tgoop.com/HISCULHEROFETHIOPIA/5698
Create:
Last Update:
Last Update:
❮❮ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ ገነዝዎ ለኢየሱስ - ዮሴፍ ኒቆዲሞስም ጌታችን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን ገነዙት ❯❯
📜 ወንጌለ ማቴዎስ 27 📜
⁵⁷ በመሸም ጊዜ ዮሴፍ የተባለው ባለ ጠጋ ሰው ከአርማትያስ መጣ፥ እርሱም ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ፤
⁵⁸ ይኸውም ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
⁵⁹ ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥
⁶⁰ ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ።
⁶¹ መግደላዊት ማርያምም ሁለተኛይቱም ማርያም በመቃብሩ አንጻር ተቀምጠው በዚያ ነበሩ።
⁶² በማግሥቱም ከመዘጋጀት በኋላ በሚሆነው ቀን፥ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ወደ ጲላጦስ ተሰበሰቡና፦
⁶³ ጌታ ሆይ፥ ያ አሳች በሕይወቱ ገና ሳለ፦ ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ እንዳለ ትዝ አለን።
⁶⁴ እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው በሌሊት እንዳይሰርቁት ለሕዝቡም፦ ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ፥ የኋለኛይቱ ስሕተት ከፊተኛይቱ ይልቅ የከፋች ትሆናለችና መቃብሩ እስከ ሦስተኛ ቀን ድረስ እንዲጠበቅ እዘዝ አሉት።
⁶⁵ ጲላጦስም፦ ጠባቆች አሉአችሁ፤ ሄዳችሁ እንዳወቃችሁ አስጠብቁ አላቸው።
⁶⁶ እነርሱም ሄደው ከጠባቆች ጋር ድንጋዩን አትመው መቃብሩን አስጠበቁ።
BY ኢትዮጵያ
![](https://photo2.tgoop.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/tw8AJrVOh11Xajcf29ZAvQPthKr8YmAyGtbNmoL6wrkfEIyD1-ISDTqfzDqUz4B4_y1zlgDmMDLTt26e0NIb3-GD8SUOvbQlS4Yjulf4HVYPGuFQ9VfLr8x-SgJa9nREPuuQb_sPHKZQus_FwaU53CeRXS-hDBH1QrgEzdbG23UPUw3cXCvGEifDz_PL7U4wfvq3ApOS4HvS8bcwjHrh_Ran2ftc1oBB78SRsMdpE5c9zpH-AkD_4EYVCIAw5E4So6fdhut56II4QYFfDBDrg4mIJLk9asBI04Zkhs02mQhC0gqeh2_-zyy5UB4un4otPeLaEAskZGO9oo1xUpe79g.jpg)
Share with your friend now:
tgoop.com/HISCULHEROFETHIOPIA/5698