Telegram Web
ግብፅ ያቀረበችውን ጥያቄ የናይል ተፋሰስ አባል ሀገራት በሙሉ ውድቅ አደረጉ

ግብፅ የናይል ተፋሰስ አባል ሀገራት በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ጉብኝት እንዳያደርጉ በደብዳቤ ብትጠይቅም፣ አንድም ሀገር ጥያቄዋን እንዳልተቀበለ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ግብፅ ያቀረበችው ጥያቄ አግባብነት የሌለውና ለሌሎች የተፋሰስ ሀገራት ንቀት የተሞላበት ነው። የተፋሰሱ አባል ሀገራት ሚኒስትሮች የህዳሴ ግድቡን በጋራ መጎብኘታቸው ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት ሲሆን፣ ግብፅ በራሷ ላይ ግብ አስቆጥራለች ብለዋል።

ጉብኝቱ ሚኒስትሮቹ ስለ ግድቡ የነበራቸውን የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲያስተካክሉና የግብፅን ሐሰተኛ ፕሮፓጋንዳ እንዲረዱ አድርጓቸዋል።

በተጨማሪም፣ ለቀጣይ የግብፅ ንግግሮች ማስተማሪያ እንደሆነና ሁሉም ሚኒስትሮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሩስያ ሞስኮ ጉብኝት ስምምነት ሲደረስ ጉብኝት ሊያደርጉ እንደሚችሉ ገልጸዋል

ወደ ሞስኮ በትክክለኛው ሰዓት አቀናለሁ ያሉት ፕሬዝዳንቱ ትክክለኛ ጊዜ የሚሆነው የሩስያ እና ዩክሬን የሚጠናቀቅበት ወቅት እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡

ትራምፕ ጦርነቱ በሳምንታት ውስጥ ሊቆም እንደሚችል ገልጸው በሞስኮ እና ኪየቭ መካከል የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ በሩስያ ጉብኝት ሊያደርጉ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡

ከሰሞኑ በዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ላይ በሰነዘሩት ከፍተኛ ትችት ከአውሮፓ እና ከዩክሬን ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማቸው ፕሬዝዳንቱ ከፈረንዳዩ ፕሬዝዳንት ጋር በትላንትናው ዕለት በዋሽንግተን ተገናኝተዋል፡፡

በነጩ ቤተ መንግስት ከኢማኑኤል ማክሮን ጋር ባደረጉት ውይይት የአውሮፓ የሰላም አስከባሪ ጦር በዩክሬን መሰማራት የሚኖረውን ጠቀሜታ ከማክሮን ማብራርያ ተደርጎላቸዋል፡፡

የአውሮፓውያንን የዩክሬን የሰላም እቅድ ያቀረቡት ማክሮን የአውሮፓ ጦር መሰማራት የሰላም ስምምነቱን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ያለውን ወሳኝነት ገልጸዋል፡፡
ብሔራዊ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት መሰረት፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደረገ።

በዚህ ጨረታ 27 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ መኖሩን ገልጿል። ባንኩ አክሎም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።

ይህ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የገንዘብ ገበያውን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሪ ተገኝነትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ትግበራ ከገባ ካለፈው ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አንስቶ የአሁን የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጨረታ ሲወጣ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል ።

በዚህም በመጀመሪያዉ ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን እና 27 ባንኮች በጨረታው ላይ መሳተፋቸውን ገልፆ ነበር።

via Capital newspaper
በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሳተፉ ከባድ ቅጣት ተጣለባቸው

ባለፉት ስድስት ወራት በፌደራልና በክልል ደረጃዎች ከ1,000 በላይ የሰዎችን ዝውውር እና የስደተኞች ንግድ ጉዳዮች ተመርምረዋል ።

በዚሁ መሰረት በትግራይ ክልል ብቻ ከ700 በላይ ጉዳዮች ተጣርተዋል። ከ800 በላይ ጉዳዮች ለፍርድ ቀርበው በህገ ወንጀል የተሳተፉ ግለሰቦች ከ5 አመት እስከ እድሜ ልክ ፅኑ እስራት መቀጣታቸውን ሁሌ አዲስ ሚዲያ ሰምቷል።

