tgoop.com/atc_news/24578
Create:
Last Update:
Last Update:
የ41 ትምህርት ቤቶች ፈቃድ መሠረዙን የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
ፈቃዳቸው የተሠረዘው የትምህርት ፖሊሲውን ባለመጠበቅና መስፈርቱን ባለማሟላታቸው ነው ብሏል ባለስልጣኑ፡፡
ባለስልጣኑ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን መዝግበው የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶችን እና ፈቃዳቸው የተሠረዘ የትምህርት ተቋማትን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን መዝግበው የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች 1 ሺህ 332 ሲሆኑ÷ የማስተማር ፈቃድ እንደተሰጣቸውም ገልጿል፡፡
በሌላ በኩል 43 ትምህርት ቤቶች በራሳቸው ጊዜ መቀጠል ስላልቻሉ ፈቃዳቸው ተሠርዟል መባሉን የባለስልጣኑ መረጃ አመላክቷል፡፡
እንዲሁም 150 ትምህርት ቤቶች ጉዳያቸው በሂደት ላይ መሆኑና ወደፊት እንደሚገለጽ ተጠቁሟል፡፡
41 ትምህርት ቤቶች ደግሞ የትምህርት ፖሊሲውን ባለመጠበቅና መስፈርቱን ባለማሟላታቸው ፈቃዳቸው መሠረዙን ነው ባለስልጣኑ ያስታወቀው፡፡
(ኢትዮ ኤፍ ኤም)
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tgoop.com/atc_news
BY ATC NEWS
![](https://photo2.tgoop.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/AXqoP1CsrawRe_68ZTQ3-UCTlFFeye8zdmhdMrAwa2DMF2-WpGu_loajz7saJ3Ok5AkbEZ-0NoHHTSTwB9wX2qCFw6Sdf1dwqfQssRobm7DoKwYapS8wmZgqioNRJQ-glfVl1nw0ZJJmHNUloSbQ6TRv-_36v0LIQ4OneSvo0h6QWOKCv1uANy60SqwjzqhWFgmMTYwyjPIphkWItf6v0fIIg4fWtd7_PObuLw7fJeMph4kf_KYxrdvhTHVH_FWPYSf8YAlipZ5pnRY2UKF__IR2iyEoDueTBERQ5NOWoW9oe0qM_kNgUS4liJDWS8fh4zDc6JyEvWiQnUO-Xm7_Eg.jpg)
Share with your friend now:
tgoop.com/atc_news/24578