ONLYFORTRUTHERSJ Telegram 3099
🤪እብዱ ደራሲ

#ተከታታይ ልቦለድ📖

#ክፍል አምስት(5)


እኔና ሰሙ የደወለችው ኡሚ መሆኗን ስናውቅ በድንጋጤ ቆመን ቀረን መንገድ ላይ ስለሆነ ያለነው ማንሳት አልፈለኩም ኡሚ ስለ ማሂር ምንም አለች ምን መንገድ ላይ መሆኑን አልፈለኩትም ሰሙም ሀሳቤን ተጋርታለች ኡሚ ደጋግማ ብትደውልም ቢሮ እስክንገባ ላለማንሳት ወስነናል ሁለታችንም ውስጣችን በፍርሀት ተሞልቷል።
እንዴትም ብለን ቢሮ ስንደርስ የቢሮውን በር ክፍት አገኘነው ሁለታችንም በድንጋጤ እና በመሰላቸት አይነት ተያየን በቃ ሰውዬሽ መቶ ይሆናል አለችኝ።ኤጭ ባልጠፋ ቀን በዚ ሰዐት ይመጣል ምኑ ብሽቅ ነው በአላህ አልኳት የሚከተለንን የስራ ብዛት እያሰብኩ፤አለቃችን በእድሜ ብዙም አይበልጠንም ነገር ግን ነገረ ስራው ሁላ የሽማግሌ ነው መነጫነጭ ይወዳል።ሰሞኑ እቃ ለማምጣት ወደ ዱባይ ሄዶ ስለነበር ተገላግለነው ነበር ደግሞ ሳይናገር ነው የሚመጣው እሱ እዚ ቢሮ አለ ማለት ማውራት የለ መሳቅ የለ መውጣት መግባት የለ ከእኔ ጋርማ የሆነ ጂኒ አያይዞታል ሲሀም እንዲ ሆነ ሲሀም እንደዛ ሆነ ሲሀም በዚ ገባ ሲሀም በዚ ወጣ🤦‍♀በደቂቃዎች ውስጥ 50ጊዜ ነው ስሜን ሚጠራው በሱ የተነሳ ስሜን ሁላ ጠልቼዋለው አንዳንዴማ ከኔ ውጪ ሰራተኛ ያለ እስከማይመስለኝ ድረስ እበሳጫለው።ሌላ ቅርንጫፍ ቢኖረውም እሱ ግን እዚ ያዘወትራል አሁንማ ጭራሽ ከአጠገባችን ያለውን ቢሮ የራሱ ሊያደርገው እያሳደሰው ነው እሱ እዚ ቢሮ የገባ ቀን እኔ ስራ አቆማለው ስላት ሰሙ ትስቃለች ስለሚወድሽ እኮ ነው ትለኛለች ለዛም ነው ሰውዬሽ ምትለኝ እኔ ግን አሁን ከስራው እና ከአለቃችን በላይ የማሂር ነገር ነው ያሳሰበኝ ቢሮ ከገባን ቡሀላ መደወል ስለማልችል አሁን እንደውልላት አልኳት ሰሙ ምንም እንኳን የማሂር ነገር ቢያሳስባትም ኡሚን በተጣደፈ አነጋገር ማናገሩን አልወደደችውም ለምሳ መውጣቱ ስለማይቀር በዛ ሰዐት እንደውላለን ባይሆን እንዳትጨነቅ አለቃችን እንደመጣ ንገሪያት ስራ እንደሚበዛ ይገባታል ብላኝ ለኡሚ ደወልኩላት ግን ለማናገር ድፍረቱን ስላጣው ለሰሙ ሰጠሗት ሰሙ የኡሚን ድምፅ ስትሰማ ፊቷ ተቀያየረ ግን እንዳልነቃ ስለፈለገች በግድ ለመሳቅ ሞከረች ነገሩ ግራ ስለገባኝ ስልኩን ተቀብዬ ኡሚ ደና ነሽ?