NUENSAK Telegram 1977
አሸንፈናል .....ግን ይርበናል::
ህመም -፪

በጦብያ ሰማይ ስር ከተጻፉ ኦቶባዮግራፊ መጽሐፍ እንደ ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለማርያም የተሳካለት የለም፡፡ የርሳቸውን የዘመን ውጣ ውረድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡ ለአሁን ግን ......

በኦቶባዮግራፊ መጽሐፋቸው ላይ ሰርክ ስለሚያስገርመኝ ነገር ላውራችሁ፡፡
ገጽ 69፡፡ የጦብያ ሌላኛው ገጽ፡፡

ከአድዋው ድል ማግስት ወደየቤቱ ወታደሩ ሲመለስ:- "....ወታደሮቻችን በሣጥን የተከተተውን ዕቃ እየበረበሩ ከውስጡ እያወጡ ሲሻሙ በሜዳው ሙሉ በየትም መነዛዘሩት፡፡ በሜዳው ላይ በየትም የተበታተነው ዕቃ ብዛቱ የአንድ የትልቅ ከተማ ዕቃ ያህላል፡፡
ተግዞ ተጭኖ የሚያልቅ አይመስልም፡፡ አይኖቼን አሰከራቸው፡፡ ስንቱ ተቆጥሮ ይዘለቃል፡፡ ጣልያኖችስ ይኸን ሁሉ ግሳንግስ በምን ጭነው አመጡት? ወይን ጠጅ -አረቄ-በያይነቱ ዱቄት-ማካሮኒ-ሱካር-ፎርማዥ-ሰርዲን-ኮንሴርቫበያይነቱ-ክብሪት-ሲጃራ-ሥዕል የተሳለበት ጋዜጣ-ብስኩት.....ይህን ሁሉ ጉድ አሞራው ወታደራችን ባንድ አፍታ አመሰቃቀለው፡፡ ይህ ሁኔታ ድል አድራጊዎቹን ፍጹም አስክሯቸዋል፡፡

ባንዲት ክብሪት ወይም ሴንጢ ወይም ብልቃጥ ጠርሙስ ወይም ሰዓት የተነሣ "እኔ ልውሰድ እኔ እብሳለሁ" በማለት እየተጣሉ ጎራዴ ይማዘዛሉ ይቋሰላሉ ይታኮሳሉ ይጋደላሉ፡፡ ባቢሎን እንደፈረሰች ጊዜ ሰዎች ቋንቋ ለቋንቋ ተሳሳቱ፡፡

ተቀምጬ ሳስተውል ብዙ ቆየሁ ከዛም መደባደቡ በረድ ሲል ጠበቅኩና እኔም የተራዬን ለመዝረፍ ተነሣሁ፡፡ ....." ይሉናል፡፡

*ከጦርነት ማግስት የተሸናፊውን ንብረት መውረስ ደንብ ቢሆንም የአድዋው ከዚህ የሚለው መጋደልም ጭምር መኖሩ ነው፡፡ (እንደፊታውራሪ አገላለፅ ከሆነ)

ከትውልድ ትውልድም የኛ መልክ ይኽው ነው፡፡ ድል በቀናን ማግስት መነጣጠቅ መዘረራረፍ፡፡ ያውም እርስበራሳችን፡፡

ድል አድርገናል በጦርነት፡፡ ድል አድርገውናል በድህነት፡፡ ችጋራችን ከዘመን ዘመን አለቀቀንም፡፡ መልካችን እስኪመስል ድረስ ተጣብቆናል፡፡ የወጣቱም ተስፋ የሽማግሌውም እርጅና የህፃናቱም መኮላተፍ ተዛንፏል፡፡

ተሰራርቀናል፡፡ ተቀማምተናል፡፡ ተነጣጥቀናል፡፡
ይሄም የኛ መልክ ነው እና እንቀበለዋለን፡፡

አሸንፈናል፡፡ ግን ይርበናል፡፡

* * * * * * * * *
Graphics:- simon



tgoop.com/Nuensak/1977
Create:
Last Update:

አሸንፈናል .....ግን ይርበናል::
ህመም -፪

በጦብያ ሰማይ ስር ከተጻፉ ኦቶባዮግራፊ መጽሐፍ እንደ ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለማርያም የተሳካለት የለም፡፡ የርሳቸውን የዘመን ውጣ ውረድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡ ለአሁን ግን ......

