tgoop.com/Official_nahi/267
Last Update:
┉••••✽̶»̶̥🌺ከረፈደ!🌺̶̥✽̶••••┉
❣:¨·.·¨: ❣
┈┈••◉❖◉●••┈┄
🌺#ክፍል_ሶስት (3)
#በእዉነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
በበዓል ሙዚቃዎች ድምቀት፤ሽብርቅ ብሎ በቀረበ የቡና አፈላል ስነስርአትና በእጣን ጢስ የታጀበ ግሩም ቁርሰ ነበር።
<<ቢኒያም ባልወልደዉም የልጄ ምትክ ልጄ ነዉ አንቺን የመሰለች ቆንጆ አማች ስላመጣልኝ ደስተኛ ነኝ!>> አሉና ሔርሜላን ሰረቅ አድርገዉ ተመለከቷት በሀፍረት ማቀርቀሯን ካስተዋሉ በሗላ<<ደሞ የምን መፍዘዝ ነዉ ልጅ በልጅነት ነዉ ቶሎ ተጋብታችሁ ዉለዱና እኔንም ወጣት አያት አድርጉኝ>> ብለዉ ሀፍረቷን ወደ ሳቅ ለወጡት። <<ስማኝ ቢኒያም ፍቅር ትዕግስትን ይፈልጋል! በጥላቻ ዓመት የሚፈጀዉ በፍቅር በአንድ ቀን ይከናወናል ግን ትዕግስትን ይሻል ፍቅር ደግሞ ከመቀበል ይልቅ ወደ መስጠቱ ያመዝናልና ለዚህች ቆንጆ ልጅ ፍቅር ለመስጠት እንዳትሰንፍ!>> ብለዉ መርቀዉ ሸኙን። ሔርሜላ ከታላቅ እህቷ ከትዕግስት ጋር ልታስተዋዉቀኝ ቀጠሮ ስለነበራት ልብሴን በፍጥነት ቀይሬ መኪናዉን አስነስቼ ወደ እህቷ ቤት አመራን። ትዕግስት የ 7 ወር ነፍሰጡር ስትሆን ባለቤቷ በስራ ምክንያት በሀገር ዉስጥ አይኖርም ጥሩ መስተንግዶ ተደረገልኝ <<ወጣት ስለሆኑክ በግልፅ ንግግርና በንፁህ ፍቅር አምናለሁ እናትም አባትም ሆኜ ያሳደኳት እኔ ነኝ። የቤተሰብ አደራ አለብን አኛ ጋር ትደግ ብለዉ ከዘመዶቻችን ጋር እስከመጣላት ደርሼ ነበር ሔርሜላ ብቸኛ የእናትና የአባት ዉርሴ ናትና አደራ!!>> አለችኝ! አደራዋን ተቀብዬ ለመሄድ ተነሳሁ ጨለምለም ብሎ ነበር ሔርሜላ እኔን እስከ በር ለመሸኘት ተከተለችኝ። የመስከረም የመጀመሪያዉ ምሽት እንደ ማለዳዉ ብሩህ ሳይሆን በተቃራኒዉ ያኮረፈና ደመናን ያዘለ ነበር። ለ3 ቀን በስራ ጉዳይ ወደ ክፍለ ሀገረ ነገ ጠዋት ስለምሄድ ሔርሜላ ክፍት ብሏት ነበር። ወደ ደረቴ ጠጋ አድርጌ አቀፍኳት! አቀረቀረች! ከአገጯ ቀና አድርጌ አይኖቿን ተመለከትኩ እንባ አቅረዋል! <<እራስህን ጠብቅ ሁሌም አፈቅርሃለሁ>> አለችኝ ከንፈሯን ስሜ ወደ መኪናዉ ገባዉ የ 3ቀን ናፍቆቴን ለመቻል እየታገልኩ መኪናዉን ወደ ፊት አንቀሳቀስኩ...
.
.
