Telegram Web
“ምን አይነት ዶሮዎች ናቸው ፀሀይ በነሱ ጩሀት እንደምትወጣ የሚያምኑት?… ምን አይነት ሞኝ ነው እርሱ ከሌለ ህይወት እንደማትቀጥል የሚያስበው?” [አኒስ መንሱር]

ህይወት ማለት የነርሱ ምህዋር ብቻ እንደሆነች የሚያስቡ ሰዎች አላገጠሟችሁም? … ማለቴ እነርሱ ከሄዱ እንደ ጨው የምትቀልጡ አድርገው የሚያስቧችሁ… ሌላ መሄጃ የሌላችሁ የሚመስላቸው… እኛ ካልጮህን ፀሀይ አትወጣም የሚሉ… ዶሮ በሏቸው… ሀሀሀ!!
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
እንኳን  ባዶ ሆነህ
እንኳን ምንም ሆነህ
ሙሳ ነኝ ብትልም አዳራሽ ሀገሩን
ደጋፊ ሚሆንህ ያስፈልጋል ሀሩን።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
"አንቺ ከራቅሽ ወዲያ እሞትልሻለሁ፣
አንቺ ከሄድሽ ወዲያ…
  በእሳት ተቃጥዬ እነድልሻለሁ"
ብሎ የሞገተው ፍቅርሽን ተርቦ ፣
አንቺ ከሄድሽ ወዲያ
አልጨረሰም እንዴ…
የሚነድበትን እንጨቶች ሰብስቦ??
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ከዕብ «ረድዬ'ሏሁ ዐንሁ» ከተቡክ ዘመቻ ወደኋላ በመቅረቱ ምክንያት ነብዩ ሊያናግሩት አልፈለጉም። ሌሎች ሰሗቦችንም እንዳያናግሩት አድርገው ነበር። ከዕብም በዚህ የተነሳ የተለየ ጭንቀት ውስጥ ገብቶ ነበር። በመጨረሻም አሏህ ተውበቱን ሲቀበለው በደስታ ወደ መስጂድ ገባ። ጠልሃ ተነሳና እየሮጠ ሄዶ አቀፈው።  ከዕብ “ወላሂ ያቺን የጠልሃን (ደስታዬን የተጋራበት መንገድ) እልረሳትም።” ይላል።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
በሆኑ አጋጣሚዎች  መንገድህን እነደገለባ ስላቀለልኩልህ  ብቻ ልትወደኝ አይገባህም። በሆኑ ክስተቶች ውስጥ ልብህን በስቃይ ስላማሰልኩት ብቻም  ልትጠላኝ አይሆንልህም። ምናልባት እኔ ሌላ ሰው ሆኜ የተገናኘንበት መንገድ ላይ  ግን ሌላ ሰው እሆናለሁ። ሸይጣን ለአቡ ሁረይራ "ከመተኛትህ በፊት አያተል ኩርሲ ቅራ" ማለቱን ታስታውሳለህ አይደል?  ነብዩላህ ሙሳስ በቦክስ ተማቶ ሰው የገደለ ጊዜ አታስታውስም?  ሙሉ እኔን ፈልገኝ ነው የምልህ።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ሙሳኮ አላህ ለርሱ ብሎ ባህሩን እንደሚከፍልለት አያውቅም። ባህሩ ጋር የደረሰውም አስቦበት አልነበረም። ግን አንድ ነገር እርግጠኛ ነበር “ጌታው መቼም በዚያ አጣብቂኝ ውስጥ  እንደማይተወው”። አቤት… የቂን፤ ዐጀብ ተወኩል ፤ “ተው(አትስጉ) ጌታዬ ከኔ ጋር ነው” የሚል ተራራ ኢማን!!  ኧረ  እንዲህ አይነት የቂን ሸልመን  ያ ወዱድ!!
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ታዳጊ ሐበሻዊ ቃሪእ ነው ፣ ዐብደሏህ ኸድር ይባላል ፣ የምሽት ግብዣ ነው……ተጋበዙልኝ!።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
የዩሱፍ ምዕራፍ አስተምሮኛል። የአላህ ፈረጅና ጥገና ከዘገየ… መቼም የተለመደ ዓይነት ሆኖ አይመጣም። እጥፍ የህይወት ሽልማት ሆኖ እንጂ። ውብ የሆነች ትዕግስት ብቻ… ትንሽ!
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ቀለል ያልክ ሰው ነህ? ሰዎች ልክ እንደራሳቸው የሚያዩህ ወዳጅ ነህ?… "ማለት?" … ማለቴ ለስላሳ ባህሪ የተላበሰ፣ በሆነ ባልሆነው የማይጨቃጨቅ፣ በሰዎች ላይ ጉዳዮችን የሚያቀል፣ የተረጋጋ ስብእና ያለው ሰው ከሆንክ ነብይህ "እነዚህ ሰዎች እሳት በነሱ ላይ እርም ናት" ይሉሃል። አብሽር።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ከባድ ሃጃ ውስጥ ሆነህ የአላህ ፈረጃ በምን መልኩ ነው የሚመጣው ብለህ አትብሰልሰል። በራስህ በኩል ከዱዓእ ጋር እስከጥግ ሰበብ በማሟላት ላይ አትሳነፍ እንጂ ጉዳዩ ከሰማይ በር ነው። የዋሻው ባለቤቶች የአላህ ፈረጅ በመኝታቸው ሁኔታ ይመጣል የሚል ጭራሽ ግምት አልነበራቸውም። … እያልኩህ ያለሁት የአላህ ጥበብ የተከናወነው በተኙበት ሃለት ነው። ከጌታህ በቀር ማን ምን ያውቃል?
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ብዙም ሳንርቅ መሀል መንገድ ላይ የአንዳንድ እንስቶች ወግ ሽበት ያወጣል።  … ክብሯን ከማይጠብቁላት ሰዎች ዓለም የሚመዘዝ ሽበት። ስለመጨረሻቸው ግድ ከማይሰጣቸው የልብ ቀልደኞች ሰፈር የሚመነጭ ሽበት።

