TFANOS Telegram 2588
ቢላል ለምን ሞተ?
* * *

ስምንት ቀን ስንት አመት ነው? ሃዘን ያጠላበት አንድ ቀን በስንት አመት ይመነዘራል? ፍስሃ ከተቀላቀለው ግማሽ ዘላለም እና ሃዘን ከደቆሰው አንድ ሳምንት ረዥሙ የቱ ነው?
ሰቆቃ ቀንን ዘልዛላ ያደርጋል፤ ህይወት ምሬት ሲጫናት የሰኣት አጋማሽ ከአእላፍ ቀናት ይልቅ ይረዝማል።

አይሻ ከሳምንት በፊት ወጣት ነበረች። ሃዘን ሲደቁሳት በቀናት እድሜ አሮጊት መሰለች። ቀይ መልኳ ጠቆረ፥ ፊቷ በማዲያት ተወረረ፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ መጎሳቆሏ አጎበጣት፥ ከናፍሮቿ ተሰነጣጠቁ፥ በረዶ መሳይ ጥርሶቿ ዝገት ያገኛቸው መሰሉ።
ከስምንት ቀናት በፊት ከነ አይሻ ቤት አቅጣጫ በተሰማ ከባድ ጩኸት ሰፈሩ ተናወጠ። ተሯሩጠን ቤታቸው ስንደርስ አይሻ በድንጋጤ በድን ሆና ቆማለች። ልጇ ዲና ቀሚሷን ጨምድዳ ይዛ በሃይል ታለቅሳለች።

"ምንድነው የተፈጠረው?" ግራ ገባኝ
"ቢላል... ቢላል... ቢ ላ ል" ያቤፅ ተንተባተበ
"ቢላል ምን ሆነ?"
"ቢ... ላል...." ትንፋሽ አጠረው
"ቢላል ምን ሆነ?" ትዕግሥት አጣኹ
"ቢላል...... ራሱን አጠፋ"
"ኢናሊላሂ..."

ዲና በሃይል ጮኸች።

ዲና፥ መልከመልካሟ፥ ትንሿ አበባ፥ ፍልቅልቋ ኮከብ ከፍ ባለ ድምፅ አለቀሰች።
ይህ ከሆነ ሳምንት አለፈው።

ወዳጃችን ቢላል፥ ታታሪው ሰራተኛ፥ የአባትነት ተምሳሌቱ፥ እውነተኛው አፍቃሪ፥ ከልግስና የማይጎድለው፥ ለዲኑ የሚታመነው..... ወንድማችን ቢላል ላይመለስ አንቀላፋ፥ከራሱ ተጣላ፥ በገዛ እጁ ራሱን አጠፋ።

ከአንድ አሏህ በቀር ማንም ቢሆን በሰው ነብስ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌለው ቢያውቅም ከመርህ አፈነገጠ። ከሚታመንለት እውነት ጋር ተላለፈ።

"ስራ ጠፍቷል። ቤተሰብ ለማስተዳደር እየተቸገረ ነበር" ያቤፅ ከቀብሩ ማግስት ሃዘን በሰበረው መንፈስ ሆኖ አናገረኝ።
"መተጋገዝ እንችል ነበር፥ ራሱ ላይ መፍረድ አልነበረበትም"
"የሰውን እጅ ማየት ያታክታል። እንደቢላል አይነት ኩሩ እና ታታሪ ሰው ራሱን ለጥገኝነት አሳልፎ መስጠት አይሆንለትም። እርሱ መለገስን እንጂ የሰውን እጅ ማየትን አያውቅበትም፥ ከጎዶሎው ላይ ቀንሶ ለሌሎች ቸርነትን ያደርጋል እንጂ ለጎደለው ነገር የሰው እጅ አያይም"
"ቢሆንም ..." ሃሳቤን በእንጥልጥል ተውኩት
ሳምንት አለፈ። ወጣቷ አይሻ አረጀች፥ ፅጌሬዳዋ ጠወለገች፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ ውበቷ ከሸፈ፥ በሳምንት እድሜ ከወጣትነት ወደ እርጅና ተሸጋገረች።

