NUENSAK Telegram 2000
እንደዚህ ብናስበውስ....

ኤልያስ ሽታኹን
*         *         *        *        *      *      *


*የኖቤል ሽልማት መስራቹ  አልፍሬድ ኖቤል ሞቷል ተብሎ ጋዜጣ ላይ ወጣ፡፡ ሞቷል የተባለው ኖቤል የገዛ የሞቱን ዜና በገዛ ቤቱ ቁጭ ብሎ አነበበው፡፡ የተሳሳተ ዜና ነበር፡፡ ወንድሙ ነበር የሞተው፡፡ ኖቤል ግን ጋዜጣው ላይ የወጣው ርዕሰ አንቀጽ ነበር ያስደነገጠው፡፡
"በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ብዙ ሰዎችን በአንዴ የሚፈጀ ፈጠራ በመፈልሰፍ ሀብታም ለመሆን የበቃው ዶ/ር አልፍሬድ ኖቤል በትናንትናው ዕለት አረፈ"  ይላል ጋዜጣው፡፡

ኖቤል ከዚህ በኃላ  እንቅልፍ አጣ፡፡ ቢሞት ኖሮ ዓለም የሚያስታውሰው በዚህ ስም ነበርና ከነበረበት ቅዠት የተሳሳተው ጋዜጣው አነቃው በዚህም ሳቢያ ዓለም በሰላም እና በደግ በደጉ እንዲያስታውሰው "ኖቤል" ሽልማትን መሰረተ፡፡ ለዓለም እና ለሰው ልጆች መልካም ያበረከቱ የሚሸለሙበት ትልቁ ሽልማት ተባለለት፡፡


እንደዚህ ብናስበውስ

የከተማው ሰዎች የሚሳለቁበት ሰው ቢፈልጉ አንድ ሞኝ አገኙ፡፡  "ከዚያ  ከተራራው ካለው በረዶ በላይ ከሚቀዘቅዘው ኩሬ ለረዥም ሰዓት ከዋኘህ ገጣሚ ትሆናለህ" አሉት፡፡
እሱም ያሉት አደረገ፡፡ ገጣሚ ግን አልሆነም፡፡
ሳቁበት፡፡ ተጠቋቆሙበት፡፡ ቆይቶ ነው እያፌዙበት መሆኑንም ያወቀው፡፡ ሞኝ አይደለ፡፡

አኮረፋቸው፡፡ ተቀየማቸው፡፡ ትቷቸው ሸሸ፡፡ ውሎውን ጫካና ከሸንተረሮቹ ከተራሮቹ አደረገ፡፡ ከሰው ተሸሸገ፡፡
ሲያኮርፋቸው በብቸኝነት ሲከርም ብዙ አሰበ፡፡ አሰላሰለ፡፡

ሲመለስ ወደከተማው የሀገሩ ትልቁ ገጣሚ ሆኖ ነበር፡፡
ገባኝ ያለውን ሲናገር ሁሉ አፉን ከፍቶ ይሰማው ጀመር፡፡ የኢራኑ የግጥም አማልክት መሃል ደረሰ፡፡ ብቸኛ ሲሆን የተመኘውን ሆነ፡፡
* ታላቁ ገጣሚ ባባ ጣሂር፡፡

እንደዚህ ብናስበውስ

* ኦገስት ስትሪንበርግ የተባለው ሰውየ በክፉ ስራው ምክንያት አንድ ምርጥ ደራሲ ለዓለም አበርክቷል፡፡ ያ ክፉ ስራው ምን እንደሆነ በግልፅ የተቀመጠ ነገር የለውም፡፡
ግን የኖርዌው ታላቁ ፀሐፌ ተውኔት እና መራሄ ተውኔት ትልልቅ ድርሰቱን የሚጽፈው የጠላቱን
የ'ኦገስት ስሪንበርግ' ፎቶ ፊት ለፊቱ አስቀምጦ ነበር፡፡ መነሸጫው ማሰላሰያው የዚሁ ሰው ፎቶ ነበር፡፡ የበደለውን ሰውየ እያየ ነበር ብዙ ሀሳብ የሚመጣለት፡፡ ጠላቱ ይነሽጠው ነበረ፡፡
ደራሲ ሄነሪክ ጆሀን ኢብሰን፡፡
"the father or realism" ተብላል በዘመኑ፡፡
(1828 ተወልዶ 1906 ላይ በ78 ዓመቱ አርፏል)

እንደዚህ ብናስበውስ

* በባርነት ዘመኑ ሁሉ ደግ የሚላት የጌታውን ሚስት ነው፡፡ ጌታው ቢጨክንበትም ሚስቱ ግን ታቀርበው ነበርና ፊደል ታስተምረው ነበር፡፡ ይሄንን የደረሰባት ባሏ አብዝቶ ተቆጣት፡፡ "ባሪያ ነው እኮ፡፡ አንቺ ካስተማርሽው ያውቃል፡፡ ካወቀ ይጠይቃል፡፡ ከጠየቅ ባርነቱን ይጠላል፡፡ እና እንዴት ታስተምሪዋለሽ?" ብሎ ተቆጣት፡፡ ለካ ባሪያው ፍሬድሪክ ዳግላስ ከጓዳ ሰምቶ ኖሮ ከጠላቱ ቁጣ የዘላለም ብርሃን በራለት፡፡ "ዕውቀት"
አሻፈረኝ አለ፡፡ ተማረ፡፡ አወቀ፡፡ በጥቁሮች ታሪክ ትልቁ ታጋይ ዳግላስ ተባለ፡፡
(1817-1895 በ78 ዓመቱ አርፏል)


እንደዚህ ብናስበውስ

* አደራ በል ጓደኛው ነው ለዓለም ውለታ የዋለለን፡፡ ታዋቂው ደራሲው ፍራንስ ካፍካ ብቸኝነት ነበር መለያው፡፡ ጥቂት ጓደኞች ብቻ ናቸው የነበሩት፡፡ በሳምባ ነቀርሳ ነው የሞተው፡፡ በአጫጭር እና በረጅም ልብወለዱ ታዋቂ ነው፡፡ የጻፋቸው ስራዎች ሁሉ ተሰብስብስበው እንዲቃጠሉ በኑዛዜው ላይ ተናግሮ ነበር፡፡ ነገር ግን 'ማክስ ብሮድ' የተባለው ጓደኛው አደራውን በላ፡፡ ያለካፍካ ፍቃድ እንዲታተሙ አደረገ፡፡  እንዲነበቡ ዓለም እንዲገረምባቸው ሆነ፡፡ አንባብያን ሁሉ "ይሄን የመሰለ ጽሑፍ ነበር ይቃጠል ያለው" ብለው ካፍካ ላይ ተገረሙበት፡፡ ጓደኛውን በልባቸው አመሰገኑት፡፡
(1883-1924 በ40 ዓመቱ አረፏል)


እንደዚህ ብናስበውስ

* አድባረ ግጥም ጸጋዬ ገብረመድኅን የእናቱ መሬት በጉልበተኞች  መሬት ተነጥቀው አጥር ፈርሶባቸው ከብቶቻቸው ይበተኑባቸው ስለነበር ነው፡፡ እንደልጅ  ይነደው ነበርና ይሄን በህግ ሊያስመልስ በቺካጎ ህግ አጥንቶ መጣ፡፡
ሲመለስ የእናቱ መሬት ብቻ ሳይሆን የሀገሬው ደሀ መሬት ሁሉ በጉልበተኞች ተወርሷልና ትግሉን
ለተበደሉ ድሆች ሁሉ አደረገ፡፡
ያውም በጥበብ አደባባይ፡፡ ያውም በግጥም አደባባይ፡፡ ለእናቱ ፍትሕ የተነሳው ጸጋዬ ወኔ ለእናት ሀገሩ ዘለቀ፡፡
(1928-1998)



*         *       *         *         *        *       *
ዋቢ
* ግሩም የዓለማችን ምርጥ ታሪኮች
ግሩም ተበጀ
*የመንፈስ ከፍታ
በረከት በላይነህ
*ጣዝማ:- አስደናቂው የደራሲያን ሕይወት
ንጉሤ አየለ እና ደጀኔ ጥላሁን
*ሸገር ራድዮ
መቆያ
*ከሕግ ፊት እና ሌሎችም
GOETHE-INSTITUT
*ምስጥረኛው ባለቅኔ
ሚካኤል ሽፈራው



tgoop.com/Nuensak/2000
Create:
Last Update:

እንደዚህ ብናስበውስ....

ኤልያስ ሽታኹን
*         *         *        *        *      *      *


*የኖቤል ሽልማት መስራቹ  አልፍሬድ ኖቤል ሞቷል ተብሎ ጋዜጣ ላይ ወጣ፡፡ ሞቷል የተባለው ኖቤል የገዛ የሞቱን ዜና በገዛ ቤቱ ቁጭ ብሎ አነበበው፡፡ የተሳሳተ ዜና ነበር፡፡ ወንድሙ ነበር የሞተው፡፡ ኖቤል ግን ጋዜጣው ላይ የወጣው ርዕሰ አንቀጽ ነበር ያስደነገጠው፡፡
"በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ብዙ ሰዎችን በአንዴ የሚፈጀ ፈጠራ በመፈልሰፍ ሀብታም ለመሆን የበቃው ዶ/ር አልፍሬድ ኖቤል በትናንትናው ዕለት አረፈ"  ይላል ጋዜጣው፡፡

ኖቤል ከዚህ በኃላ  እንቅልፍ አጣ፡፡ ቢሞት ኖሮ ዓለም የሚያስታውሰው በዚህ ስም ነበርና ከነበረበት ቅዠት የተሳሳተው ጋዜጣው አነቃው በዚህም ሳቢያ ዓለም በሰላም እና በደግ በደጉ እንዲያስታውሰው "ኖቤል" ሽልማትን መሰረተ፡፡ ለዓለም እና ለሰው ልጆች መልካም ያበረከቱ የሚሸለሙበት ትልቁ ሽልማት ተባለለት፡፡


እንደዚህ ብናስበውስ

የከተማው ሰዎች የሚሳለቁበት ሰው ቢፈልጉ አንድ ሞኝ አገኙ፡፡  "ከዚያ  ከተራራው ካለው በረዶ በላይ ከሚቀዘቅዘው ኩሬ ለረዥም ሰዓት ከዋኘህ ገጣሚ ትሆናለህ" አሉት፡፡
እሱም ያሉት አደረገ፡፡ ገጣሚ ግን አልሆነም፡፡
ሳቁበት፡፡ ተጠቋቆሙበት፡፡ ቆይቶ ነው እያፌዙበት መሆኑንም ያወቀው፡፡ ሞኝ አይደለ፡፡

አኮረፋቸው፡፡ ተቀየማቸው፡፡ ትቷቸው ሸሸ፡፡ ውሎውን ጫካና ከሸንተረሮቹ ከተራሮቹ አደረገ፡፡ ከሰው ተሸሸገ፡፡
ሲያኮርፋቸው በብቸኝነት ሲከርም ብዙ አሰበ፡፡ አሰላሰለ፡፡

ሲመለስ ወደከተማው የሀገሩ ትልቁ ገጣሚ ሆኖ ነበር፡፡
ገባኝ ያለውን ሲናገር ሁሉ አፉን ከፍቶ ይሰማው ጀመር፡፡ የኢራኑ የግጥም አማልክት መሃል ደረሰ፡፡ ብቸኛ ሲሆን የተመኘውን ሆነ፡፡
* ታላቁ ገጣሚ ባባ ጣሂር፡፡

እንደዚህ ብናስበውስ

* ኦገስት ስትሪንበርግ የተባለው ሰውየ በክፉ ስራው ምክንያት አንድ ምርጥ ደራሲ ለዓለም አበርክቷል፡፡ ያ ክፉ ስራው ምን እንደሆነ በግልፅ የተቀመጠ ነገር የለውም፡፡
ግን የኖርዌው ታላቁ ፀሐፌ ተውኔት እና መራሄ ተውኔት ትልልቅ ድርሰቱን የሚጽፈው የጠላቱን
የ'ኦገስት ስሪንበርግ' ፎቶ ፊት ለፊቱ አስቀምጦ ነበር፡፡ መነሸጫው ማሰላሰያው የዚሁ ሰው ፎቶ ነበር፡፡ የበደለውን ሰውየ እያየ ነበር ብዙ ሀሳብ የሚመጣለት፡፡ ጠላቱ ይነሽጠው ነበረ፡፡
ደራሲ ሄነሪክ ጆሀን ኢብሰን፡፡
"the father or realism" ተብላል በዘመኑ፡፡
(1828 ተወልዶ 1906 ላይ በ78 ዓመቱ አርፏል)

እንደዚህ ብናስበውስ

* በባርነት ዘመኑ ሁሉ ደግ የሚላት የጌታውን ሚስት ነው፡፡ ጌታው ቢጨክንበትም ሚስቱ ግን ታቀርበው ነበርና ፊደል ታስተምረው ነበር፡፡ ይሄንን የደረሰባት ባሏ አብዝቶ ተቆጣት፡፡ "ባሪያ ነው እኮ፡፡ አንቺ ካስተማርሽው ያውቃል፡፡ ካወቀ ይጠይቃል፡፡ ከጠየቅ ባርነቱን ይጠላል፡፡ እና እንዴት ታስተምሪዋለሽ?" ብሎ ተቆጣት፡፡ ለካ ባሪያው ፍሬድሪክ ዳግላስ ከጓዳ ሰምቶ ኖሮ ከጠላቱ ቁጣ የዘላለም ብርሃን በራለት፡፡ "ዕውቀት"
አሻፈረኝ አለ፡፡ ተማረ፡፡ አወቀ፡፡ በጥቁሮች ታሪክ ትልቁ ታጋይ ዳግላስ ተባለ፡፡
(1817-1895 በ78 ዓመቱ አርፏል)


እንደዚህ ብናስበውስ

* አደራ በል ጓደኛው ነው ለዓለም ውለታ የዋለለን፡፡ ታዋቂው ደራሲው ፍራንስ ካፍካ ብቸኝነት ነበር መለያው፡፡ ጥቂት ጓደኞች ብቻ ናቸው የነበሩት፡፡ በሳምባ ነቀርሳ ነው የሞተው፡፡ በአጫጭር እና በረጅም ልብወለዱ ታዋቂ ነው፡፡ የጻፋቸው ስራዎች ሁሉ ተሰብስብስበው እንዲቃጠሉ በኑዛዜው ላይ ተናግሮ ነበር፡፡ ነገር ግን 'ማክስ ብሮድ' የተባለው ጓደኛው አደራውን በላ፡፡ ያለካፍካ ፍቃድ እንዲታተሙ አደረገ፡፡  እንዲነበቡ ዓለም እንዲገረምባቸው ሆነ፡፡ አንባብያን ሁሉ "ይሄን የመሰለ ጽሑፍ ነበር ይቃጠል ያለው" ብለው ካፍካ ላይ ተገረሙበት፡፡ ጓደኛውን በልባቸው አመሰገኑት፡፡
(1883-1924 በ40 ዓመቱ አረፏል)


እንደዚህ ብናስበውስ

* አድባረ ግጥም ጸጋዬ ገብረመድኅን የእናቱ መሬት በጉልበተኞች  መሬት ተነጥቀው አጥር ፈርሶባቸው ከብቶቻቸው ይበተኑባቸው ስለነበር ነው፡፡ እንደልጅ  ይነደው ነበርና ይሄን በህግ ሊያስመልስ በቺካጎ ህግ አጥንቶ መጣ፡፡
ሲመለስ የእናቱ መሬት ብቻ ሳይሆን የሀገሬው ደሀ መሬት ሁሉ በጉልበተኞች ተወርሷልና ትግሉን
ለተበደሉ ድሆች ሁሉ አደረገ፡፡
ያውም በጥበብ አደባባይ፡፡ ያውም በግጥም አደባባይ፡፡ ለእናቱ ፍትሕ የተነሳው ጸጋዬ ወኔ ለእናት ሀገሩ ዘለቀ፡፡
(1928-1998)



*         *       *         *         *        *       *
ዋቢ
* ግሩም የዓለማችን ምርጥ ታሪኮች
ግሩም ተበጀ
*የመንፈስ ከፍታ
በረከት በላይነህ
*ጣዝማ:- አስደናቂው የደራሲያን ሕይወት
ንጉሤ አየለ እና ደጀኔ ጥላሁን
*ሸገር ራድዮ
መቆያ
*ከሕግ ፊት እና ሌሎችም
GOETHE-INSTITUT
*ምስጥረኛው ባለቅኔ
ሚካኤል ሽፈራው

BY ኑ እንሳቅ😂😂😂


Share with your friend now:
tgoop.com/Nuensak/2000

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Ng Man-ho, a 27-year-old computer technician, was convicted last month of seven counts of incitement charges after he made use of the 100,000-member Chinese-language channel that he runs and manages to post "seditious messages," which had been shut down since August 2020. Matt Hussey, editorial director of NEAR Protocol (and former editor-in-chief of Decrypt) responded to the news of the Telegram group with “#meIRL.” “[The defendant] could not shift his criminal liability,” Hui said. Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months. Just at this time, Bitcoin and the broader crypto market have dropped to new 2022 lows. The Bitcoin price has tanked 10 percent dropping to $20,000. On the other hand, the altcoin space is witnessing even more brutal correction. Bitcoin has dropped nearly 60 percent year-to-date and more than 70 percent since its all-time high in November 2021.
from us


Telegram ኑ እንሳቅ😂😂😂
FROM American