KETBEB_MENDER Telegram 3556
​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል 26

    ደራሲ - አብላካት



አቶ ሰለሞን እና አቶ እስክንድር ጋር ስንደርስ .....ሁለቱም ተያዩና ቃልኪዳን አለኝ አቶ እስክንድር በመጠራጠር ስሜት ውስጥ ሆኖ.... " አዎ አልተሳሳትኩም ቃል ነሽ" አለኝ..... አቶ ሰለሞንም ቀጠል አድርጎ " ቢረሳ ቢረሳ እንዴት የዳይመንድ ፈርጦች ይረሳሉ ? ከሁሉም በላይ ደሞ ቃል አንቺን አለማስታወስ በእውነቱ ንፉግነት ነው" ብሎ ፈገግ አለ........ምን ቤተክርስቲያን ሳስቀድስ እና ስዘምር ወይ በጎ ነገር ስሰራ እንዳየ ሰው አለማስታወስ ንፉግነት ነው ይላል... ባያስታውሰኝ ነበር እኮ እሚሻለኝ...... በቃ እኛ ሰዎች አሉባልተኛ ሆነን ቀረን ማለት ነው ? .....ምናለ በደህና ነገር ብንተዋወስ .... ማይለፍ ግራ በመጋባት ስሜት ውስጥ ሆኖ አይኑን ከአንዳችን ወደ አንዳችን እያንከባለለ ይቃኘናል...
"ምነው ሰላም አትይንም እንዴ ቃል" አለኝ አቶ እስክንድር...
"በጣም ይቅርታ ሀሳብ ውስጥ ሆኜ ነው እንዴት ናችሁ ?" ብዬ ተራ በተራ ጨበጥኳቸው
"እኛማ ደህና ነን እናንተ የውሀ ሽታ ሆናችሁ ከራችሁ እንጂ... እንደቀልድ ብዙ ወራት ሆናችሁ ወደ ዳይመንድ ከመጣችሁ የቤቱ ድምቀት እናንተ ነበራችሁ" አለ አቶ ሰለሞን
"አዎ ረጅም ጊዜ ሆነን ከተያየን..... ደሞም እዚህም ቢሆን ጓደኞችሽን እስካሁን አላየኋቸውም ብቻሽን ነው እንዴ የመጣሽው ?" አለኝ አቶ እስክንድር ቀጠል አድርጎ
"ፈራ ተባ እያልኩም ቢሆን መመለሴ ግድ ሆነ...አዎ ከዳይመንድ ከራቅን ረጅም ጊዜ ሆኖናል ወደዛ አካባቢ መተን አናውቅም... ጓደኞቼ ደህና ናቸው ዛሬ ከማይለፍ ጋር ነው የመጣሁት ለዛ ነው" አልኳቸው
"በሰላም ከሆነ እሺ..ልጅ ማይለፍ ምነው በዝምታ ተዋጥቅ ? ችግር አለ እንዴ ?" አለ አቶ እስክንድር
"በጭራሽ እዚሁ ነኝ ንግግራችሁን ጨርሱ ብዬ ነው" አላቸው ማይለፍ
"በቃ እንግዲህ እንገናኛለን ቃልዬ ቁጥርሽ የበፊቱ ነው አይደል ? እደውላለው" አለኝ አቶ እስክንድር
"አዎ እሺ እንገናኛለን" አልኳቸው.... ከማለፍ ጋር በዓይን ቻው ተባብለው ወደ መቀመጫቸው ተመለሱ.... እንኳን ከዚህ በላይ አልዘባረቁ ብዬ ፈጣሪዬን እያመሰገንኩ ሳለሁ ማይለፍ...
"ከዚህ እንውጣ!" አለኝ በተቆጣ አነጋገር....ብደነግጥም ምንም ሳልናገር ተከትዬው ወጣሁ....መኪናው ውስጥ እንደገባን....
"ዳይመንድ ትሄጂ ነበር ?" አለኝ
"እእ አዎ እዛ እሰራ ነበር እና ደሞ ከጓደኞቼ  ጋር እዛው እንዝናና ነበር"
"ዳይመንድ ማለት እኮ ሴሰኝነትን ከወንዱ እስከ ሴቱ እንደ ጀብድ እሚቆጥሩበት... የርካሽ ሰዎች መናሀሪያ ነው እንዴት አንቺ እዛ ተገኘሽ...  ደሞስ በዚህ ደረጃ ታዋቂ የሆንሽው በምን ምክንያት ነው  ?" ብሎ በጥያቄ አፋጠጠኝ። መጠየቁ ልክ ሆኖ ሳለ ንግግሩ ትንሽ ከስርዓት የወጣ በመሆኑ ተበሳጨሁ !
"እና እዛ መገኘቴ ርካሽ ለመሆኔ ማረጋገጫ ነው እንዴ ?"
"እንደዛ እያልኩኝ ሳይሆን እዛ ቦታ ትገኛለሽ ብዬ አልጠበኩም ሲቀጥል ደግሞ እነ አቶ ሰለሞን ማለት እኮ እንኳን ዳይመንድ የተገኘች ሴት ቀርቶ መንገድ ላይ ፈገግ ያለችላቸውን ሴት ሳይቀር አልጋ ላይ ይዘው ካልወጡ እንቅልፍ እማይወስዳቸው ሴሰኞች ናቸው" .......ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጥኩት
"ስለዚህ በተዘዋዋሪ ከእነሱ ጋር ማደሬን እየነገርከኝ ነው ?"
"አልወጣኝም ግን ደግሞ ዳይመንድ መሄድሽ ግራ አጋብቶኛል... ጓደኞችሽስ የትኞቹ ናቸው አስተዋውቀሽኝም አሳይተሽኝም አታውቂም የዚህን ያህል የዳይመንድ ፈርጦች እስከመባል ያደረሳችሁ ነገር ምንድነው እውነተኛዋስ ቃልኪዳን ማናት እኔ ያፈቀርኳት ወይስ እነ ሰለሞን ያወሩላት ? መቼስ ዳይመንድ መፅሀፍ ቅዱስ አምብበሽላቸው አደለም የወደዱሽ" ብሎ ንቀት በተሞላበት አነጋገር አፈጠጠብኝ.... ከሱ ያልጠበቁት አወራር ስለሆነ ደርቄ ቀረሁ...
"ምነው እውነት ስለሆነ መልስ አጣሽ አደል" አለኝ
"ታውቃለህ አሁን አንተ ያልካትን ቃልኪዳን እምሆነው መልስ ከሰጠሁክ ነው ! አንድ ነገር ግን ልንገርህ አንተም ብትሆን ዳይመንድ የሄድከው እና የዚህን ያህል ስለ ዳይመንድ ያወከው ለቅዳሴ ሄደህ አይደለም ! አመሰግናለሁ" ብዬ ከመኪናው ወረድኩኝ....