የሁለት ቀናት የክፍለ ሀገር ስራዬን በጥሩ ሁኔታ አጠናቅቄ በሶስተኛዉ ቀን ጠዋት ላይ ሔርሜላ ደወለች
<<እንዴት አደርክ?>> ድምጿ እንደ ሌላዉ ቀን በህይወት መኖርን የሚያስመኝ መሆኑ ቀርቶ በሀዘን የተዋጠ ነበር << እንዴት አደርሽ የእኔ ቆንጆ የተፈጠረ ነገር አለ ድምፅሽ ጥሩ አይደለም?>> አልኳት <<ወ/ሮ ሙሉ በጣም ታመዋል እሳቸዉ ጋር ነኝ ዛሬ መድረስ አለመድረስህን ላረጋግጥ ብዬ ነዉ>> አለችኝ! በድንጋጤ ክዉ ብዬ ቀረሁ <<ሄሎ የት ሄድክ?>>
<<አለሁ የእኔ ቆንጆ በጣም ታ.መ.ዋ.ል?>> ተንተባተብኩኝ! በሰላም የተሰናበትኳቸዉ ሰዉ በ 2ቀናት ዉስጥ ምን አገኛቸዉ? ብዬ ክፉኛ ደነገጥኩ! <<ዛሬ ማታ12:30 አከባቢ እደርሳለሁ ስልኩን ስጫቸዉና ላናግራቸዉ>> አልኳት! ማንንም ማናገር እንደማይፈልጉ ገልፃልኝ በቅጡ እንኳን ቻዉ ሳትለኝ ስልኩን ዘጋችዉ። ህመማቸዉ የከፋ ደረጃ ላይ ቢደርስ እንጂ ሔርሜላ እንዲህ አይነቱን ከባድ ዜና ይቅርና ቀላል የሚባሉትን እንኳ ስራ ላይ ሆኜ እንዳይደነግጥ ብላ በማሰብ እንደማትነግረኝ አዉቃለሁ። በቀጥታ አቶ እንዳለ ጋር ደወልኩና አስፈላጊዉን ስራ መጨረሴንና የደንበኞች ፊርማ ያረፈበት ሰነድም በእጄ እንደሚገኝና መነሳት ከነበረብኝ ሰዓት ቀደም ብዬ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ እንደምጀምር የተፈጠረዉን ነገር ገልጬ አስረዳሗቸዉ! አልተቃወሙኝም! አመስግኜ ስልኩን ዘጋሁትና በቀጥታ ጉዞዬን ጀመርኩ። ስለ ወ/ሮ ሙሉ በጣም ከመጨነቄ የተነሳ ከተፈቀደ የፍጥነት ወሰን በላይ እያሽከረከርኩ አዲስ አበባ 11:30 ደረስኩ በቀጥታ ወደ ቢሮ ገብቼ ወረቀቶቹን ለ አቶ እንዳለ ካስረከብኩኝ በሗላ ወደ ቤት አመራሁ ነገር ግን እንዳሰብኩት ቶሎ ወደ ቤት መድረስ አልቻልኩም መንገድ ላይ የትራፊክ አደጋ ስለተፈጠረ ለሰአታት መንገድ ላይ መቆም ግድ ሆነብኝ። ሰአቴን ተመለከትኩ ከምሽቱ 1:15 ይላል ለሔርሜላ ደወልኩ
<<ደረስክ?>>
<< አዎ ግፋ ቢል 30 ደቂቃ መንገድ ዝግ ሆኖብኝ...!>> አላስጨረሰችኝም ስልኩን ጆሮዬ ላይ ዘጋችዉ። በፍፁም የማላዉቃት ሰዉ ሆናብኛለች የትራፊክ መጨናነቁ ቀለል ሲል አቋራጮችን ተጠቅሜ ቤት ደረስኩና የግቢዉን በር ከፍቼ መኪናዉን ካስገባሁ በሗላ ወደ ወ/ሮ ሙሉ ሳሮን እየሮጥኩ ገባሁ። ያየሁትን ማመን አቃተኝ...
ይቀጥላል....
ቀጣይ ክፍል ከ25👍በኋላ ነው የምንለቀው እወዳችዋለው😘
http://www.tgoop.com/+do0OCDQEx_MzOWY0
BY official_nahi
Share with your friend now:
tgoop.com/Official_nahi/267