ከዚያም እርሷን የሚያከብራት አንድ ወንድ እርሷን ከሚያፈቅሯት ሺህ ወንዶች እንደሚሻል ትደርስበታለች። ምናልባት ሳይረፍድ ወይም ረፍዶ።  …  ሁሉም ወንድ አንዲት ሴትን ሊወዳት ይችላል። ሊያከብራት የሚችለው ግን ከስጋዊ ስሜቱ ራሱን ማስበለጥ የቻለና፣ የአስተውሎት ነብይ የተላከለት መሆኑን ትደርስበታለች።  "ይህ ወንድ  ይመስለኛል … ከውብ የቅርፅ ዓለምና የስጋ ትንፋሽ መሻገር የሚችለው።"  ትላለች።

በእዝነት ከቨሯ ውስጥ ጥንካሬዋን የሚያይ፣ ከቆራጥነቷ መድረክ ጀርባ የሚኖር ልስላሴዋን፣ ከድርቅናዋ ዓይን ላይ ልጅነቷን ማንበብ የሚችለውም እንዲህ ዓይነቱ ይመስለኛል።

“ከሷ የተሻለ አልተሰጠኝም። (ኸዲጃኮ) ሰዎቹ በካዱኝ ጊዜ በእኔ አምናለች። ሌሎች ሲያስተባብሉኝ እውነትነቴን አረጋግጣለች። ሰዎች ሲከለክሉኝ በሀብቷ ደገፋኛለች። ” ባሉት መልዕክተኛ ላይ የአላህ ሰላም ይስፈን።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
تلاوة مؤثرة يرق لها القلب-الشيخ يونس اسويلص (وَيُنَجِّي اللَّهُ…
عبدالله الرواس
ያሰላላላም! ልብን የሚገዛ ቲላዋ፣ ቁርኣን ባይኖር ንሮ ልቦች እንዴት ይሰክኑ ነበር ፣ " አዋጅ! አሏህን በማውሳት ልቦች ይሰክናሉ" [ረዕድ: 28]