እያለፈ የነበረ የላዳ ታክሲ አስቁሜ ወደ ቤቴ መሄድ ጀመርኩ.....በዚህ ልክ እንዴት ሰውን መገመት ቀላል ይሆናል ? ሳያዳምጡ ሳይጠይቁ ሳያረጋግጡ መፍረድ ቀላል ነው እንዴ ? ስለ እኔ በቅጡ እንኳን ሳያውቅ እንዴት እንዲህ ይናገረኛል.... በርግጥ ስለዳይመንድ ያወራው ሁሉ ልክ ነው ነገር ግን ዳይመንድ መገኘቴ ብቻ እንዴት የኔን ማንነት ያራክሰዋል ..... ቆይ እስር ቤት የገባ ሁሉ ወንጀለኛ ነው እንዴ ?  ቤተክርስቲያን የሄደ ሁሉ ፃድቅ ነው እንዴ ? ....  ሰው በዋለበት እና በለበሰው ነገር ሊገመገም ይገባል ብዬ አላስብም....በየትኛው ንፁህነታችን ነው በሌሎች ጫማ ውስጥ ተቀምጠን ፍርድ እምንሰጠው....ማንም ይሁን ማንም በህይወቱ ስለሚሆነው እና ሰለሚያደርገው ነገር ሊጠይቀውም ሊፈርድበትም እሚገባው የፈጠረው አምላኩ ብቻ ነው ባይ ነኝ።  ማይለፍ በዚህ ልክ አውርዶ ይመለከተኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር። ከሚፈርድብኝ ቀድሞ እኔ እንዳስረዳው በአግባቡ ቢጠይቀኝ አንድም ሳላስቀር እነገረው ነበር እሱ ግን ቀድሞ ወነጀለኝ።

"የኔ እህት ያልሽኝ ቦታ ደርሰናል" እሚል ድምፅ ከገባሁበት ሀሳብ አነቃኝ
"እእ እሺ አመሰግናለሁ"  ሂሳቡን ከፍዬ ስወርድ... "እናት"........ ብሎ መስኮቱን ከፈተና .....
"አንድ ነገር ማለት ፈልጌ ነበር ፍቃድሽ ከሆነ"..... አለኝ በተረጋጋ ድምፅ
" እሺ ምንድነው ?" መለስኩለት
"ስላንቺ ባላውቅም ያለቀሽበት ምክንያት ባይገባኝም እንባሽ ግን ለእውነተኛነትሽ ምስክር ነው። ለሰዎች ብለሽ እሚያምሩት አይኖችሽን አታድክሚያቸው....ሰላም እደሪ" አለኝ... ንግግሩ በጥቂጡም ቢሆን ፈገግ አስባለኝ።
"በጣም አመሰግናለሁ ፈጣሪ ያክብርልኝ ፤ አሜን ሰላም እደር" .....ብዬ ተሰናብቼው ወደ ቤቴ ገባሁ.....


ይቀጥላል.......

ቀጣዩ ክፍል ከ100❤️ በኋላ ይለቀቃል።



✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
       @Ketbeb_Mender 
       @Ketbeb_Mender 
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯



tgoop.com/Ketbeb_mender/3556
Create:
Last Update:

​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል 26

    ደራሲ - አብላካት



አቶ ሰለሞን እና አቶ እስክንድር ጋር ስንደርስ .....ሁለቱም ተያዩና ቃልኪዳን አለኝ አቶ እስክንድር በመጠራጠር ስሜት ውስጥ ሆኖ.... " አዎ አልተሳሳትኩም ቃል ነሽ" አለኝ..... አቶ ሰለሞንም ቀጠል አድርጎ " ቢረሳ ቢረሳ እንዴት የዳይመንድ ፈርጦች ይረሳሉ ? ከሁሉም በላይ ደሞ ቃል አንቺን አለማስታወስ በእውነቱ ንፉግነት ነው" ብሎ ፈገግ አለ........ምን ቤተክርስቲያን ሳስቀድስ እና ስዘምር ወይ በጎ ነገር ስሰራ እንዳየ ሰው አለማስታወስ ንፉግነት ነው ይላል... ባያስታውሰኝ ነበር እኮ እሚሻለኝ...... በቃ እኛ ሰዎች አሉባልተኛ ሆነን ቀረን ማለት ነው ? .....ምናለ በደህና ነገር ብንተዋወስ .... ማይለፍ ግራ በመጋባት ስሜት ውስጥ ሆኖ አይኑን ከአንዳችን ወደ አንዳችን እያንከባለለ ይቃኘናል...
"ምነው ሰላም አትይንም እንዴ ቃል" አለኝ አቶ እስክንድር...
"በጣም ይቅርታ ሀሳብ ውስጥ ሆኜ ነው እንዴት ናችሁ ?" ብዬ ተራ በተራ ጨበጥኳቸው
"እኛማ ደህና ነን እናንተ የውሀ ሽታ ሆናችሁ ከራችሁ እንጂ... እንደቀልድ ብዙ ወራት ሆናችሁ ወደ ዳይመንድ ከመጣችሁ የቤቱ ድምቀት እናንተ ነበራችሁ" አለ አቶ ሰለሞን
"አዎ ረጅም ጊዜ ሆነን ከተያየን..... ደሞም እዚህም ቢሆን ጓደኞችሽን እስካሁን አላየኋቸውም ብቻሽን ነው እንዴ የመጣሽው ?" አለኝ አቶ እስክንድር ቀጠል አድርጎ
"ፈራ ተባ እያልኩም ቢሆን መመለሴ ግድ ሆነ...አዎ ከዳይመንድ ከራቅን ረጅም ጊዜ ሆኖናል ወደዛ አካባቢ መተን አናውቅም... ጓደኞቼ ደህና ናቸው ዛሬ ከማይለፍ ጋር ነው የመጣሁት ለዛ ነው" አልኳቸው
"በሰላም ከሆነ እሺ..ልጅ ማይለፍ ምነው በዝምታ ተዋጥቅ ? ችግር አለ እንዴ ?" አለ አቶ እስክንድር
"በጭራሽ እዚሁ ነኝ ንግግራችሁን ጨርሱ ብዬ ነው" አላቸው ማይለፍ
"በቃ እንግዲህ እንገናኛለን ቃልዬ ቁጥርሽ የበፊቱ ነው አይደል ? እደውላለው" አለኝ አቶ እስክንድር
"አዎ እሺ እንገናኛለን" አልኳቸው.... ከማለፍ ጋር በዓይን ቻው ተባብለው ወደ መቀመጫቸው ተመለሱ.... እንኳን ከዚህ በላይ አልዘባረቁ ብዬ ፈጣሪዬን እያመሰገንኩ ሳለሁ ማይለፍ...
"ከዚህ እንውጣ!" አለኝ በተቆጣ አነጋገር....ብደነግጥም ምንም ሳልናገር ተከትዬው ወጣሁ....መኪናው ውስጥ እንደገባን....
"ዳይመንድ ትሄጂ ነበር ?" አለኝ
"እእ አዎ እዛ እሰራ ነበር እና ደሞ ከጓደኞቼ  ጋር እዛው እንዝናና ነበር"
"ዳይመንድ ማለት እኮ ሴሰኝነትን ከወንዱ እስከ ሴቱ እንደ ጀብድ እሚቆጥሩበት... የርካሽ ሰዎች መናሀሪያ ነው እንዴት አንቺ እዛ ተገኘሽ...  ደሞስ በዚህ ደረጃ ታዋቂ የሆንሽው በምን ምክንያት ነው  ?" ብሎ በጥያቄ አፋጠጠኝ። መጠየቁ ልክ ሆኖ ሳለ ንግግሩ ትንሽ ከስርዓት የወጣ በመሆኑ ተበሳጨሁ !
"እና እዛ መገኘቴ ርካሽ ለመሆኔ ማረጋገጫ ነው እንዴ ?"
"እንደዛ እያልኩኝ ሳይሆን እዛ ቦታ ትገኛለሽ ብዬ አልጠበኩም ሲቀጥል ደግሞ እነ አቶ ሰለሞን ማለት እኮ እንኳን ዳይመንድ የተገኘች ሴት ቀርቶ መንገድ ላይ ፈገግ ያለችላቸውን ሴት ሳይቀር አልጋ ላይ ይዘው ካልወጡ እንቅልፍ እማይወስዳቸው ሴሰኞች ናቸው" .......ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጥኩት
"ስለዚህ በተዘዋዋሪ ከእነሱ ጋር ማደሬን እየነገርከኝ ነው ?"
"አልወጣኝም ግን ደግሞ ዳይመንድ መሄድሽ ግራ አጋብቶኛል... ጓደኞችሽስ የትኞቹ ናቸው አስተዋውቀሽኝም አሳይተሽኝም አታውቂም የዚህን ያህል የዳይመንድ ፈርጦች እስከመባል ያደረሳችሁ ነገር ምንድነው እውነተኛዋስ ቃልኪዳን ማናት እኔ ያፈቀርኳት ወይስ እነ ሰለሞን ያወሩላት ? መቼስ ዳይመንድ መፅሀፍ ቅዱስ አምብበሽላቸው አደለም የወደዱሽ" ብሎ ንቀት በተሞላበት አነጋገር አፈጠጠብኝ.... ከሱ ያልጠበቁት አወራር ስለሆነ ደርቄ ቀረሁ...
"ምነው እውነት ስለሆነ መልስ አጣሽ አደል" አለኝ
"ታውቃለህ አሁን አንተ ያልካትን ቃልኪዳን እምሆነው መልስ ከሰጠሁክ ነው ! አንድ ነገር ግን ልንገርህ አንተም ብትሆን ዳይመንድ የሄድከው እና የዚህን ያህል ስለ ዳይመንድ ያወከው ለቅዳሴ ሄደህ አይደለም ! አመሰግናለሁ" ብዬ ከመኪናው ወረድኩኝ....

እያለፈ የነበረ የላዳ ታክሲ አስቁሜ ወደ ቤቴ መሄድ ጀመርኩ.....በዚህ ልክ እንዴት ሰውን መገመት ቀላል ይሆናል ? ሳያዳምጡ ሳይጠይቁ ሳያረጋግጡ መፍረድ ቀላል ነው እንዴ ? ስለ እኔ በቅጡ እንኳን ሳያውቅ እንዴት እንዲህ ይናገረኛል.... በርግጥ ስለዳይመንድ ያወራው ሁሉ ልክ ነው ነገር ግን ዳይመንድ መገኘቴ ብቻ እንዴት የኔን ማንነት ያራክሰዋል ..... ቆይ እስር ቤት የገባ ሁሉ ወንጀለኛ ነው እንዴ ?  ቤተክርስቲያን የሄደ ሁሉ ፃድቅ ነው እንዴ ? ....  ሰው በዋለበት እና በለበሰው ነገር ሊገመገም ይገባል ብዬ አላስብም....በየትኛው ንፁህነታችን ነው በሌሎች ጫማ ውስጥ ተቀምጠን ፍርድ እምንሰጠው....ማንም ይሁን ማንም በህይወቱ ስለሚሆነው እና ሰለሚያደርገው ነገር ሊጠይቀውም ሊፈርድበትም እሚገባው የፈጠረው አምላኩ ብቻ ነው ባይ ነኝ።  ማይለፍ በዚህ ልክ አውርዶ ይመለከተኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር። ከሚፈርድብኝ ቀድሞ እኔ እንዳስረዳው በአግባቡ ቢጠይቀኝ አንድም ሳላስቀር እነገረው ነበር እሱ ግን ቀድሞ ወነጀለኝ።

"የኔ እህት ያልሽኝ ቦታ ደርሰናል" እሚል ድምፅ ከገባሁበት ሀሳብ አነቃኝ
"እእ እሺ አመሰግናለሁ"  ሂሳቡን ከፍዬ ስወርድ... "እናት"........ ብሎ መስኮቱን ከፈተና .....
"አንድ ነገር ማለት ፈልጌ ነበር ፍቃድሽ ከሆነ"..... አለኝ በተረጋጋ ድምፅ
" እሺ ምንድነው ?" መለስኩለት
"ስላንቺ ባላውቅም ያለቀሽበት ምክንያት ባይገባኝም እንባሽ ግን ለእውነተኛነትሽ ምስክር ነው። ለሰዎች ብለሽ እሚያምሩት አይኖችሽን አታድክሚያቸው....ሰላም እደሪ" አለኝ... ንግግሩ በጥቂጡም ቢሆን ፈገግ አስባለኝ።
"በጣም አመሰግናለሁ ፈጣሪ ያክብርልኝ ፤ አሜን ሰላም እደር" .....ብዬ ተሰናብቼው ወደ ቤቴ ገባሁ.....


ይቀጥላል.......

ቀጣዩ ክፍል ከ100❤️ በኋላ ይለቀቃል።



✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
       @Ketbeb_Mender 
       @Ketbeb_Mender 
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯

BY የብዕር ጠብታ✍📒📖


Share with your friend now:
tgoop.com/Ketbeb_mender/3556

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

In 2018, Telegram’s audience reached 200 million people, with 500,000 new users joining the messenger every day. It was launched for iOS on 14 August 2013 and Android on 20 October 2013. How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Telegram channels fall into two types: Add the logo from your device. Adjust the visible area of your image. Congratulations! Now your Telegram channel has a face Click “Save”.! As five out of seven counts were serious, Hui sentenced Ng to six years and six months in jail.
from us


Telegram የብዕር ጠብታ✍📒📖
FROM American