በኦቶባዮግራፊ መጽሐፋቸው ላይ ሰርክ ስለሚያስገርመኝ ነገር ላውራችሁ፡፡
ገጽ 69፡፡ የጦብያ ሌላኛው ገጽ፡፡

ከአድዋው ድል ማግስት ወደየቤቱ ወታደሩ ሲመለስ:- "....ወታደሮቻችን በሣጥን የተከተተውን ዕቃ እየበረበሩ ከውስጡ እያወጡ ሲሻሙ በሜዳው ሙሉ በየትም መነዛዘሩት፡፡ በሜዳው ላይ በየትም የተበታተነው ዕቃ ብዛቱ የአንድ የትልቅ ከተማ ዕቃ ያህላል፡፡
ተግዞ ተጭኖ የሚያልቅ አይመስልም፡፡ አይኖቼን አሰከራቸው፡፡ ስንቱ ተቆጥሮ ይዘለቃል፡፡ ጣልያኖችስ ይኸን ሁሉ ግሳንግስ በምን ጭነው አመጡት? ወይን ጠጅ -አረቄ-በያይነቱ ዱቄት-ማካሮኒ-ሱካር-ፎርማዥ-ሰርዲን-ኮንሴርቫበያይነቱ-ክብሪት-ሲጃራ-ሥዕል የተሳለበት ጋዜጣ-ብስኩት.....ይህን ሁሉ ጉድ አሞራው ወታደራችን ባንድ አፍታ አመሰቃቀለው፡፡ ይህ ሁኔታ ድል አድራጊዎቹን ፍጹም አስክሯቸዋል፡፡

ባንዲት ክብሪት ወይም ሴንጢ ወይም ብልቃጥ ጠርሙስ ወይም ሰዓት የተነሣ "እኔ ልውሰድ እኔ እብሳለሁ" በማለት እየተጣሉ ጎራዴ ይማዘዛሉ ይቋሰላሉ ይታኮሳሉ ይጋደላሉ፡፡ ባቢሎን እንደፈረሰች ጊዜ ሰዎች ቋንቋ ለቋንቋ ተሳሳቱ፡፡

ተቀምጬ ሳስተውል ብዙ ቆየሁ ከዛም መደባደቡ በረድ ሲል ጠበቅኩና እኔም የተራዬን ለመዝረፍ ተነሣሁ፡፡ ....." ይሉናል፡፡

*ከጦርነት ማግስት የተሸናፊውን ንብረት መውረስ ደንብ ቢሆንም የአድዋው ከዚህ የሚለው መጋደልም ጭምር መኖሩ ነው፡፡ (እንደፊታውራሪ አገላለፅ ከሆነ)

ከትውልድ ትውልድም የኛ መልክ ይኽው ነው፡፡ ድል በቀናን ማግስት መነጣጠቅ መዘረራረፍ፡፡ ያውም እርስበራሳችን፡፡

ድል አድርገናል በጦርነት፡፡ ድል አድርገውናል በድህነት፡፡ ችጋራችን ከዘመን ዘመን አለቀቀንም፡፡ መልካችን እስኪመስል ድረስ ተጣብቆናል፡፡ የወጣቱም ተስፋ የሽማግሌውም እርጅና የህፃናቱም መኮላተፍ ተዛንፏል፡፡

ተሰራርቀናል፡፡ ተቀማምተናል፡፡ ተነጣጥቀናል፡፡
ይሄም የኛ መልክ ነው እና እንቀበለዋለን፡፡

አሸንፈናል፡፡ ግን ይርበናል፡፡

* * * * * * * * *
Graphics:- simon

BY ኑ እንሳቅ😂😂😂


Share with your friend now:
tgoop.com/Nuensak/1977

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A Telegram channel is used for various purposes, from sharing helpful content to implementing a business strategy. In addition, you can use your channel to build and improve your company image, boost your sales, make profits, enhance customer loyalty, and more. bank east asia october 20 kowloon Ng, who had pleaded not guilty to all charges, had been detained for more than 20 months. His channel was said to have contained around 120 messages and photos that incited others to vandalise pro-government shops and commit criminal damage targeting police stations. Other crimes that the SUCK Channel incited under Ng’s watch included using corrosive chemicals to make explosives and causing grievous bodily harm with intent. The court also found Ng responsible for calling on people to assist protesters who clashed violently with police at several universities in November 2019. 3How to create a Telegram channel?
from us


Telegram ኑ እንሳቅ😂😂😂
FROM American