በተጨማሪም 176,000 ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ወደተለያዩ ሀገራት በህጋዊ መንገድ የተላኩ ሲሆን 29,531 ስደተኞች ከተለያዩ ሀገራት ተመልሰው ከመጡ በኋላ አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸዋል ተብሏል።

በዚህ ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ከዳያስፖራው 2.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ገቢ ማግኘቷ ተገልጿል ።
የእግድ የተጣለባቸው የሩሲያ ንብረቶች ወደ ዩክሬን አይተላለፉም ተባለ

ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ስፔን እና የአውሮፓ ህብረት ፕሬዝደንት ሀሳቡን ተቃውመዋል

'ይህ እርምጃ ዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን የሚያሸሽ እና የአውሮፓ ህብረትን አቋም ሊያዳክም የሚችል ነው' ሲሉ የአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናት ተቃውሟቸውን አሰምተዋል
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
በኢትዮጵያ ውስጥ 10 እጅግ የናጠጡ ሀብታሞች እነማን ናቸው ?

ቢሊየነርስ አፍሪካ እንደገለፀው ግብፅ፣ ናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ በቢሊዮን የሚቆጠር ሀብት ያላቸው ባለሀብቶችን ማፍራት የቻሉ ቢሆንም ኢትዮጵያ ግን ያላት ቢሊየነር አንድ ብቻ ነው፡፡

እሳቸውም ሼክ መሀመድ አልአሙዲ ናቸው፡፡ ይሁንና እሳቸውን በመከተል ትልቅ የቢዝነስ ኤምፓየር የገነቡ፣ ለበርካቶች ስራ የፈጠሩ፣ ኢንዱስትሪዎችን የሚመሩና በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ተፅእኖ መፍጠር የሚችሉ በርካታ ሚሊየነሮች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ ዘገባው አስረድቷል፡፡

ዛሬ ለንባብ በበቃው በዚህ ዝርዝር ውስጥ አልአሙዲ በቁጥር አንድነት የተቀመጡ ሲሆን የሀብታቸው መጠን 9.56 ቢሊዮን ዶላር መሆኑ ተገልጿል፡፡

በሁለተኝነት የተቀመጡት አቶ ሳሙኤል ታፈሰ ናቸው፡፡ የሳንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ሳሙኤል በኮንስትራክሽን ዘርፍ ተሰማርተው ከአምስት ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችንና የንግድ ህንፃዎችን መገንባታቸውንና በሺህ የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትር መንገዶችን መስራታቸውን ዘገባው ጠቅሷል፡፡ ጨምሮም በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ አገር በቀል ድርጅቶች ቀዳሚው ሰንሻይን መሆኑን ገልፆ የድርጅታቸው አመታዊ ገቢ ከአንድ መቶ ሚሊዮን ዶላር እንደሚበልጥ አስረድቷል፡፡

በቢሊየነርስ አፍሪካ በዚህ ዝርዝር በሶስተኛነት የተቀመጡት አቶ በላይነህ ክንዴ ናቸው፡፡ ከአንድ ሺህ ዶላር በሚያንስ ካፒታል ቅቤና ማር በመሸጥ ስራ የጀመሩት አቶ በላይነህ በአሁኑ ወቅት በላይነህ ክንዴ ግሩፕ የተሰኘ ግዙፍ ተቋም ለመመስረት መቻላቸውን ያስረዳው ዘገባው ድርጅታቸው ባለፉት አስራ ሰባት አመታት ወደስድስት መቶ ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን ጠቅሷል፡፡

