IBNUMUHAMMEDZEYN Telegram 1562
ስንፍና እሹሩሩ
~
ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከሚታዩ አስቀያሚ ሃሳቦች አንዱ "እኔ ረጅም ፅሑፍ አልወድም" የሚል የስንፍና አዋጅ ነው። ደግሞኮ በዚህ በሽታ የተለከፈው ብዛቱ! ለምን ግን ነውር ጌጡ እንሆናለን? ሁለት ሶስት ገፅ ፅሑፍ ረዝሞ ነው "ረጅም ፅሑፍ" እያልን የምንገልፀው? ደግሞስ አለማንበብ ቁምነገር ሆኖ ነው እንደ ጀብድ የምናወራው? እኛ በዚህ ዓይነት ገዳይ ስንፍና ውስጥ ከሆንን ማነው ልጆቻችንን መስመር የሚያሲዛቸው? እንዴትስ ነው ከልብ ሆነው ኪታብ እንዲቀሩ፣ ትምህርት እንዲማሩ የምናደርጋቸው? ለመሆኑ ክፉ ምሳሌ እንዳንሆን ቦታ እየመረጥን ነው "ረጅም ፅሑፍ አልወድም" የምንለው? ነው ወይስ ለታዳጊዎችም ስንፍናችንን "በክብር" እያወረስን ነው?
እንዲያው ክፉ በሽታ ቢጣባን እንጂ እንደ ማንበብ የሚያረካ ምን አለ? እንዴት ነው ሳናነብ የአስተሳሰብ አድማሳችንን የምናሰፋው? እንዴት ነው ያለ ንባብ ራሳችንን የምንለውጠው? እንዴት ነው ያለ ንባብ ትውልድ የምንገነባው? ጭራሽ ባደባባይ ተወጥቶ "እኔ ረጅም ፅሑፍ አልወድም" እያሉ እንደ ጀብድ ይቀባበሉታል። እሺ አትወድም። ሰው ነውሩን ባደባባይ ያሰጣል? "የንባብ ባህላችን ሞተ ምን ይሻላል?"፣ "የንባብ ፍቅር የለኝም፤ ምን ባደርግ ይሻለኛል?" የሚል ሰው መፍትሄ ፍለጋ ይናገር። "እንዴት ችግሬን ልቅረፍ?" ለማለት። በጋራ መፍትሄ ለመፈለግ። ዛሬ የሚታየው ግን ሌላ ነው። አንዱ "እኔ ረጅም ፅሑፍ አልወድም" ሲል ሌሎችም እንደ ቁም ነገር እያከታተሉ "እኔም"፣"እኔም" እያሉ የኮሜንት ዶፍ ያወርዳሉ። ይሄ ነውር ነው፤ ነውር ጌጡ! ለአኺራም ይሁን ለዱንያ የሚሆኑ ቁምነገር አዘል ዳጎስ ያሉ ኪታቦችንና መፅሐፎችን ማንበቡ ቀርቶ ጭራሽ ሶስትና አራት ገፆችን ለማንበብ ልባቸው ጉሮሯቸው ስር ይወተፋል። ከዚያ ህፃን ይመስል ፕራንክ እያሯሯጡ፣ እንቶፈንቶ የቴክቶክና የዩቲዩብ ቪዲዮ እያሳደዱ ይውላሉ። ይሄ ሊታከሙት የሚገባ በሽታ ነው። ሰው እንዴት ፕራንክ የሚሉት የጅላጅል ስራ ላይ ሲያገጥ ይውላል? ሱብሓነላህ!
በተለይ ጦለበተል ዒልም (ደረሶች) እንዴት ነው ኪታብ ሳታነቡ የምትውሉት? እስኪ በዚህ አመት ስንት ኪታብ እንዳነበብክ ራስህን መለስ ብለህ ታዘበው? የዒልም ጉዞህ እንዲህ የተንዘላዘለ እንዲሆን ነው የምትፈልገው? ትርጉም ያለው የዒልም ትጥቅ መታጠቅ የሚፈልግ ሰው እንዴት ያለ ንባብ ካሰበበት እደርሳለሁ ብሎ ያስባል?! ይሄ የግድ መታረም ያለበት ክፉ ልማድ ነው።
ለማንኛውም ነፍስ እንደ ያዟት ነው የምትሆነው። ለቁርኣን ጊዜ የማይሰጥ ሰው 30 ደቂቃ ቁጭ ብሎ መቅራት ትእግስቱን ይፈታተነዋል። ከሶላት ጋር ልቡ ያልተዋሀደ ሰው አራት ረከዐ ለመስገድ አስሬ ያዛጋል። ችግሩን ለመፍታት ግን ከአላህ ጋር ቀላል ነው። በቅድሚያ የችግሩን አሳሳቢነት እንመን። ከዚያ ቁርጠኝነት እንታጠቅ። ከዚያ ተደጋጋሚ ጥረት እናድርግ። ከዚያ ለውጣችንን እንገምግም። አንዴ ህይወታችን ጋር ከተዋሀደ ወላሂ እያጣጣምነው ነው የምንኖረው። ስንፍናችንን እሹሩሩ እያልን የምንቀጥል ከሆነ ግን እድሜ ልካችንን በድንቁርና እያጌጥን ነው የምንኖረው። አላህ ይሁነን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor



tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1562
Create:
Last Update:

