BAHIRETIBEBAT Telegram 8211
ላይ ጥናት ማድረግ ለሚፈልጉ ሰዎች ያለውን ግብዐት አምኖበት፣ ነገር ግን በይዘቱ ትልቅ በመሆኑ (ከመግቢያውና መቅድሙ ውጪ 367 ገጾች አሉት) የንባብ ልምድ የሌላቸውን ምእመናን ትኩረት መሳብ ስላልቻለ፣ ምእመናን በቅዳሴ ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያሳይና ቀለል ባለ መልኩ የተጻፈ ሁለተኛ መጽሐፍ እንዳዘጋጅ በfacebook የላከልኝ መልእክት ይህን መጽሐፍ እንድጽፍ ዋነኛ ምክንያት ሆኗል፡፡ ወንድማችን ሲሳይ የጻፈልኝ የfacebook ምክረ ሐሳብ ይህን ይመስላል፡-

ይህ መጽሐፍ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለማያውቁት ለማስረዳት በቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ ለዓመታት በታመቀ እውቀት፣ በእምነትና በቁጭት የተጻፈ መጽሐፍ ሆኖ አገኘሁትና በፍቅር አነበብኩት። መጽሐፉ የጥናትና ምርምር መጽሐፍ በመሆኑ የንባቤ ትኩረት ቅዳሴው ላይ ብቻ ነበር፤ ከአቅሜ በላይ የሆኑትን መንፈሳዊና የታሪክ ጭብጦችን ጠልቄ ልመረምር አልሞከርኩም። መጽሐፉ በአብነትም በዘመናዊ ትምህርትም ተምረናል፣ አውቀናል ብለው ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንንና ቅዳሴን ለሚያቃልሉ አላዋቂዎች ትዕቢታቸውን የሚያስተነፍስ ፍቱን መድኃኒት እንደሚሆን አስተውያለሁ። ቅዳሴን በዚህ ልክ ሰማያዊና ዓለም አቀፋዊ አገልግሎቱን፤ አስፈላጊነቱን፣ ጥቅሙን፣ ክብሩን፣ የቅዳሴ ዓላማና ግቡን አስረድቶ የጻፈ መጽሐፍ ከዚህ በፊት አላነበብኩም። ስለ ቅዳሴ ለማወቅ ይኽን መጽሐፍ ሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ ሆኖ ሳለ፣ መጠኑ ትልቅ ስለሆነ በቤት ቁጭ ተብሎ እንጂ ለኪዳንም [ሆነ] ለቅዳሴ ሲሄዱ ይዘውት ሊንቀሳቀሱ ባለመቻሉ ቀዳሹም አስቀዳሹም በቀላሉ [ሊጠቀሙበት አልቻሉም]። ስለዚህ “አኰቴተ ቊርባን” መጠኑ ትልቅ ስለሆነ፣ የታተመው እንዳለ ባለው ይዘት ኅትመቱ ቀጥሎ፣ ዘወትር በቅዳሴ የሚሳተፉ ምእመናን በቀላሉ ከጸሎት መጽሐፋቸው ጋር ሊይዙት በሚችሉት መጠን ቀዳሹና አስቀዳሹ ሊያውቁት የሚገባውን ክፍል ስለቅዳሴ ለብቻ አውጥቶ በትንሹ መታተም ቢችል እጅግ በጣም ጥሩ ነው ብዬ ይህን የአደራ መልእክት አስተላልፋለሁ። (ትልቁ የቅዳሴው መጽሐፍ እያለ፤ ለምዕመናን [ለተሰጥዎ] መማሪያ ተብሎ በትንሹ በጸሎት መጽሐፍ መልክ እንደተዘጋጀው ዓይነት ማለት ነው)።

ብሌን ታከለ የቶሮንቶ መንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል አባል ናት፡፡ የቅዳሴን ጣዕም ከልጅነቷ ጀምሮ የቀመሰችና ባደገችበት የሐዋሳ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ታላቅ የአገልግሎት ተሳትፎ የነበራት ልጅ ስለሆነች፣ አኰቴተ ቊርባን እጇ ውስጥ እንደገባ በደስታ አነበበችው፡፡ አቀራረቡን አስመልክቶ ግን ለየት ያለ አስተያየት ሰጠችኝ፡፡ “ቅዳሴን በትረካ መልኩ ያቀረበ መጽሐፍ መስሎኝ ነበር” አለች ብሌን፡፡ ይህን አስተያየት በርካታ ምእመናን ሊጋሩት እንደሚችሉ ተረዳሁ፡፡ ስለዚህ ይህ መጽሐፍ “ፍቅርተ ኢየሱስ” የተባለች፣ በጌታ የተወደደች፣ በደሙ እንደተዋጀች የምታውቅና የቅዳሴን ውበት እንድታይ በቅዱስ ቃሉ ትምህርት ዐይነ ልቡናዋ የበራላት ምእመን፣ ቅዳሴው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ በጣዕመ ዜማው፣ ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት በሚነበቡ ምንባባት፣ በቅዳሴው ጸሎትና ዑደት ሐሴት እያደረገች የቅዳሴው ተሳታፊ የምትሆንበትን ሂደት በዝርዝር ለማስረዳት ይሞክራል፡፡ ፍቅርተ ኢየሱስ ለቅዳሴ ካላት ፍቅር የተነሣ ዘወትር እሑድና በዐበይት በዓላት የቅዳሴ ተሳታፊ ስለምትሆን፣ ምእመናን ለዲያቆናቱና ለካህናቱ የሚሰጡትን የዜማ መልስ (ተሰጥዎ) በሚገባ ታውቃለች፤ መቅደሱ ላይ ያለውን የጌታ ስቅለት ሥዕል እያየች ዐይነ ልቡናዋን ወደ ቀራንዮ አቅንታ፣ ድምጽዋን ከፍ አድርጋ ታዜማለች፡፡ በሥርዓተ አምልኮው ከሚከናወኑ ድርጊቶች መካከል ምሳሌያዊ ትርጉሙ ያልገባት ነገር ካለ ወይም በአብዛኛው ከሚቀደሱት ቅዳሴያት ለየት ያለ ቅዳሴ (ለምሳሌ ቅዳሴ ሠለስቱ ምእት፣ ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፣ ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ ወዘተ.) ከተቀደሰ፣ የንስሐ አባትዋን ቀሲስ ፍቅረ መለኮትን ትጠይቃለች፡፡ እርሳቸውም መጽሐፈ ቅዳሴውን ይዘው የአማርኛውን ትርጉም እያስነበቡ ጥያቄዎቿን በሙሉ በዕርጋታና በዝርዝር ይመልሱላታል፡፡

ይህ መጽሐፍ ማንኛውም የቤተ ክርስቲያናችን አባል ስለ ቅዳሴ ሊያውቃቸው የሚገባቸውን መሠረታዊ ትምርህቶች ለማቅረብ ሙከራ አድርጓል፡፡ ትምህርተ ቅዳሴው የቀረበበትም መንገድ፣ የቅዳሴውን ሦስት ዋና ዋና ክፍልች በመከተልና ከየክፍሉ በተመረጡ አርእስት ላይ መጠነኛ ሐተታ (ገለጻ) በመስጠት ሲሆን፣ ፍቅርተ ኢየሱስ የተባለች ገጸ-ባሕርይ የቤተ ክርስቲያናችንን ምእመናን እንድትወክል ተደርጓል፡፡ በሦስቱ የቅዳሴ ክፍሎች ሥር የቀረቡ ትምህርቶችን በምዕራፍ ከመከፋፈል ይልቅ፣ “ቡራኬ 1፣ ቡራኬ 2 . . .” የሚል ስያሜን መርጫለሁ፡፡ ባጠቃላይ መጽሐፉ በሦስት ዐበይት ክፍሎችና በሃያ አንድ (21) ቡራኬያት የተከፈል ሲሆን፣ ትምህርታዊ ገላጻ የተሰጠባቸው ሃያ አንዱ ቡራኬያት፣ ሠራዒው ካህን በቅዳሴ ሰዓት የሚያከናውናቸውን ሃያ አንድ የአፍኣ (የውጭ) እና የውስጥ ቡራኬያትን ያስታውሱናል፡፡

በመጽሐፉ ውስጥ ለተጠቀሱ የግእዝ ቃላትና የሥርዓተ አምልኮ ስያሜያት (liturgical terminologies) መፍትሔ ቃላት (glossary) ተዘጋጅቷል፡፡ ምእመናንን ወክላ በዚህ መጽሐፍ የቅዳሴውን ሂደት በተመስጦ፣ አንዳንዴም በዕንባ፣ የምትከታተለው ፍቅርተ ኢየሱስ የቅዳሴ ጸበል ብቻ ጠጥታ ወደ ቤቷ የምትመለስ ሳትሆን፣ ጌታችን ኢየሱስ በቅዱስ ወንጌል “ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው” (ዮሐ. 6፡51) እንዳለ፣ ከኃጢአት በሽታ የምትፈወስበትን ኅብስተ ሕይወትና ጽዋዐ አኰቴት (ሥጋውና ደሙን) የምትቀበል ኦርቶዶክሳዊት ክርስቲያን ናት፡፡ ፍቅርተ ኢየሱስን በምናባቸው እየሳሉ ይህን መጽሐፍ የሚያነብቡ፣ ነገር ግን ከቅዱስ ቊርባን የራቁ ወይም ከተቀበሉ ዓመታትን ያስቆጠሩ የቤተ ክርስቲያናችን አባላት በእውነተኛ ንስሐና በምክረ ካህን ተዘጋጅተው “ጸጋ ሆኖ የተሰጠንን ሥጋውንና ደሙን በእግዚአብሔር ጥበብ” እንደሚቀበሉ ተስፋ አደርጋለሁ - መልካም ንባብ፡፡
ቀሲስ መብራቱ ኪሮስ (Ph.D.)
ቶሮንቶ፣ ካናዳ



tgoop.com/bahiretibebat/8211
Create:
Last Update:

ላይ ጥናት ማድረግ ለሚፈልጉ ሰዎች ያለውን ግብዐት አምኖበት፣ ነገር ግን በይዘቱ ትልቅ በመሆኑ (ከመግቢያውና መቅድሙ ውጪ 367 ገጾች አሉት) የንባብ ልምድ የሌላቸውን ምእመናን ትኩረት መሳብ ስላልቻለ፣ ምእመናን በቅዳሴ ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያሳይና ቀለል ባለ መልኩ የተጻፈ ሁለተኛ መጽሐፍ እንዳዘጋጅ በfacebook የላከልኝ መልእክት ይህን መጽሐፍ እንድጽፍ ዋነኛ ምክንያት ሆኗል፡፡ ወንድማችን ሲሳይ የጻፈልኝ የfacebook ምክረ ሐሳብ ይህን ይመስላል፡-

ይህ መጽሐፍ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለማያውቁት ለማስረዳት በቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ ለዓመታት በታመቀ እውቀት፣ በእምነትና በቁጭት የተጻፈ መጽሐፍ ሆኖ አገኘሁትና በፍቅር አነበብኩት። መጽሐፉ የጥናትና ምርምር መጽሐፍ በመሆኑ የንባቤ ትኩረት ቅዳሴው ላይ ብቻ ነበር፤ ከአቅሜ በላይ የሆኑትን መንፈሳዊና የታሪክ ጭብጦችን ጠልቄ ልመረምር አልሞከርኩም። መጽሐፉ በአብነትም በዘመናዊ ትምህርትም ተምረናል፣ አውቀናል ብለው ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንንና ቅዳሴን ለሚያቃልሉ አላዋቂዎች ትዕቢታቸውን የሚያስተነፍስ ፍቱን መድኃኒት እንደሚሆን አስተውያለሁ። ቅዳሴን በዚህ ልክ ሰማያዊና ዓለም አቀፋዊ አገልግሎቱን፤ አስፈላጊነቱን፣ ጥቅሙን፣ ክብሩን፣ የቅዳሴ ዓላማና ግቡን አስረድቶ የጻፈ መጽሐፍ ከዚህ በፊት አላነበብኩም። ስለ ቅዳሴ ለማወቅ ይኽን መጽሐፍ ሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ ሆኖ ሳለ፣ መጠኑ ትልቅ ስለሆነ በቤት ቁጭ ተብሎ እንጂ ለኪዳንም [ሆነ] ለቅዳሴ ሲሄዱ ይዘውት ሊንቀሳቀሱ ባለመቻሉ ቀዳሹም አስቀዳሹም በቀላሉ [ሊጠቀሙበት አልቻሉም]። ስለዚህ “አኰቴተ ቊርባን” መጠኑ ትልቅ ስለሆነ፣ የታተመው እንዳለ ባለው ይዘት ኅትመቱ ቀጥሎ፣ ዘወትር በቅዳሴ የሚሳተፉ ምእመናን በቀላሉ ከጸሎት መጽሐፋቸው ጋር ሊይዙት በሚችሉት መጠን ቀዳሹና አስቀዳሹ ሊያውቁት የሚገባውን ክፍል ስለቅዳሴ ለብቻ አውጥቶ በትንሹ መታተም ቢችል እጅግ በጣም ጥሩ ነው ብዬ ይህን የአደራ መልእክት አስተላልፋለሁ። (ትልቁ የቅዳሴው መጽሐፍ እያለ፤ ለምዕመናን [ለተሰጥዎ] መማሪያ ተብሎ በትንሹ በጸሎት መጽሐፍ መልክ እንደተዘጋጀው ዓይነት ማለት ነው)።

ብሌን ታከለ የቶሮንቶ መንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል አባል ናት፡፡ የቅዳሴን ጣዕም ከልጅነቷ ጀምሮ የቀመሰችና ባደገችበት የሐዋሳ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ታላቅ የአገልግሎት ተሳትፎ የነበራት ልጅ ስለሆነች፣ አኰቴተ ቊርባን እጇ ውስጥ እንደገባ በደስታ አነበበችው፡፡ አቀራረቡን አስመልክቶ ግን ለየት ያለ አስተያየት ሰጠችኝ፡፡ “ቅዳሴን በትረካ መልኩ ያቀረበ መጽሐፍ መስሎኝ ነበር” አለች ብሌን፡፡ ይህን አስተያየት በርካታ ምእመናን ሊጋሩት እንደሚችሉ ተረዳሁ፡፡ ስለዚህ ይህ መጽሐፍ “ፍቅርተ ኢየሱስ” የተባለች፣ በጌታ የተወደደች፣ በደሙ እንደተዋጀች የምታውቅና የቅዳሴን ውበት እንድታይ በቅዱስ ቃሉ ትምህርት ዐይነ ልቡናዋ የበራላት ምእመን፣ ቅዳሴው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ በጣዕመ ዜማው፣ ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት በሚነበቡ ምንባባት፣ በቅዳሴው ጸሎትና ዑደት ሐሴት እያደረገች የቅዳሴው ተሳታፊ የምትሆንበትን ሂደት በዝርዝር ለማስረዳት ይሞክራል፡፡ ፍቅርተ ኢየሱስ ለቅዳሴ ካላት ፍቅር የተነሣ ዘወትር እሑድና በዐበይት በዓላት የቅዳሴ ተሳታፊ ስለምትሆን፣ ምእመናን ለዲያቆናቱና ለካህናቱ የሚሰጡትን የዜማ መልስ (ተሰጥዎ) በሚገባ ታውቃለች፤ መቅደሱ ላይ ያለውን የጌታ ስቅለት ሥዕል እያየች ዐይነ ልቡናዋን ወደ ቀራንዮ አቅንታ፣ ድምጽዋን ከፍ አድርጋ ታዜማለች፡፡ በሥርዓተ አምልኮው ከሚከናወኑ ድርጊቶች መካከል ምሳሌያዊ ትርጉሙ ያልገባት ነገር ካለ ወይም በአብዛኛው ከሚቀደሱት ቅዳሴያት ለየት ያለ ቅዳሴ (ለምሳሌ ቅዳሴ ሠለስቱ ምእት፣ ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፣ ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ ወዘተ.) ከተቀደሰ፣ የንስሐ አባትዋን ቀሲስ ፍቅረ መለኮትን ትጠይቃለች፡፡ እርሳቸውም መጽሐፈ ቅዳሴውን ይዘው የአማርኛውን ትርጉም እያስነበቡ ጥያቄዎቿን በሙሉ በዕርጋታና በዝርዝር ይመልሱላታል፡፡

ይህ መጽሐፍ ማንኛውም የቤተ ክርስቲያናችን አባል ስለ ቅዳሴ ሊያውቃቸው የሚገባቸውን መሠረታዊ ትምርህቶች ለማቅረብ ሙከራ አድርጓል፡፡ ትምህርተ ቅዳሴው የቀረበበትም መንገድ፣ የቅዳሴውን ሦስት ዋና ዋና ክፍልች በመከተልና ከየክፍሉ በተመረጡ አርእስት ላይ መጠነኛ ሐተታ (ገለጻ) በመስጠት ሲሆን፣ ፍቅርተ ኢየሱስ የተባለች ገጸ-ባሕርይ የቤተ ክርስቲያናችንን ምእመናን እንድትወክል ተደርጓል፡፡ በሦስቱ የቅዳሴ ክፍሎች ሥር የቀረቡ ትምህርቶችን በምዕራፍ ከመከፋፈል ይልቅ፣ “ቡራኬ 1፣ ቡራኬ 2 . . .” የሚል ስያሜን መርጫለሁ፡፡ ባጠቃላይ መጽሐፉ በሦስት ዐበይት ክፍሎችና በሃያ አንድ (21) ቡራኬያት የተከፈል ሲሆን፣ ትምህርታዊ ገላጻ የተሰጠባቸው ሃያ አንዱ ቡራኬያት፣ ሠራዒው ካህን በቅዳሴ ሰዓት የሚያከናውናቸውን ሃያ አንድ የአፍኣ (የውጭ) እና የውስጥ ቡራኬያትን ያስታውሱናል፡፡

በመጽሐፉ ውስጥ ለተጠቀሱ የግእዝ ቃላትና የሥርዓተ አምልኮ ስያሜያት (liturgical terminologies) መፍትሔ ቃላት (glossary) ተዘጋጅቷል፡፡ ምእመናንን ወክላ በዚህ መጽሐፍ የቅዳሴውን ሂደት በተመስጦ፣ አንዳንዴም በዕንባ፣ የምትከታተለው ፍቅርተ ኢየሱስ የቅዳሴ ጸበል ብቻ ጠጥታ ወደ ቤቷ የምትመለስ ሳትሆን፣ ጌታችን ኢየሱስ በቅዱስ ወንጌል “ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው” (ዮሐ. 6፡51) እንዳለ፣ ከኃጢአት በሽታ የምትፈወስበትን ኅብስተ ሕይወትና ጽዋዐ አኰቴት (ሥጋውና ደሙን) የምትቀበል ኦርቶዶክሳዊት ክርስቲያን ናት፡፡ ፍቅርተ ኢየሱስን በምናባቸው እየሳሉ ይህን መጽሐፍ የሚያነብቡ፣ ነገር ግን ከቅዱስ ቊርባን የራቁ ወይም ከተቀበሉ ዓመታትን ያስቆጠሩ የቤተ ክርስቲያናችን አባላት በእውነተኛ ንስሐና በምክረ ካህን ተዘጋጅተው “ጸጋ ሆኖ የተሰጠንን ሥጋውንና ደሙን በእግዚአብሔር ጥበብ” እንደሚቀበሉ ተስፋ አደርጋለሁ - መልካም ንባብ፡፡
ቀሲስ መብራቱ ኪሮስ (Ph.D.)
ቶሮንቶ፣ ካናዳ

BY የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች


Share with your friend now:
tgoop.com/bahiretibebat/8211

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Developing social channels based on exchanging a single message isn’t exactly new, of course. Back in 2014, the “Yo” app was launched with the sole purpose of enabling users to send each other the greeting “Yo.” 6How to manage your Telegram channel? Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value. bank east asia october 20 kowloon 1What is Telegram Channels?
from us


Telegram የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች
FROM American