tgoop.com/Humanity02H/8
Last Update:
1,እንኳን ተኝተህ ነቅተሕም ትሄዳለህ
.
.
ከባለፈው የቀጠለ
=======
«ዛሬ ብቅ ብላ የሄደችው ፀሀይ ነገ ብቅ ማለቷ ተመሳሳይ የሰዓት አቆጣጠር እንድንቆጥር ትፈቅድልናለች እንጂ ያንኑ ጊዜና እድል ይዛልን አትመጣም።»
ጊዜ ሁሉም ነገር የሕልውና እስትንፋሱን የሚያኝበት ነው። ያለ ጊዜ ምንም ነገር ምንም ነው። ይሁንና ሳውቀው የምናብክነው ቁጥር አንድ ነገር ደሞ ጊዜ ነው። ከላይ የተመለከትናት ባለ ታሪካችን ስትኳትን ኖራ ነበር። ነገር ግን የሕይወቷ ድምር ውጤት ከመጸጸት አላዳናትም። ምክንያቱም ልፋቷ በሙሉ ያውጠነጥን የነበረው ተለምዷዊና ለኑሮ በሚሆኑ ነገሮች ላይ ብቻ ነበር። ሌሎቹን የህይወቷን ጉዳዮች ሳታስገባቸው ጀርባ ሰጥታቸው ኖራለች። ከረፈደ በኋላ ብትባንንም አቀበት ሆነው አገኘቻቸው። ከዚህ የበለጠ የሚያስገርመው ደግሞ እኛም የእርሷኑ ዓይነት ታሪክ መድገማችን ነው።
ምክንያቱም ቤተሰቦቻችን፤ ትምህርቶቻችን፤ ባሕሎቻችን ስለ ጊዜ ዋጋ የሚገባውን ያህል አላሰረጹብንም።
በርካታ ምሁራን ከሁሉም በፊት ስለ ጊዜ እውነታዎች ማወቅ አስፈላጊ መሆኑን ያሳስባሉ።
አንደኛ፦ ጊዜ እንደ ወንዝ ውሃ አንድ ጊዜ ብቻ የሚረገጥ ነው። አላህን የሰጠንን የመጀመሪያዋን ደቂቃ ሳይወስድብን በፊት ሌላ ተጨማሪ ደቂቃ አይሰጠንም፤
ሁለተኛ፦ በጊዜ ላይ ስልጣን ያለው አንድም ሰው የለም፤
ሦስተኛ፦ ሁሉም ነገር የኛ የሚሆነውና ወደ መሆን የሚመጣው በጊዜ ውስጥ አልፎ ነው፤
አራተኛ፦ ጊዜ ለሁሉም በእኩል ተሰፍሮ የተሰጠ የሃያ አራት(24) ሰአት እርዝማኔ ያለው ነው፤
አምስተኛ፦ በሕይወታችን ላይ ለውጥ የሚያመጣው እንደ አጠቃቀማችን እንጂ እጃችን በመግባቱ አይደለም፤
ስድስተኛ፦ ሁሉም ሰው በመጭው ዓለም የተሰጠውን ዕድሜ ዘመን እንዴት እንዳሳለፈው አላህ ዘንድ ተጠያቂ ነው፤
ሰባተኛ፦ ጊዜ ከምንገምተው በላይ በጣም ፈጥኖ የሚያልፍ ነው፤
ስምንተኛ፦ ሁሉንም ነገር ማሳካት አንችልም፤
ዘጠነኛ፦ በወቅቱ እንደምናልፍበት የስሜት ጠለል የማጠርና የመርዘም ስሜቱ የሚለያይ ነው፤
አሥረኛ፦ በጥንቃቄ የሚጠቀምበትን ሰው ብቻ ነው ትርፋማ ሊያደርግ የሚችለው በማለት የጊዜ እውነታዎችን ሙሁራኖች አድረድተዋል።
ጊዜን የሚያባክኑ አሥራ አምስት(15) ነገሮችንም በጥናታቸው ዘርዝረዋል፤
.
.
.
.
ይቀጥላል
=======
ምንጭ፦ የማር ጠብታ ከሚለው መጸሀፍ
=======
Join our telegram channel for more topic፦
https://www.tgoop.com/Humanity02H
BY Human and Humanity
Share with your friend now:
tgoop.com/Humanity02H/8