tgoop.com/Tfanos/2584
Last Update:
አብይ ዛሬ ሰባት አመት ሞልቶታል። ምናልባት ከዚህ በኋላ ሌላ ሰባት አመት በመንበር ይቆይ ይሆናል።
በዘመነ አብይ ድህነት ተባብሷል ፥ ሰላም ቅንጦት ሆኗል ፥ ጦርነት መደበኛ ህይወታችን መስሏል ፥ ስራ ጠፍቷል ፥ ኑሮ ተወዷል.... ወዘተ
ይህ ሁሉ ቢሆንም አብይ ከዚህ በኋላ በስልጣን ይቆያል።
በየአቅጣጫው የአብይ ተቃዋሚዎች በዝተዋል። ታክሲ ውስጥ ድንገት መንግስትን የሚያብጠለጥል ሰው መስማት የተለመደ ነው። በኦሮሚያ የኦሮሞ ነፃነት ጦር ከመንግሥት ጋር እየተፋለመ ነው። ፋኖ ከአገዛዙ ጋር እየተዋጋ ነው። ህወሃት ከፌደራል መንግስት ጋር ሲዋጋ መክረሙ ይታወቃል።
አንዳንዱ በሀይል ፥ አንዳንዱ በሰላማዊ መንገድ መንግስትን እየተፋለመ ነው።
ቢሆንም አብይ በስልጣን ይቀጥላል።
አብይ ሎተሪ ደርሶት በስካር ገንዘቡን ያጠፋ ሰነፍ ሰውን ይመስላል። የድጋፍ መሰረቱን ንዷል ፥ ደጋፊዎቹን በትኗል። ቢሆንም በስልጣን ይቀጥላል።
"አንድ ሀሙስ የቀረው መንግስት" የሚል ፕሮፖጋንዳ ለጆሮ ደስ ቢልም አውነቱን አይቀይርም።
ደርግ በተቃውሞ መሃል 17 አመት ቆይቷል። ኢህአዴግ እያብጠለጠሉት 27 አመት ገዝቷል። አብይ እየሰደቡት ሰባት አመት ሞልቶታል።
ስድብ ፥ ማብጠልጠል የሚቀይረው ነገር የለም።
ህዝብ መተባበር ካልቻለ ፥ የጋራ አጀንዳ ካልቀረፀ ፥ አብሮ ካልተሰለፈ አንባገነን አገዛዝን አያሸንፍም።
የአብይ ተቃዋሚዎች እልፍ ናቸው። ነገር ግን መተባበር አይፈልጉም። አንባገነኖች ዋነኛ ሀይላቸው የማይተባበር ህዝብ ነው።
መተባበር እስኪኖር ድረስ አብይ በመንበሩ ይቆያል። ምናልባት ሌላ ሰባት ፥ አስር ፥ አስራ አምስት አመት....
@Tfanos
BY Tesfaab Teshome
Share with your friend now:
tgoop.com/Tfanos/2584