እና ልዮን፣ ፍላብያኖስ እና ሊሎች አራት ያልህ ደግሞ በዳኝነት በዚህኛው ጉባኤ እንዳይሰየሙ አዘዘለት ። ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ሊቃነ ጳጳስት እና ሊቃውንት ተሰብስበው የአውጣኬ ክስሱ እንዲሰማ እና የርሱም መልስ እንዲደመጥ በ449 ዓ.ም. ጉባኤ ጠራ። በጉባኤውም ወደ 127 ጳጳሳትና ሊቃውንት ተገኙ። አውጣኬን እንዲወገዝ ያስተባበሩት እነ አውሳብዮስ ፣ ፍላብያኖስ ግን ቢጠሩም ሳይገኙ ቀሩ። ጉባኤው ግን ተካሔደ። አውጣኬም ተጠየቀ። እርሱም እነርሱ ያወገዙኝ እኔን ብሏል የሚሉትን አላልኩም፤ እኔ አንድ ባሕርይ ነው ብዬ አምናለሁ። እምነቴ ቄርሎስ እንዳስተማረው እንጂ እነርሱ እንደሚሉት አይደለም ብሎ ቃሉን ሰጠ። በዚህ ምክንያት ይህ በቅዱስ ዲዮስቆሮስ የሚመራው ጉባኤ አውጣኬን ከግዝቱ ፈታው።
በዚህ ጊዜ ቀድመው ያወገዙት ሰዎች ዲዮስቆሮስ አውጣኬን ከግዝቱ የፈታው ራሱ ዲዮስቆሮስ እንደ እርሱ ቢያምን ነው ብለው ማስወራት ጀመሩ። እንዲያውም ልዮን ይህን ጉባኤ የሚጠራው ጉባኤ ፈያት እያለ እንደነበር ጽሑፍ ማንበቤን አስታውሳለሁ። አስወርተውም አልቀሩ የ451ዱ ጉባኤ ኬልቄዶን እንዲጠራ እና ሀሳቡ እንኳ በአግባቡ ሳይደመጥ ዲዮስቆሮስ እንዲወገዝ ተደረገ። በዚህ ምክንያት እስከቅርብ ጊዜያት አንዳንዶቹም እስካሁን ድረስ ኦሬንታሎቹን አውጣኬያውያን እንደሆንን ያምናሉ። የሚያስገርምም የሚያሳዝንም ነገር ነው።
አንዳንዶች ሀሳባቸውን በታወቀ መንገድ መቀየር እና ማስተካከል የጀመሩት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ (አሁን ዩኒቨርሲቲ) የመጀመሪያው ዲን የነበሩት ሕንዳዊው V.C. Samuel የተባሉት ሊቅ ለሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናታቸው መጽሐፍ ሆኖ ከታተመ በኋላ ነበር። የኒህ አባት መጽሐፍ “the Council of Chalcedon Re-Examined” – ‘ጉባኤ ኬልቄዶን እንደገና ሲመረመር’ በሚል ርእስ በሠሩት ጥናት ላይ ይህን ንጥል አንድ ብቻ ባሕርይ /monophysite/ የሚለውን እንኳን ዲዮስቆሮስ ሊቀበለው ይቅርና አውጣኬም ስለማለቱ ማረጋገጫ አላቀረባቸሁም። እርሱ ያላለውን ብሏል ብላችሁ አወገዛችሁት እንጂ እርሱ እንዲህ ነው የማምነው ብሎ ልክ አርዮስ፣ ንስጥሮስ፣ መቅዶንዮስ እንዳደረጉት አልተከራከረም ፤ ሀሳቡንም አላስረዳም። እርሱ እናንተ የምትከስሱበትን ለማለቱ ማስረጃ የላችሁም። አላልኩም ፤ እኔ የማምነው እንደ ቄርሎስ ነው ስለማለቱ ግን ማስረጃ አለ። ኦሪነታሎች አንድ ባሕርይ የሚለውን የምንጠቀመውም በተዋሕዶ እንጂ እናንተ እንደምትሉን ሞኖፊሳይት አይደለንም፤ አይመለከተንም፤ ይህን ለማረጋገጥ ከፈለጋችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስሟን ብቻ ብትመለከቱ ይበቃችኋል። ተዋሕዶ የሚለውን የስሟ መጠሪያ አድርጋዋለችና የሚለውን ሀሳብ በሰፊ ጥናት ካሳዩ በኋላ ብዙ ሊቃውንቶቻቸው ስለኦሬንታሎች ያላቸውን የተሳሳተ አመለካከት አስተካክለዋል።
በቅርብ ጊዜ ደግሞ የእኛው ቀሲስ ዶክተር መብራቱ ኪሮስ የማስተርስ ጥናቱን በዚህ ዙሪያ በመሥራት የኦሬንታሎቹ እምነት ምሥራቆቹ እንደሚሉን እንዳልሆነ ጥሩ አድርጎ አስረድቷል። የቀሲስ ዶክተር መብራቱ ትኩረቱ ታሪኩ ላይ ሳይሆን ቀጥታ ነገረ እምነታችን ወይም ዶክትሪኑ ላይ ነው። የቀሲስን ጥናት የፈለገ “Miaphysite Chrystology: An Ethiopian Perspective” በሚል ረእስ አፈላልጎ ማግኘት እና ማንበብ ይቻላል። እነዚህን ሁለቱን እንደምሳሌ አነሣሁ እንጂ ሌሎችም ይኖራሉ።
ይህም ሆኖ ብዙዎች ገዳማውያኑ እና ዓለም አቀፍ ጥናቶችን ለማወቅ ወይም እኛን ኦሬንታሎችን ቀርበው እምነታችንን በትክክል ያልተርዱት ግን እስካሁን ድረስ እኛን የሚያዩን አውጣኬያውያን አድርገው ነው። እንዲያውም አንድ ወንድም እንደ ነገረኝ በአቶስ ተራራ (Mount Athos) የኖሩት እና አሁንም ያሉት በኃይለኛ ምናኔ እና ብቃት የሚመሰገኑት የግሪክ ኦርቶዶክስ አባቶች እስካሁን ድረስ ኦሬንታሎችን አጥፋ የሚል ጸሎት ሁሉ አላቸው ብሎ ነግሮኛል። እኔም ራሴ ባለፈው ዐሥር ዓመት ውስጥ አሜሪካን ሀገር ያለ አንድ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካነ ድር ላይ የአውጣኬን እምነት የያዙ ቤተ ክርስቲያኖች አሁንም አሉ፤ ለምሳሌ የኮፕቲክ እና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብሎ ጽፎ አንብቤ እንዴት በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች በቀላሉ መረጃ በሚያገኙበት እንዲህ ትጽፋለህ ብዬ ጽፌለት ጽሑፉን የጻፈው ቄስ ይቅርታ ጠይቆ አስተካክሏል።
ስለኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት የገባሁትን ቃል አልረሳሁትም። ነገር ግን ይህች ብትቀደም ወደድኩ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ወደ ግሪክ በሔዱበት ወቅት የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የእኛ ፓትርያርክ ቀድሰው አማኞቻቸውን ያቆርቡበት ዘንድ አንድ ቤተ ክርስቲያን በውሰት ይሰጣሉ። የታሰበው አገልግሎት የተፈጸመበትን ይህን ቤተ መቅደስ ግን ግሪኮች ከዚያ በኋላ አልተጠቀሙበትም። እንደተዘጋ ትተውት ቀሩ እንጂ። ይህን ያደረጉበት ምክንያት ደግሞ ኦሪንታል ኦርቶዶክሶች አውጣኪያውያን ናቸው፤ ስለዚህ እነርሱ አርክሰውታል ብለው በማመን ነው። ይህን የሰማሁት የዛሬ 16 ዓመት ወደ ግሪክ ለአገልግሎት ብቅ ባልኩበት ወቅት እዚያው ግሪክ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ነበር።
ግሪኮች ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች ስለኦሬንታል ኦርቶዶክሶች የነበራቸው አመለካከት ወይም እምነት ይህ ነበር። ይህ የሆነበት ምክንያትም በ448 ዓ.ም. በአውሳብዮስ ከሳሽነት በፍላብያኖስ ዘቁስጥንጠንያ መሪነት ወደ 40 የሚጠጉ ሊቃነ ጳጳሳት ተሰብስበው ነበር። ክስሱ አውጣኬን ባሕርየ መለኮት ባሕርየ ሥጋን ዋጠው መጠጠው ስለዚህ አንድ ንጥል ባሕርይ (Monophysite) ነው ብሎ አስተምሯል የሚል ነበር። በርግጥ ቀጥታ የተጠየቃቸው ጥያቄዎች ሌሎች ነበሩ። በጉባኤው ላይም አውጣኬ በአካል አልተገኘም ነበር። ላቲኖች እንደሚሉት ከሆነ ያልተገኘው የገዳም አበምኔት እንደመሆኑ መጠን በዓቴን ለቅቄ አልወጣም በማለቱ ነበር። በዚህም ምክንያት ይህን ታምናለህ አታምንም እየተባለ የተጠየቀው በመልእክተኞች ሲሆን መልእክተኞቹም ዮሐንስ የሚባል ቄስ እንድርያስ እና አትናቴዎስ የሚባሉ ዲያቆናት እንደነበሩ መዝግበዋል። እነርሱን ወደዚህ ድምዳሜ የወሰዳቸው ግን ጌታ ሰው ከሆነ በኋላ ሁለት ባሕርይ መሆኑን ታምናለህ? ተብሎ ሲጠይቅ እኔ እንዲህ አልልም ቅድመ ተዋሕዶ እንጂ ደኅረ ተዋሕዶ እንደ ቄርሎስ አንድ ባሕርይ እላለሁ እንጂ ሁለት አልልም በማለቱ እነርሱ ሁለት አልልም አንድ እንጂ ካለ አንደኛው ባሕርይ ጠፍቷል ማለቱ ነው የሚል ትርጉም ራሳቸው ሰልሰጡ ነበር። በዚህም ላይ የጌታ ሰውነት እንደ እኛ አይደለም ብሏል ብለው ዲያቆናቱ የሰጡትን ምስክርነት ይዘው ነበር ያወገዙት፤ እንዳነበብኩት።
አውጣኬ ደግሞ እኔ እንደዚህ ብዬ አላስተማርኩም፤ ያወገዙኝ ያለአግባብ ነው ብሎ ለንጉሡ ቴዎዶስዮስ ካልዓይ ክስ አቀረበ። ንጉሡም የእስክንድርያው ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ባለበት እንዲታይለት እርሱን በማወገዝ ግንባር ቀደም የነበሩት እና ልዮን፣ ፍላብያኖስ እና ሊሎች አራት ያልህ ደግሞ በዳኝነት በዚህኛው ጉባኤ እንዳይሰየሙ አዘዘለት ። ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ሊቃነ ጳጳስት እና ሊቃውንት ተሰብስበው የአውጣኬ ክስሱ እንዲሰማ እና የርሱም መልስ እንዲደመጥ በ449 ዓ.ም. ጉባኤ ጠራ። በጉባኤውም ወደ 127 ጳጳሳትና ሊቃውንት ተገኙ። አውጣኬን እንዲወገዝ ያስተባበሩት እነ አውሳብዮስ ፣ ፍላብያኖስ ግን ቢጠሩም ሳይገኙ ቀሩ። ጉባኤው ግን ተካሔደ። አውጣኬም ተጠየቀ። እርሱም እነርሱ ያወገዙኝ እኔን ብሏል የሚሉትን አላልኩም፤ እኔ አንድ ባሕርይ ነው ብዬ አምናለሁ። እምነቴ ቄርሎስ እንዳስተማረው እንጂ እነርሱ እንደሚሉት አይደለም ብሎ ቃሉን ሰጠ። በዚህ ምክንያት ይህ በቅዱስ ዲዮስቆሮስ የሚመራው ጉባኤ አውጣኬን ከግዝቱ ፈታው።
በዚህ ጊዜ ቀድመው ያወገዙት ሰዎች ዲዮስቆሮስ አውጣኬን ከግዝቱ የፈታው ራሱ ዲዮስቆሮስ እንደ እርሱ ቢያምን ነው ብለው ማስወራት ጀመሩ። እንዲያውም ልዮን ይህን ጉባኤ የሚጠራው ጉባኤ ፈያት እያለ እንደነበር ጽሑፍ ማንበቤን አስታውሳለሁ። አስወርተውም አልቀሩ የ451ዱ ጉባኤ ኬልቄዶን እንዲጠራ እና ሀሳቡ እንኳ በአግባቡ ሳይደመጥ ዲዮስቆሮስ እንዲወገዝ ተደረገ። በዚህ ምክንያት እስከቅርብ ጊዜያት አንዳንዶቹም እስካሁን ድረስ ኦሬንታሎቹን አውጣኬያውያን እንደሆንን ያምናሉ። የሚያስገርምም የሚያሳዝንም ነገር ነው።
አንዳንዶች ሀሳባቸውን በታወቀ መንገድ መቀየር እና ማስተካከል የጀመሩት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ (አሁን ዩኒቨርሲቲ) የመጀመሪያው ዲን የነበሩት ሕንዳዊው V.C. Samuel የተባሉት ሊቅ ለሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናታቸው መጽሐፍ ሆኖ ከታተመ በኋላ ነበር። የኒህ አባት መጽሐፍ “the Council of Chalcedon Re-Examined” – ‘ጉባኤ ኬልቄዶን እንደገና ሲመረመር’ በሚል ርእስ በሠሩት ጥናት ላይ ይህን ንጥል አንድ ብቻ ባሕርይ /monophysite/ የሚለውን እንኳን ዲዮስቆሮስ ሊቀበለው ይቅርና አውጣኬም ስለማለቱ ማረጋገጫ አላቀረባቸሁም። እርሱ ያላለውን ብሏል ብላችሁ አወገዛችሁት እንጂ እርሱ እንዲህ ነው የማምነው ብሎ ልክ አርዮስ፣ ንስጥሮስ፣ መቅዶንዮስ እንዳደረጉት አልተከራከረም ፤ ሀሳቡንም አላስረዳም። እርሱ እናንተ የምትከስሱበትን ለማለቱ ማስረጃ የላችሁም። አላልኩም ፤ እኔ የማምነው እንደ ቄርሎስ ነው ስለማለቱ ግን ማስረጃ አለ። ኦሪነታሎች አንድ ባሕርይ የሚለውን የምንጠቀመውም በተዋሕዶ እንጂ እናንተ እንደምትሉን ሞኖፊሳይት አይደለንም፤ አይመለከተንም፤ ይህን ለማረጋገጥ ከፈለጋችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስሟን ብቻ ብትመለከቱ ይበቃችኋል። ተዋሕዶ የሚለውን የስሟ መጠሪያ አድርጋዋለችና የሚለውን ሀሳብ በሰፊ ጥናት ካሳዩ በኋላ ብዙ ሊቃውንቶቻቸው ስለኦሬንታሎች ያላቸውን የተሳሳተ አመለካከት አስተካክለዋል።
በቅርብ ጊዜ ደግሞ የእኛው ቀሲስ ዶክተር መብራቱ ኪሮስ የማስተርስ ጥናቱን በዚህ ዙሪያ በመሥራት የኦሬንታሎቹ እምነት ምሥራቆቹ እንደሚሉን እንዳልሆነ ጥሩ አድርጎ አስረድቷል። የቀሲስ ዶክተር መብራቱ ትኩረቱ ታሪኩ ላይ ሳይሆን ቀጥታ ነገረ እምነታችን ወይም ዶክትሪኑ ላይ ነው። የቀሲስን ጥናት የፈለገ “Miaphysite Chrystology: An Ethiopian Perspective” በሚል ረእስ አፈላልጎ ማግኘት እና ማንበብ ይቻላል። እነዚህን ሁለቱን እንደምሳሌ አነሣሁ እንጂ ሌሎችም ይኖራሉ።
ይህም ሆኖ ብዙዎች ገዳማውያኑ እና ዓለም አቀፍ ጥናቶችን ለማወቅ ወይም እኛን ኦሬንታሎችን ቀርበው እምነታችንን በትክክል ያልተርዱት ግን እስካሁን ድረስ እኛን የሚያዩን አውጣኬያውያን አድርገው ነው። እንዲያውም አንድ ወንድም እንደ ነገረኝ በአቶስ ተራራ (Mount Athos) የኖሩት እና አሁንም ያሉት በኃይለኛ ምናኔ እና ብቃት የሚመሰገኑት የግሪክ ኦርቶዶክስ አባቶች እስካሁን ድረስ ኦሬንታሎችን አጥፋ የሚል ጸሎት ሁሉ አላቸው ብሎ ነግሮኛል። እኔም ራሴ ባለፈው ዐሥር ዓመት ውስጥ አሜሪካን ሀገር ያለ አንድ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካነ ድር ላይ የአውጣኬን እምነት የያዙ ቤተ ክርስቲያኖች አሁንም አሉ፤ ለምሳሌ የኮፕቲክ እና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብሎ ጽፎ አንብቤ እንዴት በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች በቀላሉ መረጃ በሚያገኙበት እንዲህ ትጽፋለህ ብዬ ጽፌለት ጽሑፉን የጻፈው ቄስ ይቅርታ ጠይቆ አስተካክሏል።
እነዚህ አጋጣሚዎች ለእኔ እጅግ አስተማሪዎች ነበሩ። እውነት ለመናገር ስለሌሎች ከመናገር በፊት እነዚያ አካላት የሚሉትን በትክክል ማወቅ በእጂጉ አስፈላጊ መሆኑንና ስለተለያዩ ብቻ እያነሡ መለጠፍ፣ እንደ ልብ መናገር በጣም አደገኛ መሆኑን የተማርሁት ይህን ከመሰሉ ስለእኛ ከተነገሩ እጂግ የተሳሳቱ ትምህርቶች ፣ ጽሑፎች እና አመለካከቶች ነው። ከዚያም ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ጽሑፎች ውስጥ ሳይቀር ይህን የመሰለውን ስለእኛ ያላቸውን የተሳሳተ እምነታቸውን ሳይ በእጂጉ አዝናለሁ፤ በዚያ ምክንያትም የሥራዎቻቸውን ደኅና ነገር ሁሉ በዚያው ዓይን እያየሁ እንድጠራጠራቸው እሆናለሁ።
ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።
ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።
ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀትን በተመለከተ
አንድ ወንድም ከቲክታክ ውይይት ሰማሁት ብሎ የጠየቅኝ ጆሮጅዬን ጭው ነው ያደረገኝ። አንዳንድ ተወያዮች እድገት ያመጡ እና ከፍ ያለ ዕውቀት ላይ የደረሱ እየመሰላቸው ነው መሰል በአብና በወልድ መካከል ገብተው ሁሉ አስተያየት እየሰጡ መሆኑን (የጠየቀኝ ሰው ያለኝን ቃለ በቃል መድገም አልፈለግሁም) ከጥያቄው ተረድቻለሁ። ኪሩቤል ቀና ብለው ወደማያዩት ዙፋን፣ ሱራፌል በሁለት ክንፎቻቸው እግራቸውን በሁለት ክንፎቻቸው ፊታቸውን ሸፍነው ሁለት ክንፎቻቸውን ደግሞ ዘርግተው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ከማመስገን ውጭ ወደ ማይደፍሯት ዙፋን ወይም ገናንነት መግባት የሚፈልግ ሕሊና በፍጥነት በንስሐ መመለስ አለበት ብዬ አምናለሁ።
አንድ ወንድም አንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ነገር ገጥሞት ነበር። ከጓደኛው ጋር ወደ ጎንደር በሔዱበት ወቅት ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራን ሰላም ለማለት በገቡበት ጥያቄ አነሣ። ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች በአንድ አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉት ባሕርየ ትስብእት ከባሕርየ መለኮት ጋር ከተዋሐደ ፣ ወልድ ደጎሞ በባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ስለሆነ እንዴት ሊይድርገው ነው ይላሉ ብሎ ይጠይቃል፤ እንደማስታውሰው ነው። ሊቀ ሊቃውንትም እርሱ ከበደኝ አላለ እናንተን ምን አስጨነቃችሁ ብለው መለሱለት ብሎ የነገረኝን ባስታወስኩ ቁጥር እደነቃለሁ። (በአጻጻፍ የሳትኩት ካለ ሓላፊነቱ የእኔ ነው)። መልሱ ሁልጊዜ ያስደስተኛል። ምክንያቱም በሥላሴ አንድነት ውስጥ ገብታ ቦታ ለማካፈል የምትደፍር ኅሊና እንዴት ያለች ደፋር እና አላዋቂ ናት በእውነት ። ሙሴ እንኳ ወደ ዕፀ ጳጦስ ለመጠጋት ጫማውን እንዲያውልቅ ታዝዞ ነበር። የቀረበውም በረዓድ እና በመንቀጥቀጥ ነበር። ምሳሌው ለተመረጠው ለሙሴ እንኳ እንዲያ የሚያስፈራ ከሆነ አማናዊው የተዋሕዶ ምሥጢርም ይልቁን ምን ያህል ትሕትና እና ጥንቃቄ ይፈልግ ይሆን?