             ➥ቁርኣን
       
እንደ ጅረት ወርዶ - ባህር ሆዴ ገብቶ፣
በቃላት ተሣስሮ - ህልናዬ ረክቶ፣
የኋላ የፊቱን - ክፉ ደጉን ቃኝቶ፣

በረከቱ ሰፊ - ማዕዱ ማራኪ፣
አስደሳች አሲቂኝ - አሳዛኙን ሁሉ፣
…………………በጣፋጭ ተራኪ

የጥበብ ዓውድማ - የምድረዓለም ማማ
እርሱ ነው ቁርኣን - የዕውቀት ካባ ሻማ
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
የፊርዓውንን ቆሻሻ ይዛችሁ… የመርየምን ንፅህና የምትፈልጉ… የብዙዎች ክብረ ንፅህና ጋር ደርሳችሁ "ቢክራ ካልሆነች አሰናብታለሁ" በማለት  እንደ ዚክር የምትደጋግሙ …ትንሽ አስቡ እስኪ … ማናችሁ እናንተ?
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ባልተለመደ መልኩ ከሰላምታው ጀምሮ ቀዝቀዝ የሚል ሰው አግኝተህ ይሆናል። በረዶ የሆነ ገፅታውን ብቻ የምታይበት አይነት ሰው። እንዲህ አይነቱን ሰው "ኩራተኛ ወይም በራሱ የሚታበይ ነው" ብለህ ለመፍረድ ባትቸኩል ይሻላል።  እመነኝ…  ውስጡ ሰላም የነሳው ጩሀት አለ… ስላንተ ስሜት እንዳያስብ ያደረገው ሀይለኛ ረብሻ አይጠፋም። በቃ… ሲያገኝህ በትንሹ ምንም እንደሌለ ለማስመሰል የሚሞክር ዓይነት ሰው። ምናልባት ከርሱ ውጪ ማንም የማያውቀው አስቸጋሪ ቀናቶቹን እያለፈ ይሆናል።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
ጣም እርካታ አጥቼ - ለጉድ ተሰቃየሁ
የዱንያን ጀሂም - ካንተ ስርቅ አየሁ
እሳት ነው መሰንበት - ካንተ ርቆ ሀያት
አንተው ሁነኝ ረቢ - ነፍሴ አደብ ጎደላት።
ያ ወዱድ ያ ወዱድ!
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
« የፍቅርን አቅም ማየት ከፈለግክ ኡመሩል ፋሩቅ የረሱሉላህ ህልፈት የተነገራቸው ጊዜ የሆኑትን ልብ በል፣ የሚወዱትን ዳግም ሊያዩት እንደማይችሉ ሲያውቁ ያለውን ሀዘን መቃኘት ከፈለግክ ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ረሱሉላህን ሲሰናበት ያለውን አስተውል።
ንፁህ ፍቅር ትዝታው ከባድ እንደሆነ ለማየት ቢላል ኢብኑ ረባህ ወደ መዲና ተመልሶ መጥቶ አዛን ሲል ስለነበረው ክስተት መርምር። ልብ እጅግ የሚመኘውን ንፁህ ፍቅር ሲያገኝ ትንሽ ማየት ከፈለግክ « አላህ ሆይ ለኔና ለሙሀመድ ብቻ ምህረት አድርግ፣ ሌሎቹን ግን ቅጣቸው » ስላለው አዕራብይ ሁኔታ አስብ።
ፍቅር ልቦችን እንደሚያናግር ማወቅ ከፈለግክ ስለ ረሱሉላህ ሲወራ የአማኞችን ፊት ተመልከት። ጌታህ ከማንም አብልጦ እንደሚወድህ ለማረጋገጥ ከፈለግክ አሁንም ድረስ እዝነቱን ልብ በል። ለጌታህ ያለህን ፍቅር መግለፅ ከፈለግክ አሁንም ድረስ የተውበትን በር ክፍት እንዳደረግልህ አስተውል። »
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
« ሁሌም ከመልካም ሰዎች አጠገብ መልካም ሰዎች ብቻ ይገኛሉ ብላችሁ አትሞኙ። መልካም ሰዎችን አይታችሁ ከእነሱ አጠገብ ያያችሁትን ሁሉ በደፈናው መልካም አድርጋችሁ አትደምድሙ። አንዳንዴ ከመልካም ሰዎች በቅርብ ርቀት የሚገኙ የመልካም ሰዎቹን ፈለግ የማይከተሉ ሰዎች ይኖራሉ።
ከአሲያ ጎን ፊርዓውን ነበር። ከኡመር በቅርብ ርቀት አቡ ጀህል እንደነበር ልብ በሉ! »
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"እጅሽን ተመልከቺው…  አልማዝ ላይ ወርቅ ምን ያደርጋል?" ሊያገባት ተስማምተው … ቀለበት ሊገዛላት ሲሄድ ከተናገራት።
:
“ሁሉም የራሱን ጨረቃ በማየት ተጠምዷል። እሷ የሰማዩን ለማየት ቀና ብላለች… እኔ ደግሞ እሷን።”  አለ አሉ… አንዳንዴማ እንዲህ አይነት ነገሮችንም ላስተምራችሁ… ግን አሉ ነው።
www.tgoop.com/abdu_rheman_aman
2025/02/21 03:19:05
Back to Top
HTML Embed Code: