MGETEM Telegram 4775
#ውሸት_እናተንኮል
@Mgetem

ውሸትና ተንኮል ፣ ጓደኞች ነበሩ ፣
እውነትን ለማጥፋት ፣ እንዲህ ተማከሩ ።
እውነት የተባለው ፣ ይሄ ጠላታችን ፣
መጥፋት አለበት ፣ ጭራሽ ከዓለማችን ።
እኛ እየተጠላን ፣ እሱ እየተወደደ ፣
ብዙ ጊዜ አለፈ ፣ ዘመንም ነጎደ ።
የኛ ብቻ ይሁን ፣ መላው ሀገር ምድሩ ፣
ውሸትና ተንኮል ፣ እንዲህ ተማከሩ ።
ከዕለታት በአንዱ ቀን ፣ ተንኮል እያደባ ፣
ከውሸት ጋር ሆኖ ፣ ከእውነት ቤት ገባ ።
እውነት ከጓደኞቹ ፣ ሠላምና ፍቅር ፣
በደስታ በሀሴት ፣ ይጫወቱ ነበር ።
ተንኮልም በድንገት ፣ እውነትን ተማታ ፣
ፍቅርም አዘነ ፣ ሠላምም ተቆጣ ።
ውሸት ብቅ አለና ፣ ከተደበቀበት ፣
ከተንኮል ጋር ሆኖ ፣ እውነትን ገደሉት ።
ሠላምና ፍቅር ፣ እጅግ እያዘኑ ፣
እንቅበረው ዘንድ ፣ ስጡን አስከሬኑን ።
ብለው ተማጸኑ ፣ ውሸትን በእምባ ፣
እውነት ተቀበረ ከመቃብር ገባ ።
ዓለምን የመግዛት ፣ ብርቱ ዓላማችው ፣
ውሸትና ተንኮል ፣ ሞላ የልባቸው ።
አንድ ቀን ፣ አቶ ውሸት ተነስቶ በጧት ፣
የሰፈሩን ሰዎች ፣ ደስታ ሲመለከት ።
ተጠራጠረና ፣ ወደ ቀብሩ ሮጠ ፣
ልክ እንደደረሰ ፣ በጣም ደነገጠ ።
እውነት ተፈልጎ ፣ መቃብሩ ሲታይ ፣
ምንም ነገር የለም ፣ አንዳችም የሚታይ ።
አወይ ልፋታችን ፣ ተንኮል መጥተህ ብታይ ፣
እውነት ከቶ አልሞተም ፣ ዓርጎ ነው ሰማይ ።

እውነትና ዘይት ምንግዜም ከላይ ናቸው

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem



tgoop.com/Mgetem/4775
Create:
Last Update:

#ውሸት_እናተንኮል
@Mgetem

ውሸትና ተንኮል ፣ ጓደኞች ነበሩ ፣
እውነትን ለማጥፋት ፣ እንዲህ ተማከሩ ።
እውነት የተባለው ፣ ይሄ ጠላታችን ፣
መጥፋት አለበት ፣ ጭራሽ ከዓለማችን ።
እኛ እየተጠላን ፣ እሱ እየተወደደ ፣
ብዙ ጊዜ አለፈ ፣ ዘመንም ነጎደ ።
የኛ ብቻ ይሁን ፣ መላው ሀገር ምድሩ ፣
ውሸትና ተንኮል ፣ እንዲህ ተማከሩ ።
ከዕለታት በአንዱ ቀን ፣ ተንኮል እያደባ ፣
ከውሸት ጋር ሆኖ ፣ ከእውነት ቤት ገባ ።
እውነት ከጓደኞቹ ፣ ሠላምና ፍቅር ፣
በደስታ በሀሴት ፣ ይጫወቱ ነበር ።
ተንኮልም በድንገት ፣ እውነትን ተማታ ፣
ፍቅርም አዘነ ፣ ሠላምም ተቆጣ ።
ውሸት ብቅ አለና ፣ ከተደበቀበት ፣
ከተንኮል ጋር ሆኖ ፣ እውነትን ገደሉት ።
ሠላምና ፍቅር ፣ እጅግ እያዘኑ ፣
እንቅበረው ዘንድ ፣ ስጡን አስከሬኑን ።
ብለው ተማጸኑ ፣ ውሸትን በእምባ ፣
እውነት ተቀበረ ከመቃብር ገባ ።
ዓለምን የመግዛት ፣ ብርቱ ዓላማችው ፣
ውሸትና ተንኮል ፣ ሞላ የልባቸው ።
አንድ ቀን ፣ አቶ ውሸት ተነስቶ በጧት ፣
የሰፈሩን ሰዎች ፣ ደስታ ሲመለከት ።
ተጠራጠረና ፣ ወደ ቀብሩ ሮጠ ፣
ልክ እንደደረሰ ፣ በጣም ደነገጠ ።
እውነት ተፈልጎ ፣ መቃብሩ ሲታይ ፣
ምንም ነገር የለም ፣ አንዳችም የሚታይ ።
አወይ ልፋታችን ፣ ተንኮል መጥተህ ብታይ ፣
እውነት ከቶ አልሞተም ፣ ዓርጎ ነው ሰማይ ።

እውነትና ዘይት ምንግዜም ከላይ ናቸው

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem

BY መንፈሳዊ ግጥም ብቻ


Share with your friend now:
tgoop.com/Mgetem/4775

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

During a meeting with the president of the Supreme Electoral Court (TSE) on June 6, Telegram's Vice President Ilya Perekopsky announced the initiatives. According to the executive, Brazil is the first country in the world where Telegram is introducing the features, which could be expanded to other countries facing threats to democracy through the dissemination of false content. Informative Public channels are public to the internet, regardless of whether or not they are subscribed. A public channel is displayed in search results and has a short address (link). Write your hashtags in the language of your target audience. While the character limit is 255, try to fit into 200 characters. This way, users will be able to take in your text fast and efficiently. Reveal the essence of your channel and provide contact information. For example, you can add a bot name, link to your pricing plans, etc.
from us


Telegram መንፈሳዊ ግጥም ብቻ
FROM American