ስንፍና እሹሩሩ
~
ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከሚታዩ አስቀያሚ ሃሳቦች አንዱ "እኔ ረጅም ፅሑፍ አልወድም" የሚል የስንፍና አዋጅ ነው። ደግሞኮ በዚህ በሽታ የተለከፈው ብዛቱ! ለምን ግን ነውር ጌጡ እንሆናለን? ሁለት ሶስት ገፅ ፅሑፍ ረዝሞ ነው "ረጅም ፅሑፍ" እያልን የምንገልፀው? ደግሞስ አለማንበብ ቁምነገር ሆኖ ነው እንደ ጀብድ የምናወራው? እኛ በዚህ ዓይነት ገዳይ ስንፍና ውስጥ ከሆንን ማነው ልጆቻችንን መስመር የሚያሲዛቸው? እንዴትስ ነው ከልብ ሆነው ኪታብ እንዲቀሩ፣ ትምህርት እንዲማሩ የምናደርጋቸው? ለመሆኑ ክፉ ምሳሌ እንዳንሆን ቦታ እየመረጥን ነው "ረጅም ፅሑፍ አልወድም" የምንለው? ነው ወይስ ለታዳጊዎችም ስንፍናችንን "በክብር" እያወረስን ነው?
እንዲያው ክፉ በሽታ ቢጣባን እንጂ እንደ ማንበብ የሚያረካ ምን አለ? እንዴት ነው ሳናነብ የአስተሳሰብ አድማሳችንን የምናሰፋው? እንዴት ነው ያለ ንባብ ራሳችንን የምንለውጠው? እንዴት ነው ያለ ንባብ ትውልድ የምንገነባው? ጭራሽ ባደባባይ ተወጥቶ "እኔ ረጅም ፅሑፍ አልወድም" እያሉ እንደ ጀብድ ይቀባበሉታል። እሺ አትወድም። ሰው ነውሩን ባደባባይ ያሰጣል? "የንባብ ባህላችን ሞተ ምን ይሻላል?"፣ "የንባብ ፍቅር የለኝም፤ ምን ባደርግ ይሻለኛል?" የሚል ሰው መፍትሄ ፍለጋ ይናገር። "እንዴት ችግሬን ልቅረፍ?" ለማለት። በጋራ መፍትሄ ለመፈለግ። ዛሬ የሚታየው ግን ሌላ ነው። አንዱ "እኔ ረጅም ፅሑፍ አልወድም" ሲል ሌሎችም እንደ ቁም ነገር እያከታተሉ "እኔም"፣"እኔም" እያሉ የኮሜንት ዶፍ ያወርዳሉ። ይሄ ነውር ነው፤ ነውር ጌጡ! ለአኺራም ይሁን ለዱንያ የሚሆኑ ቁምነገር አዘል ዳጎስ ያሉ ኪታቦችንና መፅሐፎችን ማንበቡ ቀርቶ ጭራሽ ሶስትና አራት ገፆችን ለማንበብ ልባቸው ጉሮሯቸው ስር ይወተፋል። ከዚያ ህፃን ይመስል ፕራንክ እያሯሯጡ፣ እንቶፈንቶ የቴክቶክና የዩቲዩብ ቪዲዮ እያሳደዱ ይውላሉ። ይሄ ሊታከሙት የሚገባ በሽታ ነው። ሰው እንዴት ፕራንክ የሚሉት የጅላጅል ስራ ላይ ሲያገጥ ይውላል? ሱብሓነላህ!
በተለይ ጦለበተል ዒልም (ደረሶች) እንዴት ነው ኪታብ ሳታነቡ የምትውሉት? እስኪ በዚህ አመት ስንት ኪታብ እንዳነበብክ ራስህን መለስ ብለህ ታዘበው? የዒልም ጉዞህ እንዲህ የተንዘላዘለ እንዲሆን ነው የምትፈልገው? ትርጉም ያለው የዒልም ትጥቅ መታጠቅ የሚፈልግ ሰው እንዴት ያለ ንባብ ካሰበበት እደርሳለሁ ብሎ ያስባል?! ይሄ የግድ መታረም ያለበት ክፉ ልማድ ነው።
ለማንኛውም ነፍስ እንደ ያዟት ነው የምትሆነው። ለቁርኣን ጊዜ የማይሰጥ ሰው 30 ደቂቃ ቁጭ ብሎ መቅራት ትእግስቱን ይፈታተነዋል። ከሶላት ጋር ልቡ ያልተዋሀደ ሰው አራት ረከዐ ለመስገድ አስሬ ያዛጋል። ችግሩን ለመፍታት ግን ከአላህ ጋር ቀላል ነው። በቅድሚያ የችግሩን አሳሳቢነት እንመን። ከዚያ ቁርጠኝነት እንታጠቅ። ከዚያ ተደጋጋሚ ጥረት እናድርግ። ከዚያ ለውጣችንን እንገምግም። አንዴ ህይወታችን ጋር ከተዋሀደ ወላሂ እያጣጣምነው ነው የምንኖረው። ስንፍናችንን እሹሩሩ እያልን የምንቀጥል ከሆነ ግን እድሜ ልካችንን በድንቁርና እያጌጥን ነው የምንኖረው። አላህ ይሁነን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor

BY Ibnu Muhammedzeyn




Share with your friend now:
tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1562

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Find your optimal posting schedule and stick to it. The peak posting times include 8 am, 6 pm, and 8 pm on social media. Try to publish serious stuff in the morning and leave less demanding content later in the day. To view your bio, click the Menu icon and select “View channel info.” With Bitcoin down 30% in the past week, some crypto traders have taken to Telegram to “voice” their feelings. A new window will come up. Enter your channel name and bio. (See the character limits above.) Click “Create.” While some crypto traders move toward screaming as a coping mechanism, many mental health experts have argued that “scream therapy” is pseudoscience. Scientific research or no, it obviously feels good.
from us


Telegram Ibnu Muhammedzeyn
FROM American