በአራተኛ ደረጃ የተቀመጡት ደግሞ አቶ ቴዎድሮስ አሸናፊ ናቸው፡፡ አቶ ቴዎድሮስ ከሀይል አቅርቦት እስከ ሸቀጣ ሸቀጥና ሪል ስቴት ዘርፍ ባሉ ስራዎች ላይ መሰማራታቸውን የጠቀሰው ዘገባው ሳውዝ ዌስት ኢነርጂ የተሰኘ ድርጅት እንዳላቸውም አስረድቷል፡፡ አቶ ቴዎድሮስ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው የማእድን ውሀ ማለት አምቦ ውሀ ባለቤት መሆናቸውን ያስረዳው መፅሄቱ በተለያዩ አለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ የቦርድ አባል መሆናቸውንም አስታውቋል፡፡

መፅሄቱ በአምስተኛ ደረጃ ያስቀመጣቸው አቶ እዮብ ማሞ ናቸው፡፡ አቶ እዮብ በዋሽንግተን ዲሲና ኒውዮርክ  ከተሞች ውስጥ በርካታ የነዳጅ ማደያዎች እንዳላቸውና በቨርጂኒያ የሪል ስቴት ዘርፍ ላይ መሰማራታቸውንም አስታውቋል፡፡ በቀጣይነት የተቀመጡት አቶ ከተማ ከበደ፣ አቶ አለማየሁ ከተማ፣ አቶ ብዙአየሁ ቢዘኑ፣ አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴና አቶ ግርማ ዋቄ ናቸው፡፡

ምንጭ : ዘሃበሻ
አፍሪካ ቢዝነስ ኢንሳይደር በየካቲት 2025 ዝቅተኛ የነዳጅ ዋጋ ያላቸው 10 ምርጥ የአፍሪካ ሀገራትን ይፋ አድርጓል

• ኢትዮጵያ ነዳጅ በዝቅተኛ ዋጋ ከሚሸጡ 10ሩ የአፍሪካ ሀገራት ሰባተኛዋ ናት ተብሏል

አፍሪካ ቢዝነስ ኢንሳይደር በየካቲት ወር ዝቅተኛ የነዳጅ ዋጋ ያላቸው 10 ምርጥ የአፍሪካ ሀገራትን በዘገባው ይዞ ወጥቷል።

እንደ አፍሪካ ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘገባ ሊቢያ ከአፍሪካ ዝቅተኛ የነዳጅ ዋጋ ያለባት ሀገር በመሆን አንደኛ ስትሆን፤ አንጎላና ግብጽ ሁለተኛና ሦስተኛ በመሆን እንደሚከታተሉ ታውቋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የነዳጅ ዋጋ ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት ሰባተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝም ዘገባው አስታውቋል።

ከአንድ እስከ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ያለሁት ሀገራት በቅደም ተከተላቸው ከዓለም በሁለት፣ አራተኛ እና አምስተኛ ደረጃ ላይ ናቸው።

ኢትዮጵያ ከዓለለም 27ኛ ናት ።
የዩናይትድ ስቴትስ ዳኛ ትራምፕ ኤፒ የዜና ተቋም ከዋይት ሃውስ እንዳይዘግብ የጣሉትን ገደብ አፀና

አሶሽየትድ ፕሬስ (ኤፒ) የዜና ተቋም በዘገባዎቹ የሜክሲኮ ባህረሰላጤ የሚለውን ስያሜ መጠቀም በመቀጠሉ በዋይት ሀውስ ተገኝቶ እንዳይዘግብ በፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የተጣለበት ገደብ እንዲነሳለት ያቀረበው ጥያቄ በአንድ ፌደራል ዳኛ ውድቅ ተደረገ።

በፕሬዝደንት ትራምፕ የተሰየሙት የዩናይትድ ስቴትስ ፍርድ ቤት ዳኛ ትሬቨር ሚክፋደን፣ ኤፒ የፍርድ ሂደቱ እስኪጠናቀቅ" ኦቫል ኦፊስ" በተሰኘው የፕሬዝደንቱ ጽሕፈት ቤት ፣ በፕሬዝደንቱ አውሮፕላን (ኤር ፎርስ ዋን) እና ሌሎች በዋይት ሀውስ የሚከናወኑ ዝግጅቶች ላይ ተገኝቶ የመዘገብ መብቱ እንዲመለስ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል።