አልኳት።ኡሚ ድምፄን ስትሰማ እንደደነገጠች ድምጿ ያሳብቅባታል ከኡሚ ጀርባ ደግሞ ለቅሶም አይሉት ሳቅ የሚመስል ድምፅ ይሰማኛል አሁን ከቅድሙ በበለጠ ልቤ በፍርሀት ልትፈነዳ ደርሳለች ደና ነኝ ሲሁ እንዴት ዋልሽልኝ እህትሽ እኮ አለቃቹ እንደመጣ ነገረችኝ ስራ ይበዛባቹሀል በቃ ካልሆነ ቤት ቶሎ ኑ ምትወዱትን ምሳ ሰርቼ እጠብቃቹሀለው ብላ ምንም መልስ እንዳልሰጣት በሚመስል መልኩ ስልኩን ጆሮዬ ላይ ጠረቀመችብች።ይሄ የኡሚ የሁል ጊዜ ንግግር መሆኑን ባውቅም የዛሬው ግን የሀዘንና የስስት ነገር አለበት።አሁን የበለጠ ልቤ ፈርቷል ያ የተመታ ሰውዬ ባይመጣ ኖሮ ቤት እንሄድ ነበር አሁን ግን ግዴታ ነው ከሰሙ ጋር ወደ ውስጥ ገባን።ገና ከመግባታችን እሺ ማጂላኖች በስራ ሰዐት እንኳን አትቀመጡም ብሎ በነገር ለኮሰን ምን አለ አሁን ከዱባይ ነው የመጣው ሰላምታው አይቀድምም የተረገመ ሼባ ብዬ በውስጤ ተሳድቤ ወደ ቦታዬ ሄጄ ተቀመጥኩ ገና ከመቀመጣችን የስራ order ጀመረ በቃ እኔና ሰሙ የማሂርን ነገር ባንረሳውም ግን አሁን 75% የሚሆነው ሀሳባችን ስራው ላይ ሆኗል ሳናውቀው 9ሰዐት ሆኗል ለካ አረ እንስገድ አለች ሰሙ በዛውም ምሳ እንብላ አይነት መልዕክት በቃ በተራ ተራ ስገዱ ምሳ ደግሞ እኔ ነኝ ምጋብዛቹ እዚሁ አብረን እንበላለን ብሎ የኛን ፍቃድ ሳይጠይቅ ልዘዝ ብሎ ወጣ ምሳ ሰዐት ላይ ኡሚ ጋር እንደውላለን ብለን የነበረ ቢሆንም ይሄ ሰውዬ አልፈታም አለን ሁለታችንም የየራሳችንን ስድብ አወረድንበትና ለኡዱ ወጣን በተራተራ ሰገድን እና ምሳችንን በልተን ወደ ስራችን ተመለስን አሁንም ሳናውቀው 12ሰዐት ሆነ ኡሚም ደወለች በድንጋጤ ሰሙን ቀና ብዬ አየሗት አለቃችንም ስለነበር ማውራት ቢደብረኝም ስልኩን አንስቼ ወዬ ኡሚ አልኳት እናንተ ልጆች ቡናው እኮ ቀዘቀዘ አለችኝ መጣን መጣን ኡሚዬ ልንወጣ ነው አልኳት በዛውም ለሰሙ እንውጣ ለአዩብ ደግሞ ልንወጣ ነው የሚል መልዕክት እያስተላለፍኩ ስልኩን ስዘጋው በቃ ሂዱ ጠዋት በጠዋት ኑ እና ትጨርሱታላቹ አለን ማስጠንቀቂያ መሆኑ ነው።እሺ ደና እደር ብለን ተያይዘን ውልቅ አልን ሁለታችንም እቤት እስክንደርስ ቸኩለናል ምንም ባያገባንም ስለ ማሂር ማወቅ ፈልገናል ኡሚ ስለማሂር ምን ትለን ይሆን?ምን ሆኖ ይሆን.........?



..........ይቀጥላል...........



https://www.tgoop.com/tesefgna



tgoop.com/ONLYFORTRUTHERSJ/3099
Create:
Last Update:

🤪እብዱ ደራሲ

#ተከታታይ ልቦለድ📖

#ክፍል አምስት(5)


እኔና ሰሙ የደወለችው ኡሚ መሆኗን ስናውቅ በድንጋጤ ቆመን ቀረን መንገድ ላይ ስለሆነ ያለነው ማንሳት አልፈለኩም ኡሚ ስለ ማሂር ምንም አለች ምን መንገድ ላይ መሆኑን አልፈለኩትም ሰሙም ሀሳቤን ተጋርታለች ኡሚ ደጋግማ ብትደውልም ቢሮ እስክንገባ ላለማንሳት ወስነናል ሁለታችንም ውስጣችን በፍርሀት ተሞልቷል።
እንዴትም ብለን ቢሮ ስንደርስ የቢሮውን በር ክፍት አገኘነው ሁለታችንም በድንጋጤ እና በመሰላቸት አይነት ተያየን በቃ ሰውዬሽ መቶ ይሆናል አለችኝ።ኤጭ ባልጠፋ ቀን በዚ ሰዐት ይመጣል ምኑ ብሽቅ ነው በአላህ አልኳት የሚከተለንን የስራ ብዛት እያሰብኩ፤አለቃችን በእድሜ ብዙም አይበልጠንም ነገር ግን ነገረ ስራው ሁላ የሽማግሌ ነው መነጫነጭ ይወዳል።ሰሞኑ እቃ ለማምጣት ወደ ዱባይ ሄዶ ስለነበር ተገላግለነው ነበር ደግሞ ሳይናገር ነው የሚመጣው እሱ እዚ ቢሮ አለ ማለት ማውራት የለ መሳቅ የለ መውጣት መግባት የለ ከእኔ ጋርማ የሆነ ጂኒ አያይዞታል ሲሀም እንዲ ሆነ ሲሀም እንደዛ ሆነ ሲሀም በዚ ገባ ሲሀም በዚ ወጣ🤦‍♀በደቂቃዎች ውስጥ 50ጊዜ ነው ስሜን ሚጠራው በሱ የተነሳ ስሜን ሁላ ጠልቼዋለው አንዳንዴማ ከኔ ውጪ ሰራተኛ ያለ እስከማይመስለኝ ድረስ እበሳጫለው።ሌላ ቅርንጫፍ ቢኖረውም እሱ ግን እዚ ያዘወትራል አሁንማ ጭራሽ ከአጠገባችን ያለውን ቢሮ የራሱ ሊያደርገው እያሳደሰው ነው እሱ እዚ ቢሮ የገባ ቀን እኔ ስራ አቆማለው ስላት ሰሙ ትስቃለች ስለሚወድሽ እኮ ነው ትለኛለች ለዛም ነው ሰውዬሽ ምትለኝ እኔ ግን አሁን ከስራው እና ከአለቃችን በላይ የማሂር ነገር ነው ያሳሰበኝ ቢሮ ከገባን ቡሀላ መደወል ስለማልችል አሁን እንደውልላት አልኳት ሰሙ ምንም እንኳን የማሂር ነገር ቢያሳስባትም ኡሚን በተጣደፈ አነጋገር ማናገሩን አልወደደችውም ለምሳ መውጣቱ ስለማይቀር በዛ ሰዐት እንደውላለን ባይሆን እንዳትጨነቅ አለቃችን እንደመጣ ንገሪያት ስራ እንደሚበዛ ይገባታል ብላኝ ለኡሚ ደወልኩላት ግን ለማናገር ድፍረቱን ስላጣው ለሰሙ ሰጠሗት ሰሙ የኡሚን ድምፅ ስትሰማ ፊቷ ተቀያየረ ግን እንዳልነቃ ስለፈለገች በግድ ለመሳቅ ሞከረች ነገሩ ግራ ስለገባኝ ስልኩን ተቀብዬ ኡሚ ደና ነሽ?አልኳት።ኡሚ ድምፄን ስትሰማ እንደደነገጠች ድምጿ ያሳብቅባታል ከኡሚ ጀርባ ደግሞ ለቅሶም አይሉት ሳቅ የሚመስል ድምፅ ይሰማኛል አሁን ከቅድሙ በበለጠ ልቤ በፍርሀት ልትፈነዳ ደርሳለች ደና ነኝ ሲሁ እንዴት ዋልሽልኝ እህትሽ እኮ አለቃቹ እንደመጣ ነገረችኝ ስራ ይበዛባቹሀል በቃ ካልሆነ ቤት ቶሎ ኑ ምትወዱትን ምሳ ሰርቼ እጠብቃቹሀለው ብላ ምንም መልስ እንዳልሰጣት በሚመስል መልኩ ስልኩን ጆሮዬ ላይ ጠረቀመችብች።ይሄ የኡሚ የሁል ጊዜ ንግግር መሆኑን ባውቅም የዛሬው ግን የሀዘንና የስስት ነገር አለበት።አሁን የበለጠ ልቤ ፈርቷል ያ የተመታ ሰውዬ ባይመጣ ኖሮ ቤት እንሄድ ነበር አሁን ግን ግዴታ ነው ከሰሙ ጋር ወደ ውስጥ ገባን።ገና ከመግባታችን እሺ ማጂላኖች በስራ ሰዐት እንኳን አትቀመጡም ብሎ በነገር ለኮሰን ምን አለ አሁን ከዱባይ ነው የመጣው ሰላምታው አይቀድምም የተረገመ ሼባ ብዬ በውስጤ ተሳድቤ ወደ ቦታዬ ሄጄ ተቀመጥኩ ገና ከመቀመጣችን የስራ order ጀመረ በቃ እኔና ሰሙ የማሂርን ነገር ባንረሳውም ግን አሁን 75% የሚሆነው ሀሳባችን ስራው ላይ ሆኗል ሳናውቀው 9ሰዐት ሆኗል ለካ አረ እንስገድ አለች ሰሙ በዛውም ምሳ እንብላ አይነት መልዕክት በቃ በተራ ተራ ስገዱ ምሳ ደግሞ እኔ ነኝ ምጋብዛቹ እዚሁ አብረን እንበላለን ብሎ የኛን ፍቃድ ሳይጠይቅ ልዘዝ ብሎ ወጣ ምሳ ሰዐት ላይ ኡሚ ጋር እንደውላለን ብለን የነበረ ቢሆንም ይሄ ሰውዬ አልፈታም አለን ሁለታችንም የየራሳችንን ስድብ አወረድንበትና ለኡዱ ወጣን በተራተራ ሰገድን እና ምሳችንን በልተን ወደ ስራችን ተመለስን አሁንም ሳናውቀው 12ሰዐት ሆነ ኡሚም ደወለች በድንጋጤ ሰሙን ቀና ብዬ አየሗት አለቃችንም ስለነበር ማውራት ቢደብረኝም ስልኩን አንስቼ ወዬ ኡሚ አልኳት እናንተ ልጆች ቡናው እኮ ቀዘቀዘ አለችኝ መጣን መጣን ኡሚዬ ልንወጣ ነው አልኳት በዛውም ለሰሙ እንውጣ ለአዩብ ደግሞ ልንወጣ ነው የሚል መልዕክት እያስተላለፍኩ ስልኩን ስዘጋው በቃ ሂዱ ጠዋት በጠዋት ኑ እና ትጨርሱታላቹ አለን ማስጠንቀቂያ መሆኑ ነው።እሺ ደና እደር ብለን ተያይዘን ውልቅ አልን ሁለታችንም እቤት እስክንደርስ ቸኩለናል ምንም ባያገባንም ስለ ማሂር ማወቅ ፈልገናል ኡሚ ስለማሂር ምን ትለን ይሆን?ምን ሆኖ ይሆን.........?



..........ይቀጥላል...........



https://www.tgoop.com/tesefgna

BY በቁርአን ጥላ ስር


Share with your friend now:
tgoop.com/ONLYFORTRUTHERSJ/3099

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

bank east asia october 20 kowloon Public channels are public to the internet, regardless of whether or not they are subscribed. A public channel is displayed in search results and has a short address (link). How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Image: Telegram. For crypto enthusiasts, there was the “gm” app, a self-described “meme app” which only allowed users to greet each other with “gm,” or “good morning,” a common acronym thrown around on Crypto Twitter and Discord. But the gm app was shut down back in September after a hacker reportedly gained access to user data.
from us


Telegram በቁርአን ጥላ ስር
FROM American