TARIKUABERA Telegram 3164
ቢገለጥ የሚታየው የመድኃኔዓለም ክርስቶስና የቅዱሳኑ ስም ነው፡፡ ጌታዋ ዕርቃኑን በመሰቀሉ ያላፈረች ቤተ ክርስቲያን ስሙ በተጻፈበት ታቦት አታፍርም! የተከበራችሁ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጽድቅና ድኅነታችን በወንጌል ነው ።በወንጌል ሕይወት እየተመላለስን መንፈሳዊ ትውፊታችንን፣ሃይማኖታዊ በዓላቶቻችንን እና የማንነት መገለጫ ቅርሳችንን አጥብቀን ልንይዝ ይገባል።ዛሬ ሰለጠንን የሚሉት ምዕራባውያን ወንጌልን ተረድተናል በሚል የጀመሩት የአምልኮ ነጻነት መንፈሳዊ ትውፊቶቻቸውን ጠራርጎ አጥፍቶ ዛሬ ላይ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ትውልዱን ሥርዓት አልባ አድርገውት መንፈሳዊ መዓዛ ተለይቷቸው በመጨረሻም አብዛኞቹ ቤተ መቅደሶች የሚያመልክባቸው ትውልድ ጠፍቶ ወደ ጭፈራ ቤት፣መጠጥ መሸጫና ቡቲክነት እንደተቀየሩ በአውሮፓና አሜሪካ ላይ ዓይናችን እያየ ነው።ትውልዱም እግዚአብሔር የለም በሚል ፍልስፍና ተጠልፎ ለሰይጣናዊ አምልኮ ተጋልጦ ይገኛል።

ስለዚህ ሁሉን በሩቅ አጥሮ መያዝ ስለሚገባ አባቶቻችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ያቆዩልንን መንፈሳዊ ክብራችንን፣ሥርዓትና አምልኳችንን ሁሉ ጠንቅቀን ልንጠብቅ ይገባል።ክብራችንን እያቀለልን ወንጌል ገብቶኛል ማለት ፍጹም የተሳሳተ አመለካከትና ፍጻሜው የማያምር ሕይወት ነው።

አንዳንዶች አለቦታው የሚጠቀስ ጥቅስ በመጥቀስ ታቦት ተሽሯል ሲሉም እንሰማለን ።ይህ የሚያሳየው የግለሰቦቹ በዘመንና በትርጉም ተከፍሎ የሚጠናውን መጽሐፍ ቅዱስ በጥልቀት አለማጥናታቸውን ነው። ቃሉ እንዲህ የሚል ነው።

" በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን። የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም፤ ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም። " (ትንቢተ ኤርምያስ 3:16)

ይህንን ቃል በጣም በጥንቃቄ ልናስተውል ይገባል ነብዩ ኤርምያስ በዘመኑ ለነበሩ እስራኤላውያን ይህንን ቃል የተናገረው የሰላም ዘመን መቅረቡን ጦርነትና ስደት ከእነርሱ መራቁን ለማብሰር ነው።እስራኤላውያን በታሪካቸው እንደምናጠናው መከራና ችግር ሲመጣባቸው ታቦቱን አውጡልንና ይዘን እንጓዝ ይሉ ነበር አሁን እንደዚያ የምትጨነቁበት ዘመን አይሆንም ሲላቸው ነው ነብዩ የእግዚአብሔርን የቃልኪዳኑ ታቦት ብለው አይጠሩም ያለው እንጂ ታቦት ጭራሽ አያስፈልግም ለማለት አይደለም። ልብ ካልን ሲጀምር በበዛችሁ ጊዜ በምድር ላይም በረባችሁ ጊዜ ብሎ የሚጀምረው ዘመነ ሰላም እንደ ቀረበላቸው የሚያስረዳ ነው። አንዳንድ ሰዎች ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እኛ ነን ስለዚህ ታቦት ማለት ማደሪያ ስለሆነ በዚህ ዘመን አያስፈልግም ይላሉ ይህ ጥራዝ ነጥቅነት ነው።

የእኛ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያነትና የሥጋወ ደሙ መፈተቻ ታቦት ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም።ነገሮችን በጥንቃቄ ልንመረምርና ክብራችንን መንፈሳዊ እሴቶቻችንን አጥብቀን ልንጠብቅ ለትውልድም ልናስተላልፍ ይገባል። መንፈስ ቅዱስ ለሁላችንም ትሑት ልቡና ያድለን። እባካችሁ ሰዎች ከተሳሳተ አመለካከት እንዲመለሱ ትምህርቱን ለሌሎችም ሼር አድርጉት።

ለበረከት ሁኑ።
መ/ር ታሪኩ አበራ



tgoop.com/TarikuAbera/3164
Create:
Last Update:

ቢገለጥ የሚታየው የመድኃኔዓለም ክርስቶስና የቅዱሳኑ ስም ነው፡፡ ጌታዋ ዕርቃኑን በመሰቀሉ ያላፈረች ቤተ ክርስቲያን ስሙ በተጻፈበት ታቦት አታፍርም! የተከበራችሁ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጽድቅና ድኅነታችን በወንጌል ነው ።በወንጌል ሕይወት እየተመላለስን መንፈሳዊ ትውፊታችንን፣ሃይማኖታዊ በዓላቶቻችንን እና የማንነት መገለጫ ቅርሳችንን አጥብቀን ልንይዝ ይገባል።ዛሬ ሰለጠንን የሚሉት ምዕራባውያን ወንጌልን ተረድተናል በሚል የጀመሩት የአምልኮ ነጻነት መንፈሳዊ ትውፊቶቻቸውን ጠራርጎ አጥፍቶ ዛሬ ላይ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ትውልዱን ሥርዓት አልባ አድርገውት መንፈሳዊ መዓዛ ተለይቷቸው በመጨረሻም አብዛኞቹ ቤተ መቅደሶች የሚያመልክባቸው ትውልድ ጠፍቶ ወደ ጭፈራ ቤት፣መጠጥ መሸጫና ቡቲክነት እንደተቀየሩ በአውሮፓና አሜሪካ ላይ ዓይናችን እያየ ነው።ትውልዱም እግዚአብሔር የለም በሚል ፍልስፍና ተጠልፎ ለሰይጣናዊ አምልኮ ተጋልጦ ይገኛል።

ስለዚህ ሁሉን በሩቅ አጥሮ መያዝ ስለሚገባ አባቶቻችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ያቆዩልንን መንፈሳዊ ክብራችንን፣ሥርዓትና አምልኳችንን ሁሉ ጠንቅቀን ልንጠብቅ ይገባል።ክብራችንን እያቀለልን ወንጌል ገብቶኛል ማለት ፍጹም የተሳሳተ አመለካከትና ፍጻሜው የማያምር ሕይወት ነው።

አንዳንዶች አለቦታው የሚጠቀስ ጥቅስ በመጥቀስ ታቦት ተሽሯል ሲሉም እንሰማለን ።ይህ የሚያሳየው የግለሰቦቹ በዘመንና በትርጉም ተከፍሎ የሚጠናውን መጽሐፍ ቅዱስ በጥልቀት አለማጥናታቸውን ነው። ቃሉ እንዲህ የሚል ነው።

" በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን። የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም፤ ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም። " (ትንቢተ ኤርምያስ 3:16)

ይህንን ቃል በጣም በጥንቃቄ ልናስተውል ይገባል ነብዩ ኤርምያስ በዘመኑ ለነበሩ እስራኤላውያን ይህንን ቃል የተናገረው የሰላም ዘመን መቅረቡን ጦርነትና ስደት ከእነርሱ መራቁን ለማብሰር ነው።እስራኤላውያን በታሪካቸው እንደምናጠናው መከራና ችግር ሲመጣባቸው ታቦቱን አውጡልንና ይዘን እንጓዝ ይሉ ነበር አሁን እንደዚያ የምትጨነቁበት ዘመን አይሆንም ሲላቸው ነው ነብዩ የእግዚአብሔርን የቃልኪዳኑ ታቦት ብለው አይጠሩም ያለው እንጂ ታቦት ጭራሽ አያስፈልግም ለማለት አይደለም። ልብ ካልን ሲጀምር በበዛችሁ ጊዜ በምድር ላይም በረባችሁ ጊዜ ብሎ የሚጀምረው ዘመነ ሰላም እንደ ቀረበላቸው የሚያስረዳ ነው። አንዳንድ ሰዎች ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እኛ ነን ስለዚህ ታቦት ማለት ማደሪያ ስለሆነ በዚህ ዘመን አያስፈልግም ይላሉ ይህ ጥራዝ ነጥቅነት ነው።

የእኛ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያነትና የሥጋወ ደሙ መፈተቻ ታቦት ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም።ነገሮችን በጥንቃቄ ልንመረምርና ክብራችንን መንፈሳዊ እሴቶቻችንን አጥብቀን ልንጠብቅ ለትውልድም ልናስተላልፍ ይገባል። መንፈስ ቅዱስ ለሁላችንም ትሑት ልቡና ያድለን። እባካችሁ ሰዎች ከተሳሳተ አመለካከት እንዲመለሱ ትምህርቱን ለሌሎችም ሼር አድርጉት።

ለበረከት ሁኑ።
መ/ር ታሪኩ አበራ

BY Tariku Abera




Share with your friend now:
tgoop.com/TarikuAbera/3164

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Click “Save” ; Today, we will address Telegram channels and how to use them for maximum benefit. Concise ‘Ban’ on Telegram You can invite up to 200 people from your contacts to join your channel as the next step. Select the users you want to add and click “Invite.” You can skip this step altogether.
from us


Telegram Tariku Abera
FROM American