* * *
"ይኼ ቆሻሻ መንግስት ቢላልን ነጠቀን" ያቤፅ ደነፋ
"ምን አልክ?" የሰማሁትን ማመን አልሆነልኝም። ጆሮዬን በአጭበርባሪነት ጠረጠርኩት
"ቢላልን የቀማን መንግስት ነው"
አሁንም ጆሮዬን ማመን ስላልቻልኩ 'ሰልሰው እስቲ' ማለት ቃጥቶኝ ነበር። 'ያቤፅ አብዶ ይሆን' የቅፅበት ጥያቄ አቃጨለብኝ።
"ቢላል ለምን የሞተ ይመስልሃል?" ጠየቀኝ
"ኑሮ ስለከበደው" መለስኩ
"ኑሮ ለምን ከበደው?" ተኮሳተረ
"ሲሚንቶ ስለተወደደ፥ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ስለናረ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ክፉኛ ስለተጎዳ፥ የግንባታ እንቅቃሴ መቋረጥ ስለጀመረ ፥ ግንበኛው ጓደኛችን ላይ ስራ አጥነትን አመጣበት። ስራ ማጣቱ ኑሮውን አከበደው። ይኸው ነው" ሁለታችንም የምናውቀውን ነገርኩት
"ይኽ ለምን ሆነ?"

......

#ነገን_ፍለጋ መፅሐፍ ላይ የተወሰደ። ሙሉውን ከመፅሐፉ አንብቡ


@Tfanos



tgoop.com/Tfanos/2588
Create:
Last Update:

ቢላል ለምን ሞተ?
* * *

ስምንት ቀን ስንት አመት ነው? ሃዘን ያጠላበት አንድ ቀን በስንት አመት ይመነዘራል? ፍስሃ ከተቀላቀለው ግማሽ ዘላለም እና ሃዘን ከደቆሰው አንድ ሳምንት ረዥሙ የቱ ነው?
ሰቆቃ ቀንን ዘልዛላ ያደርጋል፤ ህይወት ምሬት ሲጫናት የሰኣት አጋማሽ ከአእላፍ ቀናት ይልቅ ይረዝማል።

አይሻ ከሳምንት በፊት ወጣት ነበረች። ሃዘን ሲደቁሳት በቀናት እድሜ አሮጊት መሰለች። ቀይ መልኳ ጠቆረ፥ ፊቷ በማዲያት ተወረረ፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ መጎሳቆሏ አጎበጣት፥ ከናፍሮቿ ተሰነጣጠቁ፥ በረዶ መሳይ ጥርሶቿ ዝገት ያገኛቸው መሰሉ።
ከስምንት ቀናት በፊት ከነ አይሻ ቤት አቅጣጫ በተሰማ ከባድ ጩኸት ሰፈሩ ተናወጠ። ተሯሩጠን ቤታቸው ስንደርስ አይሻ በድንጋጤ በድን ሆና ቆማለች። ልጇ ዲና ቀሚሷን ጨምድዳ ይዛ በሃይል ታለቅሳለች።

"ምንድነው የተፈጠረው?" ግራ ገባኝ
"ቢላል... ቢላል... ቢ ላ ል" ያቤፅ ተንተባተበ
"ቢላል ምን ሆነ?"
"ቢ... ላል...." ትንፋሽ አጠረው
"ቢላል ምን ሆነ?" ትዕግሥት አጣኹ
"ቢላል...... ራሱን አጠፋ"
"ኢናሊላሂ..."

ዲና በሃይል ጮኸች።

ዲና፥ መልከመልካሟ፥ ትንሿ አበባ፥ ፍልቅልቋ ኮከብ ከፍ ባለ ድምፅ አለቀሰች።
ይህ ከሆነ ሳምንት አለፈው።

ወዳጃችን ቢላል፥ ታታሪው ሰራተኛ፥ የአባትነት ተምሳሌቱ፥ እውነተኛው አፍቃሪ፥ ከልግስና የማይጎድለው፥ ለዲኑ የሚታመነው..... ወንድማችን ቢላል ላይመለስ አንቀላፋ፥ከራሱ ተጣላ፥ በገዛ እጁ ራሱን አጠፋ።

ከአንድ አሏህ በቀር ማንም ቢሆን በሰው ነብስ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌለው ቢያውቅም ከመርህ አፈነገጠ። ከሚታመንለት እውነት ጋር ተላለፈ።

"ስራ ጠፍቷል። ቤተሰብ ለማስተዳደር እየተቸገረ ነበር" ያቤፅ ከቀብሩ ማግስት ሃዘን በሰበረው መንፈስ ሆኖ አናገረኝ።
"መተጋገዝ እንችል ነበር፥ ራሱ ላይ መፍረድ አልነበረበትም"
"የሰውን እጅ ማየት ያታክታል። እንደቢላል አይነት ኩሩ እና ታታሪ ሰው ራሱን ለጥገኝነት አሳልፎ መስጠት አይሆንለትም። እርሱ መለገስን እንጂ የሰውን እጅ ማየትን አያውቅበትም፥ ከጎዶሎው ላይ ቀንሶ ለሌሎች ቸርነትን ያደርጋል እንጂ ለጎደለው ነገር የሰው እጅ አያይም"
"ቢሆንም ..." ሃሳቤን በእንጥልጥል ተውኩት
ሳምንት አለፈ። ወጣቷ አይሻ አረጀች፥ ፅጌሬዳዋ ጠወለገች፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ ውበቷ ከሸፈ፥ በሳምንት እድሜ ከወጣትነት ወደ እርጅና ተሸጋገረች።

* * *
"ይኼ ቆሻሻ መንግስት ቢላልን ነጠቀን" ያቤፅ ደነፋ
"ምን አልክ?" የሰማሁትን ማመን አልሆነልኝም። ጆሮዬን በአጭበርባሪነት ጠረጠርኩት
"ቢላልን የቀማን መንግስት ነው"
አሁንም ጆሮዬን ማመን ስላልቻልኩ 'ሰልሰው እስቲ' ማለት ቃጥቶኝ ነበር። 'ያቤፅ አብዶ ይሆን' የቅፅበት ጥያቄ አቃጨለብኝ።
"ቢላል ለምን የሞተ ይመስልሃል?" ጠየቀኝ
"ኑሮ ስለከበደው" መለስኩ
"ኑሮ ለምን ከበደው?" ተኮሳተረ
"ሲሚንቶ ስለተወደደ፥ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ስለናረ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ክፉኛ ስለተጎዳ፥ የግንባታ እንቅቃሴ መቋረጥ ስለጀመረ ፥ ግንበኛው ጓደኛችን ላይ ስራ አጥነትን አመጣበት። ስራ ማጣቱ ኑሮውን አከበደው። ይኸው ነው" ሁለታችንም የምናውቀውን ነገርኩት
"ይኽ ለምን ሆነ?"

......

#ነገን_ፍለጋ መፅሐፍ ላይ የተወሰደ። ሙሉውን ከመፅሐፉ አንብቡ


@Tfanos

BY Tesfaab Teshome


Share with your friend now:
tgoop.com/Tfanos/2588

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Although some crypto traders have moved toward screaming as a coping mechanism, several mental health experts call this therapy a pseudoscience. The crypto community finds its way to engage in one or the other way and share its feelings with other fellow members. With the administration mulling over limiting access to doxxing groups, a prominent Telegram doxxing group apparently went on a "revenge spree." With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. Today, we will address Telegram channels and how to use them for maximum benefit. 5Telegram Channel avatar size/dimensions
from us


Telegram Tesfaab Teshome
FROM American