ቪኦኤ እንደዘገበዉ ሚክፋደን በውሳኔያቸው ፕሬዝዳንቱ "ግላዊ በኾኑ አካባቢዎች" ላይ የጣሉት ገደብ፣ ከዚህ ቀደም ፍርድቤቶች የመንግሥት ባለሥልጣናት በጋዜጠኞች ላይ የተጣሉትን ገደቦችን ካነሱባቸው ሁኔታዎች የተለየ ነው ብለዋል። በፍርድ ሂደቱ ላይም "ኤፒ ለስኬት የሚያበቃ ሁኔታ አሳይቷል ማለት አልችልም" ብለዋል።

ዳኛው አክለው ዋይት ሀውስ በኤፒ የዜና ሽፋን ምክንያት አድሎ መፈፀሙን ተናግረዋል። ችግር የሚፈጥር ሁኔታ መሆኑንም ገልጸዋል።

የዳኛውን ውሳኔ ተከትሎ ዋይት ሀውስ ባወጣው መግለጫ "የዩናይትድ ስቴትስን ፕሬዝደንት በቢሮዋቸው እና በአውሮፕላናቸው ተገኝቶ መጠየቅ ለጋዜጠኞች የተሰጠ ልዩ መብት እንጂ ሕጋዊ ግዴታ አይደለም" ብሏል።
ትራምፕ በአሜሪካ የመንግስት ሰራተኞች ላይ በ"ሚም" ሲሳለቁ

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትናንትናው እለት ያጋሩት አስቂኝ የካርቱን ምስልም በሌላው አለም ያለውን ፈገግ ቢያሰኝም የሚመለከታቸውን አካላት ግን አስከፍቷል።

"ስፖንጅቦብ" የተሰኘውን የካርቱን ፊልም ገጸባህሪ በመጠቀም የተሰራው "ሚም" በአሜሪካ የፌደራል የመንግስት ሰራተኞች ላይ የሽሙጥ እና ስላቅ መልዕክት የያዘ ነው።

ትራምፕ የመንግስት ሰራተኞች እነዚህን አምስት ምላሾች ሊሰጡ ይችላሉ ሲሉ ተሳልቀዋል።
ኢዜማ መንግስት ወጣቶችን በህገ-ወጥ መንገድ ማፈኑን አወገዘ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ መሆኑን አውግዟል። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ መንግስት ወጣቶችን አፍኖ የት እንዳደረሳቸው እንዲገልጽ ጠይቋል።

ኢዜማ በመግለጫው መንግስት አፍኗቸው ያሉትን ወጣቶች የወንጀል ተጠያቂነት አለባቸው ካለ ክሱን በግልጽ መሥርቶ እራሳቸውን የመከላከል መብታቸውን እንዲያከብር ወይም በቶሎ እንዲፈታቸው ጠይቋል።

በተጨማሪም ያፈናቸውን ወጣቶች ቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኟቸው፣ የሕግ ጠበቃ እንዲቀርብላቸው እና አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግላቸው ጠይቋል።

ፓርቲው ይህን ህገ-ወጥ ተግባር የፈጸሙ የመንግስት አካላትን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት አካላትን በማሳተፍ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጠይቋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ተመልክቶ የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርቧል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ለመኖር የሚያስችል ፈቃድ በ5 ሚሊየን ዶላር ለሽያጭ አቀረቡ

ከዚህ ቀደም ከሚታወቀው አረንጓዴ ካርድ (የመኖሪያ ፈቃድ) ጋር የሚስተካከለውና 5 ሚሊየን ዶላር የመክፈል አቅም ላላቸው የሚቀርበው ወርቃማው ካርድ በቀጣዮቹ ቀናት ለገዥዎች ክፍት ይሆናል።
ወርቃማው ካርድ በሂደት የአሜሪካ ዜግነትንም ያስገኛል ተብሏል።
የአረንጓዴ ካርድ ዕጣ ፈንታን በተመለከተ ፕሬዝዳንቱ አስተያየት አልሰጡም። ስለጉዳዩ የሚያውቁ ግን ፕሬዝዳንቱ አረንጓዴ ካርድን የመገደብ ፍላጎት አላቸው። አዲሱ ወርቃማ ካርድ ተሽጦ የሚገኘው ገንዘብ የአሜሪካን የበጀት ጉድለት ለሟሟላት ይውላል። [ዋዜማ ]
ለአንድ የስራ መደብ 3ሺህ ሰው ተመዘገበ

አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ የግል ፎቶግራፈር እፈልጋለሁ ብላ ባወጣችው ማስታወቂያ ከ3000 በላይ ስራ ፈላጊ እንደተመዘገበ አስታወቀች።

ከአጋሮቼ ጋር በመሆን የመለየት ስራው ተሰርቶ ተፈትኖ በትላንትናው እለት የካቲት 18/2017 ዓም አሸናፊው ተመርጦ ወደ ስራ ገብተናል ብላለች።

በፊት የግል ቦዲ ጋርድ የተለመደ ሲሆን ከለውጡ በኋላ የግል ፎቶ ግራፈር እየተለመደ መጥቷል።
በኦሮሚያ ክልል መቱ ከተማ የነዳጅ ዋጋ በሊትር እስከ 900 ብር እየተሸጠ ነዉ!

* በኦሮሚያ ክልል መቱ ከተማ የነዳጅ ዋጋ በሊትር እስከ 900 ብር በመሸጡ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው።

* በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ፣ በወላይታ እና በጎፋ ዞኖች አንድ ሊትር ነዳጅ ከ500 ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ እየተሸጠ መሆኑ ተገልጿል።

* የነዳጅ አቅርቦት እጥረት በነዳጅ ማደያዎች በመኖሩ ምክንያት ነዳጁ በከፍተኛ ዋጋ በጥቁር ገበያ እየተሸጠ መሆኑን ነዋሪዎች ለአሐዱ ሬዲዮ ገልጸዋል።

* በተለይ የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፉ በከፍተኛ ሁኔታ እንደተጎዳ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

* የዋጋ ጭማሪው የካቲት 2017 ዓ.ም ከገባ ጀምሮ እየተባባሰ እንደመጣ የገለጹት ነዋሪዎች፣ የሚመለከተው አካል የነዳጅ አቅርቦት ችግሩን እንዲፈታ ጠይቀዋል።

* የኦሮሚያ ንግድ ቢሮ የንግድና ኢንስፔክሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ቆጲሳ በክልሉ እና በተለይም በመቱ ከተማ የነዳጅ እጥረት እንዳለ አምነው፣ ነገር ግን ነዳጁ እስከ 900 ብር እየተሸጠ መሆኑን አልተቀበሉም።

* የክልሉ መንግስት ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድን ለመቆጣጠር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

* የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ሳዲሁን ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ በነዳጅ ጥቁር ገበያ ላይ ችግሮች እንደነበሩ ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅት ግን ሁኔታው መሻሻል ማሳየቱን ተናግረዋል።

* ሁለቱም የክልል ባለስልጣናት ሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድን ለመቆጣጠር የማህበረሰቡን ትብብር ጠይቀዋል።
የከሰም የስኳር ፋብሪካ ከ3 ሺህ በላይ ሰራተኞቹን አሰናበተ ⵑⵑ

ፋብሪካው በአፋር ክልል እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት እንዳለ ይፋ ባደረገ በወሩ፣ ከ3,700 በላይ ሠራተኞቹን ከሥራ ማሰናበቱን ነው ያስታወቀው ፡፡

እንደሪፖርተር ዘገባ በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመጣው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ተፈናቅለው በካምፕ የተጠለሉ 3,750 ቋሚና ጊዜያዊ የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች፣ የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ባልጠበቁት ሁኔታ ከሥራ መሰናበታቸው ተገልጿል፡፡

ጋዜጣው አገኘሁት ያለው የሰነድ ማስረጃ እንደሚያስረዳው፣ ከሥራ ገበታቸው የተገለሉት 1,250 ቋሚ ሠራተኞች ሲሆኑ፣ የተቀሩት 2,500 ሠራተኞች ደግሞ በሸንኮራ እርሻና በፋብሪካው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎች ላይ አስተዋፅኦ የነበራቸው ጊዜያዊ የሥራ ቅጥር ውል የነበራቸው ሠራተኞች ናቸው።
በአዲስ አበባ አገልጋዮች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ ተከለከሉ

በአዲስአበባ ፤ አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይገቡ ታገዱ::

አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ መከልከሉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታወቀ።

ሀገረ ስብከቱ የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት  ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎችና ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ቄሰ ገበዞች ጋር ባደረገው ውይይትና ስምምነት መነሻነት  የተለያዩ መመሪያዎች  መተላለፋቸው ተገልጿል።

ከመመሪያዎች አንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ  የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ  የተከለከተለ መሆኑን ለሁሉም  ገዳማትና አድባራት በተላከው የመመሪያ ደብዳቤ  ለማወቅ ተችሏል።

በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት መሠረት ቅዳሴ የሁሉም ጸሎታት ማጠናቀቂያ ፣ ቀራንዮ ላይ ምንገኝበት፣ የበጉ ሠርግ ላይ የምንታደምበት፣የጌታችንን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በአንድነት ለሓጢአት ሥርየት፣ ለነፍስ ሕይወት፣ ለሃይማኖት ጽንዐትና ለመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ይሆነን ዘንድ የምቀበልበት  ታላቅ የጸሎት ሰዓት ነው ብሏል ሀገረ ስብከቱ።

በመሆኑም አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም ጎልጎታን ከሚያስረሱ ፣በረከትን ከሚያሳጡና  ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ እንደተከለከለም  ተገልጿል።

ይህንን መመሪያም የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ  መታዘዛቸውን በተጻፈ ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።
(አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)
አማራ ክልል በትራፊክ አደጋ የ14 ሠዎች ሕይወት አለፈ!

በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ የ14 ሠዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ዐሳወቀ!።

የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር ይበልጣል መርሻ፦ ዛሬ ለዶይቼ ቬለ በስልክ እንደገለፁት ተሽከርካሪው ትናንት ከበየዳ ወደ ደባርቅ ሠዎችንና እህል ጭኖ ሲጓዝ ከረፋዱ 3፡30 አካባቢ በደባርቅ ወረዳ ልዩ ሥሙ «አበርጊና» በተባለ ቦታ ላይ ሲደርስ ተገልብጦ 14 ሰዎች ሲሞቱ ሌሎች በርካቶች ቆስለዋል ።

ተጨማሪ ምርመራዎች እየተደረጉ ቢሆንም፤ ለመኪናው መገልበጥ ምክንያት ነው ያሉትን ኃላፊው ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል ። «ከበየዳ ወደ ደባርቅ ሲመጣ የነበረ በተለምዶ ‘ካሶኒ’ እየተባለ የሚጠራ መኪና ነው፥ በየዳ አድሮ እህል ጭኖ እየመጣ ከበየዳ ወጣ እንዳለ አበርጊና ከተባለች ጎጥ ሲደርስ ተገልብጧል» ብለዋል ።

የአደጋው መንሳኤ አንዱ ከመጠን በላይ መጫን መሆኑን የገለፁት ኃላፊው፦ የመኪናው አቅም ከሚችለው እህል ጭነት በላይ 50 ሠዎችን አሳፍሮ ነበር ብለዋል። ሌላው ለአደጋው መንሳኤ ተብሎ የሚገመተው አሽከርካሪው ለመስመሩ አዲስ በመሆኑ የመንገዱን ባሕርይ ዐለማወቅ ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል ። በአድጋው 12 ሠዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ፤ ሌሎች ሁለት ደግሞ ዛሬ ጠዋት ሕይወታቸው አልፏል ብለዋል ። ቀሪ 37ቱ ደግሞ በተለያዩ የሕክምና ቦታዎች ሕክምና እየወሰዱ እንደሆነና 27ቱ በከባዱ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተዘግቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም የእንሰሳት አርቢዎች "የብድር እና የኢንሹራንስ አገልግሎት" በቀላሉ ማግኘት የሚያስችላቸውን ቴክኖሎጂ ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ

በኢትዮጵያ ቀዳሚው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም የድርጅት ደንበኞችን እና ተቋማትን አቅም የሚገነቡ እና የሚያዘምኑ በክላውድ አገልግሎት ላይ የተመሰረቱ የዲጂታል ሶሉሽኖችን ይፋ አደርጓል።

ከእነዚህም መካከል አንዱ ትኩረት የሚስብ የዲጂታል ላይቭስቶክ ትራኪንግ (የእንስሳት ዲጂታል ክትትል) ሲሆን፣ ይህ ሶሉሽን የእንስሳት እርባታን ዘመናዊ በማድረግ እና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሏል።

የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ እንደተናገሩት ይህን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ገበሬዎች እና እንስሳት አርቢዎች የከብቶቻቸውን እንቅስቃሴ እና ጤና መከታተል፣ እንዲሁም የብድር እና የኢንሹራንስ አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ።
ከ6 ሺሕ በላይ የሱስ ተጠቂዎች የሕክምና ዕድል አገኙ

የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ በአዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ከ6 ሺሕ 300 በላይ የሚሆኑ የሱስ ተጠቂዎች የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል።

ይህ እርምጃ በሚኒስቴሩ የአይምሮ ጤና ፕሮግራም ባለሙያ አቶ ጀማል ተሾመ እንደተገለጸው፣ በሀገሪቱ እየጨመረ ያለውን የሱስ ተጠቂዎች ቁጥር ለመግታት የተወሰደ ነው።

በተለይም በጫት፣ በአልኮል እና ተያያዥ ሱስ አስያዥ ነገሮች ላይ የተጠመዱ ወጣቶች ከፍተኛ ቁጥር እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ተጠቂዎች በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ይገኛሉ።

ሚኒስቴሩ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑትን ለመርዳት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሰራ ሲሆን፣ ልዩ የሕክምና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው 4 ነጥብ 9 በመቶ የሚሆኑት እንደሆኑ ተገልጿል። ከእነዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 9 በመቶ የሚሆኑት በአልኮል ሱስ የተጠቁ ናቸው።
በተጀመረው የሕክምና አገልግሎት ከ6 ወር ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት በክትትል ሥር እንዲቆዩ በማድረግ ወደ ጤንነታቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ነዉ ተብሏል ።
መተሃራ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ ከፍተኛ ዝርፊያ ተፈጸመ

በአዋሽ-ወልዲያ-ሃራ ገበያ የባቡር ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ላይ ከፍተኛ የሆነ የዝርፊያ ወንጀል መፈጸሙ ተገለጸ።

ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ ከመተሃራ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ ድረስ ባለው 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 78.9 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ እና 25.7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ተዘርፏል።

በፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተክለወይን ብርሃነአሰፋ እንደገለጹት፣ ከባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ እስከ ሁለት ባለው ርቀት ላይም 2.2 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ ተዘርፏል።

በዚህም በድምሩ ከ758 ሺህ ዶላር በላይ እና ከ6.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደርሷል።

የስርቆቱ ወንጀል የተፈጸመው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ወደ ስራ እስኪገባ ድረስ በጊዜያዊነት ኃይል ይዞ እንዲቆይ ለማድረግ ከስራ ተቋራጩ ጋር ምክክር እየተደረገ ባለበት ወቅት መሆኑን አቶ ተክለወይን ገልጸዋል።

በተጨማሪም፣ የተዘረፈ የኮንዳክተር ሽቦ በአይሱዙ መኪና ተጭኖ በአዳማ ከተማ ላይ ሲጓጓዝ መያዙን እና በዱለሳ ወረዳ ደግሞ ለመቁረጥ የሚያገለግል መሳሪያ ይዘው የተገኙ ሁለት ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
2025/02/27 08:27:29
Back to Top
HTML Embed Code: