ATERIRA Telegram 128
Hilawe Tesfaye
Feb 29, 2016
" አንተን ሲደላህና ሲመችህ አገርህን የምትወዳት፤ ሲጎልብህና
ሲከፋህ የምትጠላት ከሆነ አንተ የምትወደው ሀገርህን ሳይሆን
ራስህን ነው።"
.
.
እንደው እውነት ለመናገር እቺ አባባል እንደጥቅስ ታክሲ ላይና
ራስጌ ለመለጠፍ ታምራለች እንጂ ለመተግበር ትከብዳለች።
ማንም ሰው አገሩ ሲመቸው ፍቅሩ ከፍ ይላል። ሲበደል ደግሞ
ተቃራኒው...
.
.
ነገር ግን እነዚህ ሰዎች በበደል ውስጥም ሆነው ይቺን ጥቅስ
የእውነት ነውንነውታል። ምንም ቢበደሉም የሚያልፈውን
መንግስት ሳይሆን ቋሚዋን አገራቸውን አርቀው አይተዋል።
.
.
'ያወራብሽ ኖሮ የሰራልሽ ሞተ' ያሉት 'ከሀይለስላሴ' ጋር
የተጣሉት 'በላይ ዘለቀ' እንኳን 'ወንድ አይውጣብሽ' ብለው
ሀገራቸውን ተራግመዋል።
.
.
(1)
-
'ደጃዝማች ጉዋንጉል ዘገየ።'
-
"እኚህ ሰው ምኒሊክ ላይ ሸፍተው ከምኒሊክ ጭፍሮች ጋር
በጦርነት የተፈታተኑ ሰው ናቸው።
-
የውጪ ጦር ሲመጣብን ግን ከግዚያዊው ምኒሊክ ፀብ ይልቅ
ሩቋን ሀገራቸውን በማሰብ ህዳር 24 ቀን ምኒሊክ 'መርሳ' ላይ
ሰፍረው ሳለ የጓንጉል መልክተኛ እንዲህ የሚል መልክት ይዞ
መጣ:
-
-
"ጃንሆይ ከርሶ ተጣልቼ በርሀ ገብቻለሁ። አሁን ግን በሀገሬ ላይ
የውጪ ጠላት ስለመጣባት የርሶና የኔ ጉዳይ ቀርቶ ይማሩኝና
መጥቼ ከእርሶ ጌታዬ ጋር ሆኜ ያገሬን ጠላት ልውጋ?" ብሎ
ሲናገር ምኒሊክ ተደስተው 'ይምጣ ምሬዋለሁ' ብለው
ተቀበሉት።
-
(ይልሀል 'ጳውሎስ ኞኞ' አጤ ምኒሊክ' በሚለው መፃፉ)
.
.
(2)
-
ክቡሩ ሰው 'ባልቻ ሳፎ (አባ ነፍሶ)'
-
እኚህ ሰውዬ ምንም እንኳን የአድዋ ጦርነትን ጨምሮ ላገራቸው
ወሳኝ ስራ የሰሩ ቢሆንም 'ንግስት ዘውዲቱን' ከሚደግፉት
ወገን ስለነበሩ የአልጋወራሽ ተፈሪን ትዕዛዝ አልቀበልም ስላሉ
ታስረውና ተግዘው ይኖሩ ነበር።
-
-
ጣሊያን ለሁለተኛ ጊዜ ሲወረን በዚያን ጊዜ እንደሳቸው
በእስራትና ግዞት ላይ የነበሩት እነ 'ደጃዝማች አባውቃው፤ ራስ
ሀይሉ ካሳ' እና ሌሎች ነፃ በመሆናቸው ከጣሊያኖች ጋር በደስታ
ሲፈነጥዙ፤
-
-
ባልቻ ግን " ጠላቴ ሀይለስላሴ እንኳን ወደቀ" ሊሉ ቀርቶ
ጭራሽ በእልፍኛቸው ውስጥ እየተዘዋወሩ "ወይኔ እኔ ባልቻ!
አይኔ እያየ የምኒሊክ አገር ኢትዮጵያ ትውደቅ? በማለት ምርር
ብለው አለቀሱ" ይባላል።
-
-
ዕንባቸውን አፍሰው አልቀሩም ጉልበታቸው በደከመበት
በስተርጅና ሲዋጉ ደማቸውን አፍሰው ሞቱ።"
-
(ይለናል 'ብርሀኑ ድንቄ' ቄሳርና አብዬት' በሚለው መፅሀፉ)
.
.
(3)
-
'ልጅ አብዩ'
-
ይሄ 'ከራስ መኮንን' ጋር መቀሌ የዘመተው ልጅ ነው። እራስ
'አሉላን' ጨምሮ መኳንንቶቹ ምሽጉን ጥሶ ስለመግባት ሲማከሩ
አብዩ እየተቃወመ ተናገረ " ሰራዊቱን በከንቱ ከምናስጨርስ
ውሀውን እንዝጋበት እጁን ይሰጣል።" ሲል ሁሉም የአብዩን
ሀሳብ 'ፈርተህ እንዳይሆን' በሚል ሲቃወሙበት
-
-
አብዩም መለሰ " ሰራዊቱ በከንቱ እንዲያልቅ በመደረጉ
አዝናለሁ። ግን እናንተ ስትሞቱ እኔ የቀረሁ እንደሆን የዛኔ እኔ
ፈሪ ተብዬ እሰደባለሁ" ብሎ ባላመነበት ጦርነት ዘምቶ
በሚያሳዝን ሁኔታ ተዋግቶ ሞተ።
-
-
እንዳለውም ብዙ ሰራዊት አለቀ። እቴጌ ጣይቱ እሱ ያነሳውን
'ውሀውን የመቆጣጠር' ሀሳብ አምጥተው ተተገበረና ጣሊያኖቹ
ከምሽጋቸው ወጥተው እጅ ሰጡ።
-
(ይሉናል ተክለሀዋርያት 'ኦቶባዮግራፊ' የህይወቴ ታሪክ'
በሚለው መፅሀፋቸው)
.
.
ከነገ ወዲያ እሮብ የካቲት 23 የአድዋ ድል በአል ተከብሮ
ይውላልና መልካም በአል!!



tgoop.com/aterira/128
Create:
Last Update:

Hilawe Tesfaye
Feb 29, 2016
" አንተን ሲደላህና ሲመችህ አገርህን የምትወዳት፤ ሲጎልብህና
ሲከፋህ የምትጠላት ከሆነ አንተ የምትወደው ሀገርህን ሳይሆን
ራስህን ነው።"
.
.
እንደው እውነት ለመናገር እቺ አባባል እንደጥቅስ ታክሲ ላይና
ራስጌ ለመለጠፍ ታምራለች እንጂ ለመተግበር ትከብዳለች።
ማንም ሰው አገሩ ሲመቸው ፍቅሩ ከፍ ይላል። ሲበደል ደግሞ
ተቃራኒው...
.
.
ነገር ግን እነዚህ ሰዎች በበደል ውስጥም ሆነው ይቺን ጥቅስ
የእውነት ነውንነውታል። ምንም ቢበደሉም የሚያልፈውን
መንግስት ሳይሆን ቋሚዋን አገራቸውን አርቀው አይተዋል።
.
.
'ያወራብሽ ኖሮ የሰራልሽ ሞተ' ያሉት 'ከሀይለስላሴ' ጋር
የተጣሉት 'በላይ ዘለቀ' እንኳን 'ወንድ አይውጣብሽ' ብለው
ሀገራቸውን ተራግመዋል።
.
.
(1)
-
'ደጃዝማች ጉዋንጉል ዘገየ።'
-
"እኚህ ሰው ምኒሊክ ላይ ሸፍተው ከምኒሊክ ጭፍሮች ጋር
በጦርነት የተፈታተኑ ሰው ናቸው።
-
የውጪ ጦር ሲመጣብን ግን ከግዚያዊው ምኒሊክ ፀብ ይልቅ
ሩቋን ሀገራቸውን በማሰብ ህዳር 24 ቀን ምኒሊክ 'መርሳ' ላይ
ሰፍረው ሳለ የጓንጉል መልክተኛ እንዲህ የሚል መልክት ይዞ
መጣ:
-
-
"ጃንሆይ ከርሶ ተጣልቼ በርሀ ገብቻለሁ። አሁን ግን በሀገሬ ላይ
የውጪ ጠላት ስለመጣባት የርሶና የኔ ጉዳይ ቀርቶ ይማሩኝና
መጥቼ ከእርሶ ጌታዬ ጋር ሆኜ ያገሬን ጠላት ልውጋ?" ብሎ
ሲናገር ምኒሊክ ተደስተው 'ይምጣ ምሬዋለሁ' ብለው
ተቀበሉት።
-
(ይልሀል 'ጳውሎስ ኞኞ' አጤ ምኒሊክ' በሚለው መፃፉ)
.
.
(2)
-
ክቡሩ ሰው 'ባልቻ ሳፎ (አባ ነፍሶ)'
-
እኚህ ሰውዬ ምንም እንኳን የአድዋ ጦርነትን ጨምሮ ላገራቸው
ወሳኝ ስራ የሰሩ ቢሆንም 'ንግስት ዘውዲቱን' ከሚደግፉት
ወገን ስለነበሩ የአልጋወራሽ ተፈሪን ትዕዛዝ አልቀበልም ስላሉ
ታስረውና ተግዘው ይኖሩ ነበር።
-
-
ጣሊያን ለሁለተኛ ጊዜ ሲወረን በዚያን ጊዜ እንደሳቸው
በእስራትና ግዞት ላይ የነበሩት እነ 'ደጃዝማች አባውቃው፤ ራስ
ሀይሉ ካሳ' እና ሌሎች ነፃ በመሆናቸው ከጣሊያኖች ጋር በደስታ
ሲፈነጥዙ፤
-
-
ባልቻ ግን " ጠላቴ ሀይለስላሴ እንኳን ወደቀ" ሊሉ ቀርቶ
ጭራሽ በእልፍኛቸው ውስጥ እየተዘዋወሩ "ወይኔ እኔ ባልቻ!
አይኔ እያየ የምኒሊክ አገር ኢትዮጵያ ትውደቅ? በማለት ምርር
ብለው አለቀሱ" ይባላል።
-
-
ዕንባቸውን አፍሰው አልቀሩም ጉልበታቸው በደከመበት
በስተርጅና ሲዋጉ ደማቸውን አፍሰው ሞቱ።"
-
(ይለናል 'ብርሀኑ ድንቄ' ቄሳርና አብዬት' በሚለው መፅሀፉ)
.
.
(3)
-
'ልጅ አብዩ'
-
ይሄ 'ከራስ መኮንን' ጋር መቀሌ የዘመተው ልጅ ነው። እራስ
'አሉላን' ጨምሮ መኳንንቶቹ ምሽጉን ጥሶ ስለመግባት ሲማከሩ
አብዩ እየተቃወመ ተናገረ " ሰራዊቱን በከንቱ ከምናስጨርስ
ውሀውን እንዝጋበት እጁን ይሰጣል።" ሲል ሁሉም የአብዩን
ሀሳብ 'ፈርተህ እንዳይሆን' በሚል ሲቃወሙበት
-
-
አብዩም መለሰ " ሰራዊቱ በከንቱ እንዲያልቅ በመደረጉ
አዝናለሁ። ግን እናንተ ስትሞቱ እኔ የቀረሁ እንደሆን የዛኔ እኔ
ፈሪ ተብዬ እሰደባለሁ" ብሎ ባላመነበት ጦርነት ዘምቶ
በሚያሳዝን ሁኔታ ተዋግቶ ሞተ።
-
-
እንዳለውም ብዙ ሰራዊት አለቀ። እቴጌ ጣይቱ እሱ ያነሳውን
'ውሀውን የመቆጣጠር' ሀሳብ አምጥተው ተተገበረና ጣሊያኖቹ
ከምሽጋቸው ወጥተው እጅ ሰጡ።
-
(ይሉናል ተክለሀዋርያት 'ኦቶባዮግራፊ' የህይወቴ ታሪክ'
በሚለው መፅሀፋቸው)
.
.
ከነገ ወዲያ እሮብ የካቲት 23 የአድዋ ድል በአል ተከብሮ
ይውላልና መልካም በአል!!

BY Ateriraአጤሪራ


Share with your friend now:
tgoop.com/aterira/128

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

For crypto enthusiasts, there was the “gm” app, a self-described “meme app” which only allowed users to greet each other with “gm,” or “good morning,” a common acronym thrown around on Crypto Twitter and Discord. But the gm app was shut down back in September after a hacker reportedly gained access to user data. Earlier, crypto enthusiasts had created a self-described “meme app” dubbed “gm” app wherein users would greet each other with “gm” or “good morning” messages. However, in September 2021, the gm app was down after a hacker reportedly gained access to the user data. You can invite up to 200 people from your contacts to join your channel as the next step. Select the users you want to add and click “Invite.” You can skip this step altogether. To delete a channel with over 1,000 subscribers, you need to contact user support Hashtags are a fast way to find the correct information on social media. To put your content out there, be sure to add hashtags to each post. We have two intelligent tips to give you:
from us


Telegram Ateriraአጤሪራ
FROM American