የተገለጠና እና በትክክል የምናውቀው እንኳ ቢሆን እንዲህ ያለው ይዘት በፍጹም ለማኅበራዊ ሚዲያ የሚሆን አይደለም። እውነቱን ለመናገር “የተቀደሰውን ለውሾች አት ስጡን” ለምን አንጠብቀውም የሚለውን እጠይቅና የተቀደሰውን ስለማናውቀው ይሆናል በሚል መልስ እንደገና እቆማለሁ። በርግጥም የምናውቀው አይመስለኝም። ይህ ሁሉ እንግዲህ ኦርቶዶክሳዊውን ነገረ ዕውቀት በመጠቆም ለማሳሰብ እንደ መግቢያ ያነሣሁት ነው።
ሴባስቲያን ብሮክ የሚባለው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የኦሬንታል በተለይም የሶርያ ኦርቶዶክስ አባቶችን ጽሑፎች በተመለከተ ብዙ ካጠና በኋላ ሀሳቦቹን ካጋራባቸው መጻሕፍት አንዱ ሰሞኑን በሕሊና በለጠ ብርህት ዓይን ተብሎ የተተረጎመውን The luminous Eye የተባለ መጸሐፍ ጽፏል። ብሮክ በዚህ መጽሐፉ ካነሳቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የምሥራቃውያን (ኦሬንታል) አባቶች ትምህርታቸውን እንደ ምዕራቡ በነገረ ጉዳይ የተደራጀ (Systematic) ለምን አላዳረጉትም የሚለው ይገኝበታል። (ይህን ስጽፍ መጽሐፉን እያየሁ ስላልሆነ በትክክል ባልገልጸውም አሁን) እርሱ የሚለው የኦሬንታል ሊቃውንት የምዕራብ ሊቃውንት ያደረጉትን ማድረግ ስለማይችሉ ወይም አቅም ስለሌላቸው ሳይሆን ስለኦርቶዶክስ ነገረ ዕውቀት ባላቸው መረዳት ምክንያት ነው። ለምሳሌ የምዕራብ ሊቃውንት አንድን ጉዳይ ብያኔ (definition) ሰጥተው ይጽፋሉ። ለምሥራቃውያን ደግሞ ብያኔ ችግር ያመጣል።
ምክንያቱም መበየን ማለት ለነገሮች ድንበር መሥራት፣ መከለል፣ መለየት፣ መወሰን ማለት ነው። ነገረ ሃይማኖት ደግሞ ለሰው ልጅ አእምሮ በሚመጥን ከእግዚአብሔር የተገለጠ መለኮታዊ ሀሳብ ነው። ያን መልኮታዊ ሀሳብ ደግሞ ጥልቀቱን መወሰን እና ለዚያም ድንበር ማበጀት አይቻልም። የሰው ቋንቋም ለሰው ማስረዳት ቢችልም ነገረ አምላክን ወስኖ መያዝ ግን አይችልም። ስለዚህ እግዚአብሔር በገለጠልን መጠን እናብራራዋለን (እንተረጉመዋለን) እንጂ ልንወስነው ወይም በብያኔ ልንዘጋው አንችልም የሚል እምነት ወይም አረዳድ ስላላቸው ብያኔ እና ብያኔያዊ አካሔድ አይጠቀሙም የሚል ማብራሪያ ይሰጣል። ይህን ሀሳብ በየንታ እሸቱ ርጢን መጽሐፍ መቅድም ላይ ለመጠቆም ሙከራ አድርጊያለሁና ያንንም ማየት ይቻላል።ይህን እውነታ ከእኛም ሆነ ከሌሎች የኦሬንታል አብያተ ክርስቲያን ትውፊት መረዳት ይቻላል።
ኦሬንታሎቹን ብቻ ሳይሆን እኔ እስካየሁት ድረስ ምሥራቅ ኦርቶዶክሶችን ከምዕራቡ (ከካቶሊክም ከሮቴስታንትም) ከሚለዩን መሠረታዊ ነገሮች አንዱ ይህን የሚመለከት ነው።
ሌላውና መሠረታዊው የኦርቶቶዶክስ ነገረ ዕውቀት የሚያጠነጥነው ደግሞ መገለጥ ላይ ነው። መገለጥ በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በሮማ ካቶሊክ በተለይም ደግሞ ከቶማስ አኲናስ መምጣት በኋላ (በእምነት መግለጫዋ ላይም እንዳለው) የሰው አእምሮ ወይም የመረዳት ችሎታ (reason) ብቻውን እግዚአብሔርን በርግጠኝነት ለማወቅ በአጠቃላይ ሃይማኖትን ለማወቅ በቂ ነው ብለው ያምናሉ። (ይህን ሀሳብ Thinking Orthodox እና የመሳሰሉትን መጻሕፍት አንብቦ የበለጠ መረዳት ይቻላል።)
በሁለቱም ኦርቶዶክሶች ግን ይህ ሀሳብ ተቀባይነት የለውም። እንደዚህ ከሆነ ሃይማኖት ከሳይንስ የሚለይበት መሠረታዊ ነገር ይጠፋል ወይም ያንሣል። ይህን ጉዳይ አሁንም በስፋት መግባት ባልፈልግም ኦርቶዶክሳዊው ነገረ ዕውቀት ከዚህ በጅጉ የራቀ እና የተለየ መንገድ ያለው ነው። ምንም እንኳ ሲስተማቲክ ቲዖሎጂ በእኛም ተቋማት እየተሰጠ እና በዚሁ መንገድ መጻሕፍት እየተጻፉና እየተዘጋጁ ቢሆንም መሠርታዊ ጥንቃቄ እና ኦርቶዶክሳዊውን ድነበር መጠበቅ ግን በብዙ የምሥራቅ ሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ብቻ ሳይሆን የተለመደም ጭምር ነው።
በኦርቶዶክሳዊያን ዘንድ ደግሞ በሰው አእምሮ አድሮ የሚናገረው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ይህም በጥልቅ መግቦቱ ለሰው ልጆች በመግለጥ የሚያሳየው ነው። ሰዎች በቅጥነተ ኅሊና ማለትም አእምሮአቸውን በማራቀቅ ብቻ ሊደርሱበት የሚቻላቸውም አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን “እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤” /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 1 – 2/ የሚላቸው በክርስትና ለመንፈሳዊ ሕይወት ሕጻናት ስለሆኑ እንጂ ለእውቀት ለፍልስፍና እና ለአመክንዮ ሕጻናት ሆነው አልነበረም ባዮች ናቸው። ስለዚህ በመንፈሳዊ ሕይወት በተጋድሎ ውስጥ በምትገኝ የማትቋረጥ መገለጥ የሚሰጥ እንጂ የሰው አእምሮ የማሰብ ችሎታ ብቻውን ይደርስበት ዘንድ አይቻልም ብለው ያምናሉ። በተለይም ደግሞ መጀመሪያ ቅዱስ ወግሪስ እንደተናገረው የሚታመነው “እውነተኛ የነገረ ሃይማኖት ዐዋቂ የሚጸልይ ሰው ነው” የሚለው አባባል የሰው የሃይማኖት ዕውቀት የመረዳት ችሎታ ላይ እንዳያርፍ መጠበቂያ አጥራቸው ነው።
የኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት ሦስተኛው መሠረታዊ መለያ ደግሞ ሃይማኖታዊ ዕውቀት በመሠርቱ ለሰዎች ድኅነት ቅድሚያ የሰጠ (Pastoral) መሆኑ ነው። ይህም ማለት ጉዳዮች የሚብራሩት የሚተረጎሙት የሚሰበኩት የሰውን ድኅነት ቅድሚያ ሰጥተው እንጂ ለዕውቀት እና ለርቃቄ ተብለው አይደለም። ከዚህ የተነሣ ለድኅነት ከሚጠቅመው ውጭ እንኳን እንዳሁኑ ማንም ሊያየው በሚችል ሚዲያ ይቅርና ለኦርቶዶክሳዊያን ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን የጉባኤ ቀለም ለመናገር እና ለማራቀቅ የሚደክም የለም፣ ሲያጋጥምም አይመሰገንም። ምክንያቱም ለድኅነታቸው
አንድ ወንድም ከቲክታክ ውይይት ሰማሁት ብሎ የጠየቅኝ ጆሮጅዬን ጭው ነው ያደረገኝ። አንዳንድ ተወያዮች እድገት ያመጡ እና ከፍ ያለ ዕውቀት ላይ የደረሱ እየመሰላቸው ነው መሰል በአብና በወልድ መካከል ገብተው ሁሉ አስተያየት እየሰጡ መሆኑን (የጠየቀኝ ሰው ያለኝን ቃለ በቃል መድገም አልፈለግሁም) ከጥያቄው ተረድቻለሁ። ኪሩቤል ቀና ብለው ወደማያዩት ዙፋን፣ ሱራፌል በሁለት ክንፎቻቸው እግራቸውን በሁለት ክንፎቻቸው ፊታቸውን ሸፍነው ሁለት ክንፎቻቸውን ደግሞ ዘርግተው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ከማመስገን ውጭ ወደ ማይደፍሯት ዙፋን ወይም ገናንነት መግባት የሚፈልግ ሕሊና በፍጥነት በንስሐ መመለስ አለበት ብዬ አምናለሁ።
አንድ ወንድም አንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ነገር ገጥሞት ነበር። ከጓደኛው ጋር ወደ ጎንደር በሔዱበት ወቅት ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራን ሰላም ለማለት በገቡበት ጥያቄ አነሣ። ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች በአንድ አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉት ባሕርየ ትስብእት ከባሕርየ መለኮት ጋር ከተዋሐደ ፣ ወልድ ደጎሞ በባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ስለሆነ እንዴት ሊይድርገው ነው ይላሉ ብሎ ይጠይቃል፤ እንደማስታውሰው ነው። ሊቀ ሊቃውንትም እርሱ ከበደኝ አላለ እናንተን ምን አስጨነቃችሁ ብለው መለሱለት ብሎ የነገረኝን ባስታወስኩ ቁጥር እደነቃለሁ። (በአጻጻፍ የሳትኩት ካለ ሓላፊነቱ የእኔ ነው)። መልሱ ሁልጊዜ ያስደስተኛል። ምክንያቱም በሥላሴ አንድነት ውስጥ ገብታ ቦታ ለማካፈል የምትደፍር ኅሊና እንዴት ያለች ደፋር እና አላዋቂ ናት በእውነት ። ሙሴ እንኳ ወደ ዕፀ ጳጦስ ለመጠጋት ጫማውን እንዲያውልቅ ታዝዞ ነበር። የቀረበውም በረዓድ እና በመንቀጥቀጥ ነበር። ምሳሌው ለተመረጠው ለሙሴ እንኳ እንዲያ የሚያስፈራ ከሆነ አማናዊው የተዋሕዶ ምሥጢርም ይልቁን ምን ያህል ትሕትና እና ጥንቃቄ ይፈልግ ይሆን?
የተገለጠና እና በትክክል የምናውቀው እንኳ ቢሆን እንዲህ ያለው ይዘት በፍጹም ለማኅበራዊ ሚዲያ የሚሆን አይደለም። እውነቱን ለመናገር “የተቀደሰውን ለውሾች አት ስጡን” ለምን አንጠብቀውም የሚለውን እጠይቅና የተቀደሰውን ስለማናውቀው ይሆናል በሚል መልስ እንደገና እቆማለሁ። በርግጥም የምናውቀው አይመስለኝም። ይህ ሁሉ እንግዲህ ኦርቶዶክሳዊውን ነገረ ዕውቀት በመጠቆም ለማሳሰብ እንደ መግቢያ ያነሣሁት ነው።
ሴባስቲያን ብሮክ የሚባለው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የኦሬንታል በተለይም የሶርያ ኦርቶዶክስ አባቶችን ጽሑፎች በተመለከተ ብዙ ካጠና በኋላ ሀሳቦቹን ካጋራባቸው መጻሕፍት አንዱ ሰሞኑን በሕሊና በለጠ ብርህት ዓይን ተብሎ የተተረጎመውን The luminous Eye የተባለ መጸሐፍ ጽፏል። ብሮክ በዚህ መጽሐፉ ካነሳቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የምሥራቃውያን (ኦሬንታል) አባቶች ትምህርታቸውን እንደ ምዕራቡ በነገረ ጉዳይ የተደራጀ (Systematic) ለምን አላዳረጉትም የሚለው ይገኝበታል። (ይህን ስጽፍ መጽሐፉን እያየሁ ስላልሆነ በትክክል ባልገልጸውም አሁን) እርሱ የሚለው የኦሬንታል ሊቃውንት የምዕራብ ሊቃውንት ያደረጉትን ማድረግ ስለማይችሉ ወይም አቅም ስለሌላቸው ሳይሆን ስለኦርቶዶክስ ነገረ ዕውቀት ባላቸው መረዳት ምክንያት ነው። ለምሳሌ የምዕራብ ሊቃውንት አንድን ጉዳይ ብያኔ (definition) ሰጥተው ይጽፋሉ። ለምሥራቃውያን ደግሞ ብያኔ ችግር ያመጣል።
ምክንያቱም መበየን ማለት ለነገሮች ድንበር መሥራት፣ መከለል፣ መለየት፣ መወሰን ማለት ነው። ነገረ ሃይማኖት ደግሞ ለሰው ልጅ አእምሮ በሚመጥን ከእግዚአብሔር የተገለጠ መለኮታዊ ሀሳብ ነው። ያን መልኮታዊ ሀሳብ ደግሞ ጥልቀቱን መወሰን እና ለዚያም ድንበር ማበጀት አይቻልም። የሰው ቋንቋም ለሰው ማስረዳት ቢችልም ነገረ አምላክን ወስኖ መያዝ ግን አይችልም። ስለዚህ እግዚአብሔር በገለጠልን መጠን እናብራራዋለን (እንተረጉመዋለን) እንጂ ልንወስነው ወይም በብያኔ ልንዘጋው አንችልም የሚል እምነት ወይም አረዳድ ስላላቸው ብያኔ እና ብያኔያዊ አካሔድ አይጠቀሙም የሚል ማብራሪያ ይሰጣል። ይህን ሀሳብ በየንታ እሸቱ ርጢን መጽሐፍ መቅድም ላይ ለመጠቆም ሙከራ አድርጊያለሁና ያንንም ማየት ይቻላል።ይህን እውነታ ከእኛም ሆነ ከሌሎች የኦሬንታል አብያተ ክርስቲያን ትውፊት መረዳት ይቻላል።
ኦሬንታሎቹን ብቻ ሳይሆን እኔ እስካየሁት ድረስ ምሥራቅ ኦርቶዶክሶችን ከምዕራቡ (ከካቶሊክም ከሮቴስታንትም) ከሚለዩን መሠረታዊ ነገሮች አንዱ ይህን የሚመለከት ነው።
ሌላውና መሠረታዊው የኦርቶቶዶክስ ነገረ ዕውቀት የሚያጠነጥነው ደግሞ መገለጥ ላይ ነው። መገለጥ በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በሮማ ካቶሊክ በተለይም ደግሞ ከቶማስ አኲናስ መምጣት በኋላ (በእምነት መግለጫዋ ላይም እንዳለው) የሰው አእምሮ ወይም የመረዳት ችሎታ (reason) ብቻውን እግዚአብሔርን በርግጠኝነት ለማወቅ በአጠቃላይ ሃይማኖትን ለማወቅ በቂ ነው ብለው ያምናሉ። (ይህን ሀሳብ Thinking Orthodox እና የመሳሰሉትን መጻሕፍት አንብቦ የበለጠ መረዳት ይቻላል።)
በሁለቱም ኦርቶዶክሶች ግን ይህ ሀሳብ ተቀባይነት የለውም። እንደዚህ ከሆነ ሃይማኖት ከሳይንስ የሚለይበት መሠረታዊ ነገር ይጠፋል ወይም ያንሣል። ይህን ጉዳይ አሁንም በስፋት መግባት ባልፈልግም ኦርቶዶክሳዊው ነገረ ዕውቀት ከዚህ በጅጉ የራቀ እና የተለየ መንገድ ያለው ነው። ምንም እንኳ ሲስተማቲክ ቲዖሎጂ በእኛም ተቋማት እየተሰጠ እና በዚሁ መንገድ መጻሕፍት እየተጻፉና እየተዘጋጁ ቢሆንም መሠርታዊ ጥንቃቄ እና ኦርቶዶክሳዊውን ድነበር መጠበቅ ግን በብዙ የምሥራቅ ሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ብቻ ሳይሆን የተለመደም ጭምር ነው።
በኦርቶዶክሳዊያን ዘንድ ደግሞ በሰው አእምሮ አድሮ የሚናገረው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ይህም በጥልቅ መግቦቱ ለሰው ልጆች በመግለጥ የሚያሳየው ነው። ሰዎች በቅጥነተ ኅሊና ማለትም አእምሮአቸውን በማራቀቅ ብቻ ሊደርሱበት የሚቻላቸውም አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን “እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤” /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 1 – 2/ የሚላቸው በክርስትና ለመንፈሳዊ ሕይወት ሕጻናት ስለሆኑ እንጂ ለእውቀት ለፍልስፍና እና ለአመክንዮ ሕጻናት ሆነው አልነበረም ባዮች ናቸው። ስለዚህ በመንፈሳዊ ሕይወት በተጋድሎ ውስጥ በምትገኝ የማትቋረጥ መገለጥ የሚሰጥ እንጂ የሰው አእምሮ የማሰብ ችሎታ ብቻውን ይደርስበት ዘንድ አይቻልም ብለው ያምናሉ። በተለይም ደግሞ መጀመሪያ ቅዱስ ወግሪስ እንደተናገረው የሚታመነው “እውነተኛ የነገረ ሃይማኖት ዐዋቂ የሚጸልይ ሰው ነው” የሚለው አባባል የሰው የሃይማኖት ዕውቀት የመረዳት ችሎታ ላይ እንዳያርፍ መጠበቂያ አጥራቸው ነው።
የኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት ሦስተኛው መሠረታዊ መለያ ደግሞ ሃይማኖታዊ ዕውቀት በመሠርቱ ለሰዎች ድኅነት ቅድሚያ የሰጠ (Pastoral) መሆኑ ነው። ይህም ማለት ጉዳዮች የሚብራሩት የሚተረጎሙት የሚሰበኩት የሰውን ድኅነት ቅድሚያ ሰጥተው እንጂ ለዕውቀት እና ለርቃቄ ተብለው አይደለም። ከዚህ የተነሣ ለድኅነት ከሚጠቅመው ውጭ እንኳን እንዳሁኑ ማንም ሊያየው በሚችል ሚዲያ ይቅርና ለኦርቶዶክሳዊያን ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን የጉባኤ ቀለም ለመናገር እና ለማራቀቅ የሚደክም የለም፣ ሲያጋጥምም አይመሰገንም። ምክንያቱም ለድኅነታቸው
ሳይሆን ለመመስገን፣ ለምደነቅ ወይም ለመከበር ተብሎ ስለሚሆን እና እነዚህም ጠባያት ደግሞ የሥጋ ጠባዮች ስለሆኑ እነዚህ መግቢያ አድርጎ ሰይጣን እንዳያስተውም ስለሚፈራ ነው።
ሁልጊዜም ቢሆን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ችግሮች የሚፈጠሩት ቲኦሎጂን ወይም ነገረ እምነትን ለአማኞች ድኅነት ቅድሚያ ሰጥቶ ማስተማር ቀርቶ የራስን ፍላጎት ለማርካት በሚደረግ አላስፈልጊ ዕውቀት መሰል ክርክር ውስጥ ነው። ይህ ጉዳይ ከዚህም አልፎ ክርክር በማያስነሡ ጉዳዮች እንኳን የሚነሣው የተለየ ነገር ተናግሮ ማስደነቅና መከበርንም ሆነ ሌላ ነገር ሲፈለግ የሚያጋጥም ስለሆነ ነው።
እንዲያውም ከዚህም አልፎ አሁንም ብዙ ገዳማዊያን ሊቃውንት አንድ መሠረታዊ ሥጋታቸውን ደጋግመው ሲያነሡ አይቻለሁ። ይህም አሁን አሁን ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ወደ ዕውቀትነት እያወረዱት ነው የሚል ሥጋት ነው። ይህ ሥጋታቸው ደግሞ ተራ ሥጋት አይደለም። በአሁኑ ጊዜ በርከት ያሉ ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ያጠኑታል፣ ለማወቅ ይጥሩለታል፣ ይወድዱታል፤ በዚያም ደስተኞች ይሆናሉ። ከዚህም የተነሣ ወደ እውነተኛው የመዳን ዕውቅት ሳይሸጋገሩ ልክ እንደ አካዳሚክ ዕውቀት በጥናት ላይ ብቻ ተመሥርተው ይቀራሉ። ይህ ባሕል እየሆነና እየተለመደ ስለሔደ ክርስቲያናዊው እውነተኛው ሕይወታዊውን ዕውቀት አካዳሚያዊ ዕውቀት እየተካው ስለሆነ ክርስትና አደጋ ላይ ነው ያለው ይላሉ። ይህን የሚሉበት ምክንያት ክርስቲያናዊ ዕውቀት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት በማድረግ ከመነገር በላይ ወደ ሆነው ወደ ሚኖረው ዕውቀት ካልተሸጋገረ አካዳሚያዊ ዕውቀት ይሆናል። ከዚህም የተነሣ እንደማንኛውም አካዳሚያዊ ነገር በሰው አእምሮ መረዳት (reasoning) ላይ ይወሰንና ስፉሕ አእምሮ ያላቸው ሰዎች ሲመጡ ያንን የሚያሻሽሉት የሚያስፋፉት፣ ጠባብ አእምሮ ያላቸው ሲይዙት ደግሞ እንደዚያው የሚያጠብቡት ይሆንና በመጨረሻም በሒደት የመበረዝ ፣ የመለወጥ ፣ የመጥፋት አደጋ ይገጥመዋል የሚል ተጨባጭ ሥጋት አላቸው።
የእኛ ዘመን ተሟጋች ትውልድ ደግሞ አብዛኛው መጀመሪያ የተማረው ዘመናዊውን ወይም ምዕራባዊውን ትምህርት ነው። ይህን አስቀድሞ መማር በራሱ ችግር አይደለም፤ ( ሊሆንም አይችልም። እነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮ ዘእንዚናዙ እና ሊሎችም ጭምር መጀመሪያ የተማሩት የዓለሙን ፍልስፍና ነውና። የእኛ ትውልድ ግን ከመጠን በላይ ሲስተማቲክ በሆነው አካዳሚክስ ውስጥ ከማለፉ የተነሣ ነገሮችን ሳያውቀው በዚያ መጠን የመበየን፣ ጨርሶ የማወቅ እና አቋም መያዝ ድረስ መድረሱ ችግሩ ብቅ እያለ መሆኑን ያመለክታል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም ክርስትናን ከትምህርት ከሚገኝ መጠነኛ ዕውቀት በሕይወት ወደሚደረስበት የመረዳት ዕውቀት ካልተሸጋገረ ችግር መግጠሙ አይቀሬ ነው። በሰሚዕ የሚገኝ ዕውቀት እና እምነት መግቢያ በር እንጂ መድረሻ አዳራሽ ወይም ቤት አይደለምና።
ይህ ጉዳይ ራሱን የቻለ ብዙ እንድንማማር የሚያደርግ ስለሆነ ጊዜውና ችሎታው ያላችሁ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ ዕውቀት ብታካፍሉን ብዙዎቻቸን መንገዳችንን ለማቃናት ብዙ ይጠቅመናል፤ ጉዳዮችን በአካዳሚ መንገድ እና ዓይን ከማየት፣ አለፍ ሲልም እንደ ፖለቲካ አቋምን ከመለካካት ሊያተርፉን ይችላሉ፤ ሲሆን ሲሆን ደግሞ ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንድንገባ እና መንገዳችንን ወደዚያ እንድናደርግ ሊረዱን ይችላሉ ብዬ አስባለሁ።
ከሰሞኑ ውይይቶች በተለይ አስተያየት መስጫ ላይ የማያቸው ጥያቄዎች እና መልሶች ብዙዎቹ ትውልዱ ወደዚህ አካዳሚያዊ የነገረ መለኮት ዕውቀት ሳያውቀውም ቢሆን እያደላ መሆኑን የሚጠቁሙ ይመስለኛል። በእኔ መረዳት ኦርቶዶክሳዊ የነገረ ዕውቀት አቀራረብ ቀርቶ ምዕራባዊ የምነለውንና የራሱ ሥነ ሥርዓት ያለውንም ያንን እንኳ የማያሟሉ፣ የነገሮቹን መቅድማቸውን እንኳ በውል ሳናገኘው አንኳር ጉዳዩ ላይ ገብተን እንደዚያ ያለ አስተያየቶች መወራወራችን በእጂጉ ያስፈራል። ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው በእጂጉ ያስፈራል። እኔን እስከገባኝ ደርሰ ከፍተኛ ድፍረት የተሞላው የአላዋቂ ክርክር ወስጥ መሆናችንን በታላቅ ትሕትና (ነገሩ እንኳ ሳስበው ድፍረትም ጭምር ነው) መጠቆም እፈልጋለሁ።
በማኅበራዊ ሚዲያ ልናደርጋቸው የሚገቡንን ውይይቶች እና ትምህርቶች በተመለከተ እኔ ከጠቆምኳቸው እና ከሌሎቹም መሠረታዊ ትውፊቶቻችን አንጻር በማየት በውስጥ መወያየት እና አቀራረቦችን ማስተካከል ይቻላል፤ ይገባለም ብዬ አምናለሁ። አበቃሁ። መልካም ጾም ይሁንልን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ሁልጊዜም ቢሆን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ችግሮች የሚፈጠሩት ቲኦሎጂን ወይም ነገረ እምነትን ለአማኞች ድኅነት ቅድሚያ ሰጥቶ ማስተማር ቀርቶ የራስን ፍላጎት ለማርካት በሚደረግ አላስፈልጊ ዕውቀት መሰል ክርክር ውስጥ ነው። ይህ ጉዳይ ከዚህም አልፎ ክርክር በማያስነሡ ጉዳዮች እንኳን የሚነሣው የተለየ ነገር ተናግሮ ማስደነቅና መከበርንም ሆነ ሌላ ነገር ሲፈለግ የሚያጋጥም ስለሆነ ነው።
እንዲያውም ከዚህም አልፎ አሁንም ብዙ ገዳማዊያን ሊቃውንት አንድ መሠረታዊ ሥጋታቸውን ደጋግመው ሲያነሡ አይቻለሁ። ይህም አሁን አሁን ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ወደ ዕውቀትነት እያወረዱት ነው የሚል ሥጋት ነው። ይህ ሥጋታቸው ደግሞ ተራ ሥጋት አይደለም። በአሁኑ ጊዜ በርከት ያሉ ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ያጠኑታል፣ ለማወቅ ይጥሩለታል፣ ይወድዱታል፤ በዚያም ደስተኞች ይሆናሉ። ከዚህም የተነሣ ወደ እውነተኛው የመዳን ዕውቅት ሳይሸጋገሩ ልክ እንደ አካዳሚክ ዕውቀት በጥናት ላይ ብቻ ተመሥርተው ይቀራሉ። ይህ ባሕል እየሆነና እየተለመደ ስለሔደ ክርስቲያናዊው እውነተኛው ሕይወታዊውን ዕውቀት አካዳሚያዊ ዕውቀት እየተካው ስለሆነ ክርስትና አደጋ ላይ ነው ያለው ይላሉ። ይህን የሚሉበት ምክንያት ክርስቲያናዊ ዕውቀት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት በማድረግ ከመነገር በላይ ወደ ሆነው ወደ ሚኖረው ዕውቀት ካልተሸጋገረ አካዳሚያዊ ዕውቀት ይሆናል። ከዚህም የተነሣ እንደማንኛውም አካዳሚያዊ ነገር በሰው አእምሮ መረዳት (reasoning) ላይ ይወሰንና ስፉሕ አእምሮ ያላቸው ሰዎች ሲመጡ ያንን የሚያሻሽሉት የሚያስፋፉት፣ ጠባብ አእምሮ ያላቸው ሲይዙት ደግሞ እንደዚያው የሚያጠብቡት ይሆንና በመጨረሻም በሒደት የመበረዝ ፣ የመለወጥ ፣ የመጥፋት አደጋ ይገጥመዋል የሚል ተጨባጭ ሥጋት አላቸው።
የእኛ ዘመን ተሟጋች ትውልድ ደግሞ አብዛኛው መጀመሪያ የተማረው ዘመናዊውን ወይም ምዕራባዊውን ትምህርት ነው። ይህን አስቀድሞ መማር በራሱ ችግር አይደለም፤ ( ሊሆንም አይችልም። እነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮ ዘእንዚናዙ እና ሊሎችም ጭምር መጀመሪያ የተማሩት የዓለሙን ፍልስፍና ነውና። የእኛ ትውልድ ግን ከመጠን በላይ ሲስተማቲክ በሆነው አካዳሚክስ ውስጥ ከማለፉ የተነሣ ነገሮችን ሳያውቀው በዚያ መጠን የመበየን፣ ጨርሶ የማወቅ እና አቋም መያዝ ድረስ መድረሱ ችግሩ ብቅ እያለ መሆኑን ያመለክታል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም ክርስትናን ከትምህርት ከሚገኝ መጠነኛ ዕውቀት በሕይወት ወደሚደረስበት የመረዳት ዕውቀት ካልተሸጋገረ ችግር መግጠሙ አይቀሬ ነው። በሰሚዕ የሚገኝ ዕውቀት እና እምነት መግቢያ በር እንጂ መድረሻ አዳራሽ ወይም ቤት አይደለምና።
ይህ ጉዳይ ራሱን የቻለ ብዙ እንድንማማር የሚያደርግ ስለሆነ ጊዜውና ችሎታው ያላችሁ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ ዕውቀት ብታካፍሉን ብዙዎቻቸን መንገዳችንን ለማቃናት ብዙ ይጠቅመናል፤ ጉዳዮችን በአካዳሚ መንገድ እና ዓይን ከማየት፣ አለፍ ሲልም እንደ ፖለቲካ አቋምን ከመለካካት ሊያተርፉን ይችላሉ፤ ሲሆን ሲሆን ደግሞ ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንድንገባ እና መንገዳችንን ወደዚያ እንድናደርግ ሊረዱን ይችላሉ ብዬ አስባለሁ።
ከሰሞኑ ውይይቶች በተለይ አስተያየት መስጫ ላይ የማያቸው ጥያቄዎች እና መልሶች ብዙዎቹ ትውልዱ ወደዚህ አካዳሚያዊ የነገረ መለኮት ዕውቀት ሳያውቀውም ቢሆን እያደላ መሆኑን የሚጠቁሙ ይመስለኛል። በእኔ መረዳት ኦርቶዶክሳዊ የነገረ ዕውቀት አቀራረብ ቀርቶ ምዕራባዊ የምነለውንና የራሱ ሥነ ሥርዓት ያለውንም ያንን እንኳ የማያሟሉ፣ የነገሮቹን መቅድማቸውን እንኳ በውል ሳናገኘው አንኳር ጉዳዩ ላይ ገብተን እንደዚያ ያለ አስተያየቶች መወራወራችን በእጂጉ ያስፈራል። ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው በእጂጉ ያስፈራል። እኔን እስከገባኝ ደርሰ ከፍተኛ ድፍረት የተሞላው የአላዋቂ ክርክር ወስጥ መሆናችንን በታላቅ ትሕትና (ነገሩ እንኳ ሳስበው ድፍረትም ጭምር ነው) መጠቆም እፈልጋለሁ።
በማኅበራዊ ሚዲያ ልናደርጋቸው የሚገቡንን ውይይቶች እና ትምህርቶች በተመለከተ እኔ ከጠቆምኳቸው እና ከሌሎቹም መሠረታዊ ትውፊቶቻችን አንጻር በማየት በውስጥ መወያየት እና አቀራረቦችን ማስተካከል ይቻላል፤ ይገባለም ብዬ አምናለሁ። አበቃሁ። መልካም ጾም ይሁንልን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
«ዝክረ ኒቅያ» ሀገር አቀፍ የሊቃውንት ጉባኤ ሊዘጋጅ ነው!
የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)
<<የሊቃውንት ብዛት ለዓለም መድኃኒት ነው>>
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ታሪካዊና በዓይነቱ ልዩ የሆነ <<ዝክረ ኒቂያ>> የተሰኘ ሀገር አቀፍ የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ከሚያዚያ 20 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለማካሔድ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ የጉባኤውን ዓላማ እና ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ፋይዳ አስመልክቶ ዛሬ ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሕዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት መግለጫ በሊቃውንት ጉባኤ ተሰጥቷል፡፡
በቀደምት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥያቄዎችና የኑፋቄ ትምህርቶች ሲነሱ መልስ ለመስጠት ሊቃውንቱ ተሰባስበው ምላሽ የሚሰጡ መሆኑንና አሁንም በቤተ ክርስቲያን ላይ በነገረ ሃይማኖት እንዲሁም በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተለያዩ ኑፋቄና ቀኖናዊ ጥያቄዎች እየተነሱ በመሆኑ የሊቃውንት መሰባሰብ አስፈላጊ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡
ጉባኤው ከጥር 26-29 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለማካሄድ ታቅዶ እንቅስቃሴ ሲደረግ የቆየ ቢሆንም፡-
1ኛ) ጉባኤው በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንት የሚታደሙበት እንደመሆኑ፥ በተለይ በጠረፉ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ መምህራንን በበቂ ቊጥር ለማካተት እንዲቻል ፥ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ፤
2ኛ) በጥር ወር በርካታ ሀገራዊ ክንውኖችና ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት በየአካባቢው የሚካሄዱ በመሆናቸው የጉባኤው መካሄጃ ጊዜ እንዲስተካከል ከአንዳንድ አህጉረ ስብከት በተደጋጋሚ አስተያየት በመሰጠቱ ፤
3ኛ) ጉባኤው ከዘመናት ቆይታ በኋላ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድና በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቃሚ ውይይቶችን በማካሄድ ፥ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የሚጠቅም የውሳኔ ሐሳብና አስተያየት የሚያቀርብ ፥ አልፎም የአቋም መግለጫ የሚያወጣ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ከመካሄዱ ጥቂት ቀደም ብሎ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፥ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፥ የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች በሚገኙበት ከሚያዝያ 20-25 ቀን 2017 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሚካሄድ ይሆናል።
በጉባኤው፡- ያለውን ማጽናት፣ የጠመመውን ማቅናት፣ የጠፋውን መፈለግ፣ ሊቃውንቱን እርስ በእርስ ማስተዋወቅና ቤተክርስቲያን ያለችበትን ችግር ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ እና ብፁዓን አበው በተገኙበት ለምልአተ ጉባኤው ጥያቄ የሚቀርብ እና ምላሽ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ ግቡን ማድረጉ ተገልጧል፡፡
ከመላው የሀገሪቱ ክፍል ከተቻለም ከውጭው ዓለም ያሉ የቤተክርስቲያን ሊቃውንት የሚሰባሰቡ ሲሆን በጊዜው በኒቂያ እንደተደረገው በዚህ ጉባኤም 318 ሊቃውንት የሚታደሙ እንደሆነ በመግለጫው ተገልጧል፡፡
በብፁዕ አቡነ እንድርያስ ሰብሳስቢነት የሚመራው የሊቃውንት ጉባኤ ከ 15 በላይ አባላት ያለው መሆኑ በመግለጫው ላይ ለማስታወስ ተሞክሯል፡፡
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)
<<የሊቃውንት ብዛት ለዓለም መድኃኒት ነው>>
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ታሪካዊና በዓይነቱ ልዩ የሆነ <<ዝክረ ኒቂያ>> የተሰኘ ሀገር አቀፍ የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ከሚያዚያ 20 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለማካሔድ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ የጉባኤውን ዓላማ እና ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ፋይዳ አስመልክቶ ዛሬ ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሕዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት መግለጫ በሊቃውንት ጉባኤ ተሰጥቷል፡፡
በቀደምት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥያቄዎችና የኑፋቄ ትምህርቶች ሲነሱ መልስ ለመስጠት ሊቃውንቱ ተሰባስበው ምላሽ የሚሰጡ መሆኑንና አሁንም በቤተ ክርስቲያን ላይ በነገረ ሃይማኖት እንዲሁም በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተለያዩ ኑፋቄና ቀኖናዊ ጥያቄዎች እየተነሱ በመሆኑ የሊቃውንት መሰባሰብ አስፈላጊ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡
ጉባኤው ከጥር 26-29 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለማካሄድ ታቅዶ እንቅስቃሴ ሲደረግ የቆየ ቢሆንም፡-
1ኛ) ጉባኤው በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንት የሚታደሙበት እንደመሆኑ፥ በተለይ በጠረፉ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ መምህራንን በበቂ ቊጥር ለማካተት እንዲቻል ፥ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ፤
2ኛ) በጥር ወር በርካታ ሀገራዊ ክንውኖችና ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት በየአካባቢው የሚካሄዱ በመሆናቸው የጉባኤው መካሄጃ ጊዜ እንዲስተካከል ከአንዳንድ አህጉረ ስብከት በተደጋጋሚ አስተያየት በመሰጠቱ ፤
3ኛ) ጉባኤው ከዘመናት ቆይታ በኋላ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድና በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቃሚ ውይይቶችን በማካሄድ ፥ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የሚጠቅም የውሳኔ ሐሳብና አስተያየት የሚያቀርብ ፥ አልፎም የአቋም መግለጫ የሚያወጣ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ከመካሄዱ ጥቂት ቀደም ብሎ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፥ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፥ የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች በሚገኙበት ከሚያዝያ 20-25 ቀን 2017 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሚካሄድ ይሆናል።
በጉባኤው፡- ያለውን ማጽናት፣ የጠመመውን ማቅናት፣ የጠፋውን መፈለግ፣ ሊቃውንቱን እርስ በእርስ ማስተዋወቅና ቤተክርስቲያን ያለችበትን ችግር ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ እና ብፁዓን አበው በተገኙበት ለምልአተ ጉባኤው ጥያቄ የሚቀርብ እና ምላሽ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ ግቡን ማድረጉ ተገልጧል፡፡
ከመላው የሀገሪቱ ክፍል ከተቻለም ከውጭው ዓለም ያሉ የቤተክርስቲያን ሊቃውንት የሚሰባሰቡ ሲሆን በጊዜው በኒቂያ እንደተደረገው በዚህ ጉባኤም 318 ሊቃውንት የሚታደሙ እንደሆነ በመግለጫው ተገልጧል፡፡
በብፁዕ አቡነ እንድርያስ ሰብሳስቢነት የሚመራው የሊቃውንት ጉባኤ ከ 15 በላይ አባላት ያለው መሆኑ በመግለጫው ላይ ለማስታወስ ተሞክሯል፡፡
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
በቤተክርስቲያን የአገልግሎት ሰዓት አገልጋዮች የእጅ ስልካቸውን ይዘው እንዳይገቡ መከልከሉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታወቀ !
የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
ሀገረ ስብከቱ የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ጸሐፍትና ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ቄሰ ገበዞች ጋር ባደረገው ውይይትና ስምምነት መነሻነት የተለያዩ መመሪያዎች መተላለፋቸው ተገልጿል።
ከመመሪያዎች አንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ወቅት የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ለሁሉም ገዳማትና አድባራት በተላከው የመመሪያ ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።
በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት መሠረት ቅዳሴ የሁሉም ጸሎታት ማጠናቀቂያ ፣ ቀራንዮ ላይ የምንገኝበት ፣ የበጉ ሰርግ ላይ የምንታደምበት፣ የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በአንድነት ለኃጢአት ሥርየት፣ ለነፍስ ሕይወት ፣ ለሃይማኖት ጽንዐትና ለመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ይሆነን ዘንድ የምንቀበልበት ታላቅ የጸሎት ሰዓት ነው።
በመሆኑም አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም ጎልጎታን ከሚያስረሱ በረከትን ከሚያሳጡና ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ እንደተከለከለም ተገልጿል።
ይህንን መመሪያም ለየገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ መታዘዛቸውን በተጻፈ ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።
©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
@EotcLibilery
የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
ሀገረ ስብከቱ የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ጸሐፍትና ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ቄሰ ገበዞች ጋር ባደረገው ውይይትና ስምምነት መነሻነት የተለያዩ መመሪያዎች መተላለፋቸው ተገልጿል።
ከመመሪያዎች አንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ወቅት የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ለሁሉም ገዳማትና አድባራት በተላከው የመመሪያ ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።
በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት መሠረት ቅዳሴ የሁሉም ጸሎታት ማጠናቀቂያ ፣ ቀራንዮ ላይ የምንገኝበት ፣ የበጉ ሰርግ ላይ የምንታደምበት፣ የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በአንድነት ለኃጢአት ሥርየት፣ ለነፍስ ሕይወት ፣ ለሃይማኖት ጽንዐትና ለመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ይሆነን ዘንድ የምንቀበልበት ታላቅ የጸሎት ሰዓት ነው።
በመሆኑም አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም ጎልጎታን ከሚያስረሱ በረከትን ከሚያሳጡና ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ እንደተከለከለም ተገልጿል።
ይህንን መመሪያም ለየገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ መታዘዛቸውን በተጻፈ ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።
©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
@EotcLibilery
EOTC ቤተ መጻሕፍት pinned ««ዝክረ ኒቅያ» ሀገር አቀፍ የሊቃውንት ጉባኤ ሊዘጋጅ ነው! የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ) <<የሊቃውንት ብዛት ለዓለም መድኃኒት ነው>> በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ታሪካዊና በዓይነቱ ልዩ የሆነ <<ዝክረ ኒቂያ>> የተሰኘ ሀገር አቀፍ የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ከሚያዚያ 20 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለማካሔድ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ…»
🔴 ዐቢይ ጾም || የጾም መግቢያ || ...
Enqo silassie
✝ዐቢይ ጾም || የጾም መግቢያ✝
Size:-42MB
Length:-45:22
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Size:-42MB
Length:-45:22
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ከማቴዎስ ወንጌል ጀምሮ እስከ ራእየ ዮሐንስ መጨረሻ፣ ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትን በእጃቸው የጻፉት ሊቀ ጳጳስ
<<የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው>> በሚለው ጽኑዕ አቋማቸው ይታወቃሉ፡፡ ትምህርትን አብዝተው የሚወድዱ እና ሰዎችም እንዲማሩ በብርቱ የሚደግፉ፤ ጾመ ድጓ፣ ምዕራፍ፣ ቅኔ፣ የዜማ፣ የአቋቋም፣ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪት፣ የዳዊት ትርጓሜን ፣ ሐዲሳትን፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም፣ ኪዳን፣ ትምህርተ ኅቡዓት፣ ፍትሐ ነገሥት፣ በሀገር ውስጥ ከተማሯቸው ጥቂቱ ነው፡፡
ከትግራይ እስከ አርሲ ሀገረ ስብከት ጠባቂነት በጵጵስና ደረጃ ቤተክርስቲያንን ያገለገሉበት ከፍተኛ እርከን ቢሆንም በመምህርነትም ብዙ ዓመታትን ቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግለዋል፤ በተለይ በብሥራተ ወንጌል የሬዲዮ አገልግሎታቸውን በእጅጉ ይወድዱታል ይኮሩበታልም፡፡ ከሊቃውንት ወገን የሚመደቡት፣ በአስተዳደር ዘመናቸውም ሙስሊሙን ከክርስቲያኑ አስማምተው፣ አዋድደውና አፋቅረው መርተዋል፤ የቀድሞ አባ መዐዛ ቅዱሳን የኋላው ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ካረፉ ዛሬ የካቲት 21/2017 ዓ.ም ዘጠኝ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡
ትውልዳቸው በምሥራቅ ትግራይ ክለተ አውላሎ አውራጃ አውዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጥቢያ ከአባታቸው አቶ ገብረ ሕይወት ፀዓዱ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ወለተ ክርስቶስ ቢሻው ግንቦት 12 ቀን 1923 ዓ.ም ነው፡፡ ወላጆቻቸው ልጆችን እየወለዱ በተደጋጋሚ ይሞቱባቸው ስለነበር በጭንቀት ውስጥ ሳሉ ነው ብፁዕነታቸው የተወለዱት፡፡
አባታቸው ገና በጨቅላነታቸው በመሞታቸው በእናታቸው ዘንድ በስስት እየታዩ ነው ያደጉት፡፡ ከዚህም የተነሣ ባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን ያጡት እናትም የሁሉም ምትክ የሆኑት ልጃቸውን ካሣዬ ብለው ስም አወጡላቸው፡፡ ትንሹ ካሣዬም የእናታቸውን ፍቅር ሳይጠግቡ፤ እናትም በስስት የሚመለከቱትን የልጃቸውን ስም ጠርተው በዐይናቸው አይተው ሳይጠግቡ በለጋነት ዕድሜያቸው እናታቸውን በሞት ተነጠቁ፡፡ እናታቸው በልጅነታቸው በማረፋቸው ምክንያትም ከእኅታቸው ጋራ መኖር ጀመሩ፡፡ የእኅታቸው ፍላጎት ከብት እንዲጠብቁ፣ ዕድሜያቸው ለአቅመ አዳም ሲደርስም በሕግ በትዳር ተወስነው እንዲኖሩና እያረሱ በግብርና ኑሮአቸውን እንዲገፉ ነበር፡፡
የካሣዬ ሐሳብ ደግሞ ከአድማስ ባሻገር ነበር፡፡ ይኸውም በአካባቢያቸው ባሉት አብያተ ክርስቲያናት እንደሚመለከቱት ሁሉ ከሊቃውንቱ እግር ሥር ቁጭ ብሎ መማር፣ ቤተክርስቲያንን ማገልገል፣ ጉባኤ አስፍቶ ወንበር ዘርግቶ ማስተማር ነበር ::
ብፁዕነታቸው አባቴ <<በጣም መንፈሳዊ ሰው ነበሩ፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አባታችን እያሉ ይጠሩኛል ስለእኔ ግን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ትልቅ አባት ይሆናል ብለው ይናገሩ እንደነበረ ነግረውኛል፡፡ በወቅቱ እኔ ልጅ ስለነበርኩ ይናገሩት የነበረውን አላስታውሰውም>> በማለት ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ፍላጎታቸውን ለመወጣት ወደ አለቃ መብራቴ ዘንድ በመሔድ በአቡነ አሳይ ቤተክርስቲያን ንባብና የቃል ትምህርት ጀመሩ፡፡ የኔታ ሰሎሞን የሚባሉ የአቋቋም መምህራቸው ያላቸውን የትምህርት ፍላጎት በመረዳት፤ ነገ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅሙ ሆነው ስለታዩአቸው ወደ ሌላ ሔደው እንዳይሰናከሉ በማሰብ ከእርሳቸው ዘንድ እንዲማሩ ስለሚፈልጉ ርቀው ወደ ቆሎ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ሦስት ዋስ አስጠርተዋቸው በዚያው እንዲቆዩ አደረጓቸው፡፡
በልጅነታቸው አባትና እናታቸውን ያጡት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ግን ልባቸው ለትምህርት አድልቷልና ቤተክርስቲያንን እናት፣ እግዚአብሔርን አባት አድርገው ከተወለዱበትና ከአደጉበት ወላጆቻቸውንም ካጡበት ቀዬአቸው ትምህርትን ፍለጋ ለመኮብለል ወሰኑ፡፡ ስለዚህም ተጨማሪ ትምህርት ለመቅሰም ከመምህራንና ከቤተሰቦቻቸው ተደብቀው በጥንቱ ቆሎ ተማሪ ልማድ ስማቸውን ቀይረው ጎጃም (በጌምድር) ትምህርት ፍለጋ ተሰደዱ፡፡ በቆሎ ትምህርት ቤትም መዓዛ ቅዱሳን ተብለው ተጠሩ፡፡
ወደ ጎንደር እና ጎጃም ተሻግረው ከየኔታ ኃይሉ ስሜ በየላ ኢየሱስ፣ ከየኔታ መኰንን ላስታ አመራ ማርያም ከእነዚህ ከሁለቱም ጾመ ድጓና ምዕራፍ ከተማሩ በኋላ እንደገና ወደ ቅኔ ቤት ገቡ፡፡ ክህነት የተቀበሉትም ሁለት ጊዜ ምዕራፍና ጾመ ድጓ ዘልቀው ቅኔ እስከ ዘእይዜ ከቆጠሩ በኋላ ነበር፡፡ በደቡብ ጎንደር እና ወሎ ተዘዋውረውም በጉባኤ ቤቶች የዜማ፣ የአቋቋም ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የሰሜን ጎንደር ደባርቅ ወረዳ ደረስጌ ማርያም አቅንተውም ከየኔታ መንበሩ ዘንድ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የቅኔ ዕውቀታቸውን ለማስፋፋትም ከአዲስ አበባ ስማዳ ወረዳ ደብረ ዕንቁ በማምራት ከታላቁ ሊቅ ከየኔታ ጌጡ ዘንድ ተምረዋል፡፡ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪትና ዳዊት ትርጓሜን ተምረዋል፡፡
ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመማር አዲስ አበባ በሚገኘው ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ገብተው ሐዲሳትን በመጀመሪያ ከመጋቤ ሐዲስ ወ/ሚካኤል፣ ከመ/ር ገብረ ማርያም ዓለሙ፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም ከመምህር ይኄይስ፣ ኪዳን ትምህርተ ኅቡዓት ከመምህር ከየኔታ ገብረ ማርያም፣ ከመምህርገብረ ሕይወት ፍትሐ ነገሥት ተምረዋል፡፡
ለራሳቸው እየተማሩ ከቤታቸው ያሉትን ተማሪዎች እያስተማሩ ቆይተዋል፡፡ የመጻሕፍት ተማሪ ሆነው መጻሕፍተ ሐዲሳትን እየተማሩ ሌሊት ከማቴዎስ ወንጌል ጀምሮ እስከ ራእየ ዮሐንስ መጨረሻ ድረስ እንዲሁም ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትን በእጃቸው ጽፈዋል፡፡ መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜን በቀዳማይ ኃይለ ሥላሴ ፊት እንዲተረጉሙ ተፈቅዶላቸው በሚገባ በመወጣታቸው ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ ሽልማት ተቀብለዋል፡፡
ዓላማቸው በተመረቁበት በሐዲሱ ተማሪ አብዝተው ጉባኤ አስፍተው ማስተማር ነበር፡፡ ነገር ግን በቅድስት ሥላሴ መምህራን ማሠልጠኛ እድል አግኝተው ለሁለት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡
ቅኔ ቤት ገብተው ከየኔታ መንበሩ ደረስጌ ስሜን ጃና አሞራ ገብተው ሲማሩ አንድ ዘመዳቸው “ምሰሶ ታቃፊ ሆነህ እንዳትቀር ዲቁና ተቀበል" ያላቸው ትዝ እያላቸው ዲቁና የተቀበሉት ካደጉና ከተማሩ በኋላ ነው፡፡ ይኸውም ከጎንደር ሸዋ (አዲስ አበባ) ድረስ በእግራቸው ተጉዘው በመምጣት በሚያዝያ ወር በ1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ከአቡነ ይስሐቅ ዲቁና ተቀብለዋል፡፡
አቡነ ባስልዮስ በጸመ ፍልሰታ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይዘዋቸው በመሔድም ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ ማርያም እየተረጎሙ እዚያው ከርመው ሦስቱን ታላላቅ መዓርጋት ቅስና፣ ምንኲስና ቁምስና በ1953 ዓ.ም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ተቀብለዋል፡፡
ጵጵስና ጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ለኤጲስ ቆጶስነት ከተመረጡት 13 አባቶች መካከል አንዱ ሲሆኑ፤ የትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሾሙ፡፡ በትግራይ ሀገረ ስብከትም እስከ 1975 ዓ.ም አገልግለዋል፡፡
ዘመናዊ ትምህርት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ወደፊት ጵጵስና የሚሾሙ ሰዎች ውጭ ሀገር ሔደው የውጭውን ትምህርትና ልምድ እንዲቀስሙ ያስፈልጋል በማለት ለአቡነ ባስልዮስ አሳሰቧቸው፡፡ ሊቃውንት ሲመረጡም በንጉሡ አማካይነት ተጠቁመው ውጪ ሀገር ከሚሔዱት መካከል አንዱ ሆኑ፡፡
<<የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው>> በሚለው ጽኑዕ አቋማቸው ይታወቃሉ፡፡ ትምህርትን አብዝተው የሚወድዱ እና ሰዎችም እንዲማሩ በብርቱ የሚደግፉ፤ ጾመ ድጓ፣ ምዕራፍ፣ ቅኔ፣ የዜማ፣ የአቋቋም፣ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪት፣ የዳዊት ትርጓሜን ፣ ሐዲሳትን፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም፣ ኪዳን፣ ትምህርተ ኅቡዓት፣ ፍትሐ ነገሥት፣ በሀገር ውስጥ ከተማሯቸው ጥቂቱ ነው፡፡
ከትግራይ እስከ አርሲ ሀገረ ስብከት ጠባቂነት በጵጵስና ደረጃ ቤተክርስቲያንን ያገለገሉበት ከፍተኛ እርከን ቢሆንም በመምህርነትም ብዙ ዓመታትን ቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግለዋል፤ በተለይ በብሥራተ ወንጌል የሬዲዮ አገልግሎታቸውን በእጅጉ ይወድዱታል ይኮሩበታልም፡፡ ከሊቃውንት ወገን የሚመደቡት፣ በአስተዳደር ዘመናቸውም ሙስሊሙን ከክርስቲያኑ አስማምተው፣ አዋድደውና አፋቅረው መርተዋል፤ የቀድሞ አባ መዐዛ ቅዱሳን የኋላው ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ካረፉ ዛሬ የካቲት 21/2017 ዓ.ም ዘጠኝ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡
ትውልዳቸው በምሥራቅ ትግራይ ክለተ አውላሎ አውራጃ አውዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጥቢያ ከአባታቸው አቶ ገብረ ሕይወት ፀዓዱ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ወለተ ክርስቶስ ቢሻው ግንቦት 12 ቀን 1923 ዓ.ም ነው፡፡ ወላጆቻቸው ልጆችን እየወለዱ በተደጋጋሚ ይሞቱባቸው ስለነበር በጭንቀት ውስጥ ሳሉ ነው ብፁዕነታቸው የተወለዱት፡፡
አባታቸው ገና በጨቅላነታቸው በመሞታቸው በእናታቸው ዘንድ በስስት እየታዩ ነው ያደጉት፡፡ ከዚህም የተነሣ ባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን ያጡት እናትም የሁሉም ምትክ የሆኑት ልጃቸውን ካሣዬ ብለው ስም አወጡላቸው፡፡ ትንሹ ካሣዬም የእናታቸውን ፍቅር ሳይጠግቡ፤ እናትም በስስት የሚመለከቱትን የልጃቸውን ስም ጠርተው በዐይናቸው አይተው ሳይጠግቡ በለጋነት ዕድሜያቸው እናታቸውን በሞት ተነጠቁ፡፡ እናታቸው በልጅነታቸው በማረፋቸው ምክንያትም ከእኅታቸው ጋራ መኖር ጀመሩ፡፡ የእኅታቸው ፍላጎት ከብት እንዲጠብቁ፣ ዕድሜያቸው ለአቅመ አዳም ሲደርስም በሕግ በትዳር ተወስነው እንዲኖሩና እያረሱ በግብርና ኑሮአቸውን እንዲገፉ ነበር፡፡
የካሣዬ ሐሳብ ደግሞ ከአድማስ ባሻገር ነበር፡፡ ይኸውም በአካባቢያቸው ባሉት አብያተ ክርስቲያናት እንደሚመለከቱት ሁሉ ከሊቃውንቱ እግር ሥር ቁጭ ብሎ መማር፣ ቤተክርስቲያንን ማገልገል፣ ጉባኤ አስፍቶ ወንበር ዘርግቶ ማስተማር ነበር ::
ብፁዕነታቸው አባቴ <<በጣም መንፈሳዊ ሰው ነበሩ፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አባታችን እያሉ ይጠሩኛል ስለእኔ ግን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ትልቅ አባት ይሆናል ብለው ይናገሩ እንደነበረ ነግረውኛል፡፡ በወቅቱ እኔ ልጅ ስለነበርኩ ይናገሩት የነበረውን አላስታውሰውም>> በማለት ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ፍላጎታቸውን ለመወጣት ወደ አለቃ መብራቴ ዘንድ በመሔድ በአቡነ አሳይ ቤተክርስቲያን ንባብና የቃል ትምህርት ጀመሩ፡፡ የኔታ ሰሎሞን የሚባሉ የአቋቋም መምህራቸው ያላቸውን የትምህርት ፍላጎት በመረዳት፤ ነገ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅሙ ሆነው ስለታዩአቸው ወደ ሌላ ሔደው እንዳይሰናከሉ በማሰብ ከእርሳቸው ዘንድ እንዲማሩ ስለሚፈልጉ ርቀው ወደ ቆሎ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ሦስት ዋስ አስጠርተዋቸው በዚያው እንዲቆዩ አደረጓቸው፡፡
በልጅነታቸው አባትና እናታቸውን ያጡት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ግን ልባቸው ለትምህርት አድልቷልና ቤተክርስቲያንን እናት፣ እግዚአብሔርን አባት አድርገው ከተወለዱበትና ከአደጉበት ወላጆቻቸውንም ካጡበት ቀዬአቸው ትምህርትን ፍለጋ ለመኮብለል ወሰኑ፡፡ ስለዚህም ተጨማሪ ትምህርት ለመቅሰም ከመምህራንና ከቤተሰቦቻቸው ተደብቀው በጥንቱ ቆሎ ተማሪ ልማድ ስማቸውን ቀይረው ጎጃም (በጌምድር) ትምህርት ፍለጋ ተሰደዱ፡፡ በቆሎ ትምህርት ቤትም መዓዛ ቅዱሳን ተብለው ተጠሩ፡፡
ወደ ጎንደር እና ጎጃም ተሻግረው ከየኔታ ኃይሉ ስሜ በየላ ኢየሱስ፣ ከየኔታ መኰንን ላስታ አመራ ማርያም ከእነዚህ ከሁለቱም ጾመ ድጓና ምዕራፍ ከተማሩ በኋላ እንደገና ወደ ቅኔ ቤት ገቡ፡፡ ክህነት የተቀበሉትም ሁለት ጊዜ ምዕራፍና ጾመ ድጓ ዘልቀው ቅኔ እስከ ዘእይዜ ከቆጠሩ በኋላ ነበር፡፡ በደቡብ ጎንደር እና ወሎ ተዘዋውረውም በጉባኤ ቤቶች የዜማ፣ የአቋቋም ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የሰሜን ጎንደር ደባርቅ ወረዳ ደረስጌ ማርያም አቅንተውም ከየኔታ መንበሩ ዘንድ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የቅኔ ዕውቀታቸውን ለማስፋፋትም ከአዲስ አበባ ስማዳ ወረዳ ደብረ ዕንቁ በማምራት ከታላቁ ሊቅ ከየኔታ ጌጡ ዘንድ ተምረዋል፡፡ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪትና ዳዊት ትርጓሜን ተምረዋል፡፡
ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመማር አዲስ አበባ በሚገኘው ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ገብተው ሐዲሳትን በመጀመሪያ ከመጋቤ ሐዲስ ወ/ሚካኤል፣ ከመ/ር ገብረ ማርያም ዓለሙ፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም ከመምህር ይኄይስ፣ ኪዳን ትምህርተ ኅቡዓት ከመምህር ከየኔታ ገብረ ማርያም፣ ከመምህርገብረ ሕይወት ፍትሐ ነገሥት ተምረዋል፡፡
ለራሳቸው እየተማሩ ከቤታቸው ያሉትን ተማሪዎች እያስተማሩ ቆይተዋል፡፡ የመጻሕፍት ተማሪ ሆነው መጻሕፍተ ሐዲሳትን እየተማሩ ሌሊት ከማቴዎስ ወንጌል ጀምሮ እስከ ራእየ ዮሐንስ መጨረሻ ድረስ እንዲሁም ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትን በእጃቸው ጽፈዋል፡፡ መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜን በቀዳማይ ኃይለ ሥላሴ ፊት እንዲተረጉሙ ተፈቅዶላቸው በሚገባ በመወጣታቸው ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ ሽልማት ተቀብለዋል፡፡
ዓላማቸው በተመረቁበት በሐዲሱ ተማሪ አብዝተው ጉባኤ አስፍተው ማስተማር ነበር፡፡ ነገር ግን በቅድስት ሥላሴ መምህራን ማሠልጠኛ እድል አግኝተው ለሁለት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡
ቅኔ ቤት ገብተው ከየኔታ መንበሩ ደረስጌ ስሜን ጃና አሞራ ገብተው ሲማሩ አንድ ዘመዳቸው “ምሰሶ ታቃፊ ሆነህ እንዳትቀር ዲቁና ተቀበል" ያላቸው ትዝ እያላቸው ዲቁና የተቀበሉት ካደጉና ከተማሩ በኋላ ነው፡፡ ይኸውም ከጎንደር ሸዋ (አዲስ አበባ) ድረስ በእግራቸው ተጉዘው በመምጣት በሚያዝያ ወር በ1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ከአቡነ ይስሐቅ ዲቁና ተቀብለዋል፡፡
አቡነ ባስልዮስ በጸመ ፍልሰታ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይዘዋቸው በመሔድም ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ ማርያም እየተረጎሙ እዚያው ከርመው ሦስቱን ታላላቅ መዓርጋት ቅስና፣ ምንኲስና ቁምስና በ1953 ዓ.ም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ተቀብለዋል፡፡
ጵጵስና ጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ለኤጲስ ቆጶስነት ከተመረጡት 13 አባቶች መካከል አንዱ ሲሆኑ፤ የትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሾሙ፡፡ በትግራይ ሀገረ ስብከትም እስከ 1975 ዓ.ም አገልግለዋል፡፡
ዘመናዊ ትምህርት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ወደፊት ጵጵስና የሚሾሙ ሰዎች ውጭ ሀገር ሔደው የውጭውን ትምህርትና ልምድ እንዲቀስሙ ያስፈልጋል በማለት ለአቡነ ባስልዮስ አሳሰቧቸው፡፡ ሊቃውንት ሲመረጡም በንጉሡ አማካይነት ተጠቁመው ውጪ ሀገር ከሚሔዱት መካከል አንዱ ሆኑ፡፡
አባ መዓዛ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ትምህርት በቂ ችሎታ አላቸው ከሚባሉ መምህራን አንዱ ናቸው፡፡ እኒህ የቤተክርስቲያን ሊቅ ዕውቀታቸውን በበለጠ በዓለም ዐቀፍ ቋንቋ ለማሻሻል ባላቸው ፍላጎት መሠረት ወደ ኢየሩሳሌም አንግሊካን ቤተክርስቲያን ሴንት ጆርጅ ኮሌጅ ተላኩ፡፡ ወደፊት ጵጵስና የሚሾም ብለው ጃንሆይ በተናገሩት መሠረት የኤጲስ ቆጶስነት ትምህርት እንዲሠለጥኑ ነበር የተላኩት፡፡ ሁለት ዓመት ተኩል የቤተክርስቲያን አስተዳደር (Church History and Administration) ተምረው ተመለሱ፡፡ ከውጭ ሀገር እንደተመለሱ ከ1951-1960 ዓ.ም በተማሩት ትምህርት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካህናት አስተዳደሪ ሆነው ቤተክርስቲያንን በማገልገል ምእመናንን በማስተማር ሐዋርያዊ ግዴታቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡
በዚሁ መካከል በ1958 ዓ.ም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል፡፡ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው እንኳን በበጎ ፈቃደኝነት ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም እየተመላለሱ ያስተምሩ ነበር፡፡ በኋላም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ወደ እንግሊዝ ሀገር ኦክስፎርድ ኦስሄትሮፕ የሚባል የካቶሊክ ኮሌጅ በ1961 ዓ.ም ተልከው በእንግሊዝ ሀገር ለአራት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው (Bachelor of Divinity in Basic Philosophy Super mental and Developmental Psychology) ዲግሪ ተቀብለው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ከሀገርና ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን ታላቅ አደራ አክብረው ሀገራቸውን ለማገልገል በውጭ ሀገር የቀሰሙትን ሥልጣኔና ልምድ ለሀገራቸው የሚያውሉ ምሁራን በርካታ ናቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ካፈራቻቸው ሊቃውንት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በምዕራቡ ዓለም በትምህርት ቆይታቸው በትምህርትና በልምድ ያካበቱትን ዕውቀት በተግባር ላይ ለማዋል የቻሉ ምሁር ናቸው፡፡ በዚህም መነሻ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ የሰበታ ቤተ ደናግል የበላይ ኀላፊና የቦርድ አባል ሆነው አገልግለዋል፡፡ በባሕል ሚኒስቴርም በቋንቋ ጥናት አካዳሚ ውስጥ መርሐ ልሳን ተብሎ በሚታወቀው ክፍል በመምህርነት ሠርተዋል፡፡
በተፈሪ መኰንን ት/ቤት ውስጥ ከውጭ ሀገር በልዩ ልዩ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ኢየሱሳውያን ያስተምሩ ስለነበር ብዙ ጊዜ የሃይማኖት ግጭት ይፈጠር ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ተማሪዎች በመንፈሳዊ ዕውቀታቸው ጠንካሮች ስለነበሩ በሚያቀርቡት ጥያቄ በተማሪዎቹና በመምህራን መካካልም በየጊዜው ግጭት ይፈጠራል፡፡ ዐፄ ኃይለ ሥላሴም ጉዳዩን ሲያጣሩ የግብረ ገብነት መምህር እንደሌላቸው በተማሪዎቹ ስለተነገራቸው በአባ ሐና አቅራቢነት በዚያን ጊዜ ስማቸው አባ መዐዛ ቅዱሳን ወደ ጃንሆይ ቀርበው በግብረ ገብ መምህርነት እንዲቀጠሩ ስለፈቀዱ ለተፈሪ መኮንን ት/ቤት የግብረ ገብ መምህር ሆነው ተቀጥረው ከ1949 ዓ.ም እስከ 1954ዓ.ም ድረስ በግብረ ገብነት አስተማሪነታቸው አገልግለዋል፡፡
ብፁዕነታቸው በተፈሪ መኮንን ት/ቤት እያስተማሩ የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም በተጓዳኝ በትምህርት ቤቱ ግብረ ገብ የሚያስተምሯቸውን ተማሪዎች ሰፋ ያለ የሃይማኖት ትምህርት የሚቀስሙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ሲሉ በምስካዬ ኅዙናን መድኃ ኔዓለም ገዳም ወጣቶችን ስለሃይማኖት ማስተማር ጀመሩ፡፡ የዚህ አገልግሎት ፍጻሜም አንጋፋውን የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት ለመመሥረት አብቅቶታል፡፡ ብፁዕነታቸውም የዚህ ሰንበት ት/ቤት ከመሥራቾቹ አባላት አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በወቅቱ ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ቋሚ ሰባኬ ወንጌል በመሆንም አገልግለዋል፡፡
ቅድስት ቤተክርስቲያን በሬዲዮ ትምህርት በምታስተምርበት ወቅት፤ አባ መዐዛ ቅዱሳን (በኋላ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል) በርቱዕ አንደበታቸው በብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ “ማኅበራዊ ኑሮ በቤተክርስቲያን'' እና “የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት” በተሰኙ አርእስተ ትምህርት ይሰጡ ነበር፡፡ ብፁዕነታቸው በሕይወት ዘመናቸው ካከናወኗቸው ተግባራት ለምእመናን በሬዲዮ ስብከተ ወንጌልን በማስተላለፍ የሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገሩ ነበር፡፡
በአርሲ ሀገረ ስብከት ከ1975 ዓ.ም ጀምሮ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ33 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት ቆይታቸውም በምእመናን የሚወደዱና የሚከበሩ ታላቅ አባት ነበሩ፡፡ ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት በመጡበት የመጀመሪያ ሳምንታት ውስጥ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ያሉትን ዐበይት ችግሮች ካጠኑ በኋላ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ አንድም የወጣቶች እንቅስቃሴ የሚደረግበት አጥቢያ አለመኖሩንና ሰንበት ት/ቤቶችም የተዘጉና ወጣቶችም በቤተክርስቲያን አካባቢ እንዳይታዩና ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር ይደረግባቸው እንደነበረ ካወቁ በኋላ <<የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው>> በማለት አቋማቸውን በአደባባይ ከመግለጻቸውም በላይ በዘመኑ በሥልጣን ላይ ከነበሩት የደርግ ሹማምንት ፊት ለፊት በመጋፈጥ ልጆቻቸውን ከጥቃት ታድገዋል፤ ተቋርጦ የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት እንዲቀጥል አድርገዋል፡፡
ብፁዕነታቸው የነገይቱ ቤተክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች መሆናቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁ ስለሆነ በሀገረ ስብከታቸው ውስጥ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ለወጣቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲጠናከሩ አድርገዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት ተመድበው ሲመጡ የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር 117 (አንድ መቶ አሥራ ሰባት) ብቻ የነበሩ ሲሆን እርሳቸው በሕይወት በነበሩባቸው ዘመናት ከ300 (ሦስት መቶ) በላይ አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትን በማስከተል ምእመናን በርቀት ምክንያት ሳይንገላቱ በአቅራቢያቸው ከቤተክርስቲያን አገልግሎት ተሳትፎ እንዲኖራቸው ከማድረጋቸውም በላይ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዕረፍት ምክንያት ከነሐሴ ወር 2004 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተመርጠው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሆነው እስከተሾሙበት የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ በዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክነት ቅድስት ቤተክርስቲያን በመምራት አባታዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል፡፡
ብፁዕነታቸው ባደረባቸው ሕመም ምክንያት የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም ልክ በዛሬዋ ቀን ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ዐርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው የካቲት 24 ቀን 2008 ዓ.ም በደብር ቅዱስ ደብረ መዓዛ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ተፈጽሟል፡፡
የብፁዕ አባታችን በረከታቸው ይደርብን፡፡
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
በዚሁ መካከል በ1958 ዓ.ም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል፡፡ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው እንኳን በበጎ ፈቃደኝነት ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም እየተመላለሱ ያስተምሩ ነበር፡፡ በኋላም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ወደ እንግሊዝ ሀገር ኦክስፎርድ ኦስሄትሮፕ የሚባል የካቶሊክ ኮሌጅ በ1961 ዓ.ም ተልከው በእንግሊዝ ሀገር ለአራት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው (Bachelor of Divinity in Basic Philosophy Super mental and Developmental Psychology) ዲግሪ ተቀብለው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ከሀገርና ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን ታላቅ አደራ አክብረው ሀገራቸውን ለማገልገል በውጭ ሀገር የቀሰሙትን ሥልጣኔና ልምድ ለሀገራቸው የሚያውሉ ምሁራን በርካታ ናቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ካፈራቻቸው ሊቃውንት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በምዕራቡ ዓለም በትምህርት ቆይታቸው በትምህርትና በልምድ ያካበቱትን ዕውቀት በተግባር ላይ ለማዋል የቻሉ ምሁር ናቸው፡፡ በዚህም መነሻ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ የሰበታ ቤተ ደናግል የበላይ ኀላፊና የቦርድ አባል ሆነው አገልግለዋል፡፡ በባሕል ሚኒስቴርም በቋንቋ ጥናት አካዳሚ ውስጥ መርሐ ልሳን ተብሎ በሚታወቀው ክፍል በመምህርነት ሠርተዋል፡፡
በተፈሪ መኰንን ት/ቤት ውስጥ ከውጭ ሀገር በልዩ ልዩ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ኢየሱሳውያን ያስተምሩ ስለነበር ብዙ ጊዜ የሃይማኖት ግጭት ይፈጠር ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ተማሪዎች በመንፈሳዊ ዕውቀታቸው ጠንካሮች ስለነበሩ በሚያቀርቡት ጥያቄ በተማሪዎቹና በመምህራን መካካልም በየጊዜው ግጭት ይፈጠራል፡፡ ዐፄ ኃይለ ሥላሴም ጉዳዩን ሲያጣሩ የግብረ ገብነት መምህር እንደሌላቸው በተማሪዎቹ ስለተነገራቸው በአባ ሐና አቅራቢነት በዚያን ጊዜ ስማቸው አባ መዐዛ ቅዱሳን ወደ ጃንሆይ ቀርበው በግብረ ገብ መምህርነት እንዲቀጠሩ ስለፈቀዱ ለተፈሪ መኮንን ት/ቤት የግብረ ገብ መምህር ሆነው ተቀጥረው ከ1949 ዓ.ም እስከ 1954ዓ.ም ድረስ በግብረ ገብነት አስተማሪነታቸው አገልግለዋል፡፡
ብፁዕነታቸው በተፈሪ መኮንን ት/ቤት እያስተማሩ የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም በተጓዳኝ በትምህርት ቤቱ ግብረ ገብ የሚያስተምሯቸውን ተማሪዎች ሰፋ ያለ የሃይማኖት ትምህርት የሚቀስሙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ሲሉ በምስካዬ ኅዙናን መድኃ ኔዓለም ገዳም ወጣቶችን ስለሃይማኖት ማስተማር ጀመሩ፡፡ የዚህ አገልግሎት ፍጻሜም አንጋፋውን የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት ለመመሥረት አብቅቶታል፡፡ ብፁዕነታቸውም የዚህ ሰንበት ት/ቤት ከመሥራቾቹ አባላት አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በወቅቱ ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ቋሚ ሰባኬ ወንጌል በመሆንም አገልግለዋል፡፡
ቅድስት ቤተክርስቲያን በሬዲዮ ትምህርት በምታስተምርበት ወቅት፤ አባ መዐዛ ቅዱሳን (በኋላ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል) በርቱዕ አንደበታቸው በብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ “ማኅበራዊ ኑሮ በቤተክርስቲያን'' እና “የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት” በተሰኙ አርእስተ ትምህርት ይሰጡ ነበር፡፡ ብፁዕነታቸው በሕይወት ዘመናቸው ካከናወኗቸው ተግባራት ለምእመናን በሬዲዮ ስብከተ ወንጌልን በማስተላለፍ የሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገሩ ነበር፡፡
በአርሲ ሀገረ ስብከት ከ1975 ዓ.ም ጀምሮ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ33 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት ቆይታቸውም በምእመናን የሚወደዱና የሚከበሩ ታላቅ አባት ነበሩ፡፡ ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት በመጡበት የመጀመሪያ ሳምንታት ውስጥ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ያሉትን ዐበይት ችግሮች ካጠኑ በኋላ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ አንድም የወጣቶች እንቅስቃሴ የሚደረግበት አጥቢያ አለመኖሩንና ሰንበት ት/ቤቶችም የተዘጉና ወጣቶችም በቤተክርስቲያን አካባቢ እንዳይታዩና ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር ይደረግባቸው እንደነበረ ካወቁ በኋላ <<የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው>> በማለት አቋማቸውን በአደባባይ ከመግለጻቸውም በላይ በዘመኑ በሥልጣን ላይ ከነበሩት የደርግ ሹማምንት ፊት ለፊት በመጋፈጥ ልጆቻቸውን ከጥቃት ታድገዋል፤ ተቋርጦ የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት እንዲቀጥል አድርገዋል፡፡
ብፁዕነታቸው የነገይቱ ቤተክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች መሆናቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁ ስለሆነ በሀገረ ስብከታቸው ውስጥ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ለወጣቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲጠናከሩ አድርገዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት ተመድበው ሲመጡ የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር 117 (አንድ መቶ አሥራ ሰባት) ብቻ የነበሩ ሲሆን እርሳቸው በሕይወት በነበሩባቸው ዘመናት ከ300 (ሦስት መቶ) በላይ አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትን በማስከተል ምእመናን በርቀት ምክንያት ሳይንገላቱ በአቅራቢያቸው ከቤተክርስቲያን አገልግሎት ተሳትፎ እንዲኖራቸው ከማድረጋቸውም በላይ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዕረፍት ምክንያት ከነሐሴ ወር 2004 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተመርጠው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሆነው እስከተሾሙበት የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ በዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክነት ቅድስት ቤተክርስቲያን በመምራት አባታዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል፡፡
ብፁዕነታቸው ባደረባቸው ሕመም ምክንያት የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም ልክ በዛሬዋ ቀን ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ዐርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው የካቲት 24 ቀን 2008 ዓ.ም በደብር ቅዱስ ደብረ መዓዛ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ተፈጽሟል፡፡
የብፁዕ አባታችን በረከታቸው ይደርብን፡፡
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery