BEMALEDANEK Telegram 2079
2•  ንስሐ

   2.1•  ንስሐ ምንድነው?

ክፍል - ፩

    ✞ ፊትን ወደ እግዚአብሔር ጀርባን ወደ ዓለም ✞

   አዳምን ወላጅ ሆኖ ያስገኘ የሥጋ ማኅፀን የለም፡፡ ለመጀመሪያው የሰው ልጅ የመጀመሪያ እናትና አባት አልነበረውም፡፡ የአዳም እናቱም አባቱም የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፡፡ አዳም የተጸነሰባት ማኅፀን የአምላክ ፈቃድ ነበረች፡፡

   ቀዳሚው የሰው ልጅ ከተጸነሰ በኋላ እስኪወለድ ድረስ በምቾት የኖረባት ስፍራ ዔድን ገነት ትባላለች፡፡ ልጅ ከእናት ማኅፀን ተወልዶ ዓይኑን በመግለጥ የመጣበትን ዓለም ለማወቅ እንደሚጀምር፤ የእውቀትን ዛፍ ገና ያልበላው አዳም በገነት ሳለ በእግዚአብሔር የፈቃድ ማኅፀን ውስጥ ነው የነበረው፡፡ ወይንም በቀላሉ ገነትን አዳምን አርግዛ እንዳለች አንዲት ነፍሰጡር በምናብ እንሳላት፡፡ የነፍሰጡሯ የእርግዝና ወራት (አዳም በገነት የሚቆይበት ጊዜ ማለት ነው) "በእግዚአብሔር አንድ ቀን በሰው ልጅ አንድ ሺህ ያህል ዓመት ነበር፡፡" (2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፥8)

   ሺህውም ዓመት ሲፈጸም (ስድስተኛውን ቀን ሲጨርስ) አዳም ከገነት ይወለዳል፡፡ ማለት በሰባተኛው ቀን ላይ የሰው ልጅ ከእውቀት ዛፍ በልቶ ዓይኑን በመግለጥ በወላጁ (በእግዚአብሔር) ክንድ ውስጥ ይታቀፋል፡፡ ወደ ቀጣዩ ሥርዓት ማደግ (መርቀቅ) ይጀምራል፡፡

   የቀደመው ወንዱ ልጅ በገነት መኖሩን እንደቀጠለ፤ በራእየ ዮሐንስ ምዕራፍ ዐሥራ ሁለት ላይ የተጠቀሰው ዘንዶ ብዙ ነፍሳትን በልቶ ሳይወፍር በፊት "የቀደመው እባብ" ሳለ በአትክልቱ ስፍራ ውስጥ የቀደመቺው ሴት ፊት [አዳምን ሊበላ አስቦ] ቆመ፡፡

   ዘንዶው ከሰማይ ሥርዓት ከእግዚአብሔር እውነትና ፈቃድ በማፈንገጥ ወድቋል፡፡ በዚህም የተነሣ ውድቀት የክፉው መንፈስ ልዩ ማንነትና መገለጫ ባሕሪይ ሆኗል፡፡ ስለ መውደቅ ስናነሣ፤ ውድቀት ወደ ታች እንጂ ወደ ላይ አይመለከተውም፡፡ ምክንያቱም ወደ ላይ አይወደቅም፡፡ በመሆኑም ዲያቢሎስ በመውደቅ ውስጥ ባለ ጠባይ ራሱን ስለሚገልጥ፤ የአሳቡም ሆነ የሥራው መነሻና መድረሻ ሕግ ሁልጊዜ ራሱንም ሌላውንም ወደ ታች መጣል ነው፡፡

   ከላይ በተጨዋወትነው መሠረት፤ የአዳም ሰብአዊ ባሕሪይ ከስድስተኛው ቀን ወደ ላይኛው ሰባተኛው ቀን በመጓዝ ላይ ነበር፡፡ በማብራሪያ ግልጽ ለማድረግ፤ የሰው ልጅ መጀመሪያ የተፈጠረበት ሰብአዊ ተክለ ቁመና ሙሉ በሙሉ ሕያው በመሆንና ባለመሆን መካከል ቦታ ያለ ነበር፡፡ እናም የአዳም ባሕሪይ ከዚህ ከመካከል ላይ ተነሥቶ ፍጹም ሆኖ ወደ ሚቀጥለው ሥርዓት ወደ ሚረቅበት ልዕልና ለመሻገር ሺውን ዓመት በገነት ጨርሶ የሕይወትን እና የእውቀትን ዛፍ በየጊዜያቸው መብላት ያስፈልገው ነበር፡፡

   ሆኖም ውድቀትን በላዩ ይዞ የሚንቀሳቀሰው መንፈስ፤ የፍጡራን ከእግዚአብሔር ፈቃድ መውጣት ልክ እንደርሱ ወደታች መጣልን እንደሚያስከትል ከራሱ ስለተገነዘበ፤ "አትብላ!" ብሎ እግዚአብሔር ያለ ቀኑ እንዳይበላት የከለከለውን የዛፍ ፍሬ እንዲበላ "ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ" ባላት አካሉ በኩል አዳምን ገፋፋው (መንፈስ ከውስጥ ሲገባ ከገዛ አካላችን ጋር መፋለም የመሰለ ጦርነት ነው የሚከፍተው)፡፡ ያቀደውም ሆነለት፡፡ "አዳም ሆይ ከወላጅህ ከእግዚአብሔር ይልቅ የሚስትህን ፈቃድ ለመፈጸም ወድደሃልና፤ ወደ መጣህበት መሬት ተመለስ፡፡ አፈር ነህና፤ ወደ አፈርም ትመለሳለህ" የሚል ቃል ከአምላክ ተደመጠ፡፡ የሰው ልጅ ሕልውና ወደ ሰባተኛው ቀን መርቀቅ ትቶ ወደ ኋላ ወደ አንደኛው ቀን (አፈር የተፈጠረው በመጀመሪያው ቀን ነው) በመመለሱ ምክንያት ዲያቢሎስ ውጥኑ ሰመረለት፡፡ ወደ ላይ ከማረግ ይልቅ እንደርሱ ወደታች መውደቅን አዳም በባሕሪዩ እንዲያውቀው አደረገው፡፡

   አዳም ከገነት (ከፈቃደ እግዚአብሔር) ወጥቶ ወደ መጣበት ምድር (የእግዚአብሔር አሳብ ወዳልነበረው) መሬት ሲመለስ፤ መቼም ጀርባውን ለአምላክ ፊቱን ለምድር ሰጥቶ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ አዳም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ተለይቶ በመውጣት የሰው ፈቃድ ወዳመጣው ከፀሐይ ሥርዓት በታች በተወሰነ አኗኗር ውስጥ ገባ፡፡ የአዳምና የሔዋን ከገነት ተለይቶ መውጣት በአካል ብቻ የተከናወነ ሳይሆን፤ በባሕሪይም ጭምር የሚገለጥ እውነት ነው፡፡ ለምሳሌ በአዳም ባሕሪይ ውስጥ የተሰማው ሞት የሰውነትን ባሕሪይ በሚይዙት የአዳም ልጆች ላይ ሁሉ ይዋረሳል፡፡ በተለምዶ "የአዳም ኃጢአት" እየተባለ የሚነገረውም ጉዳይ ይህ ነው፡፡ ስለዚህ አዳም በባሕሪይው ጭምር ነው ከገነት የወጣው ስንል፤ የአዳም ልጆች የሆኑት ሰዎች ሁሉ የሕይወት ገጻቸውን  ወደ መጡበት ምድር (ሥጋ) አዙረው፤ ለእግዚአብሔር ፈቃድና እውነት (ለነፍስ) ጀርባ ሰጥተው ከአምላካቸው ፈቃድ እየወጡ .. እየወጡ ይኖራሉ እያልን ነው፡፡

   ንስሐ የምንላት መንፈሳዊ ሚስጢርም የምትመጣው እዚህ አዳም ፊቱን ከእግዚአብሔር አዙሮ ከወጣባት ቅጽበት ጀምሮ ነው፡፡ የሰው ልጅ "እንደ አምላክ" በመሆን ከንቱ ምክር ተታልሎ ከፈጣሪው ከተጣላ በኋላ፤ አስታራቂ ማኅተም ሆና ከመሃል የምትገባው ረቂቅ ኃይል ንስሐ የምንላት የምሕረት ክፍል ናት፡፡

   ንስሐ የሚለው ቃል በጥሬ ትርጓሜው ጸጸት፣ ሐዘን፣ ቁጭት፣ ቅጣት፣ የኃጢአት ካሳ ማለት ነው (የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት)፡፡ ይህንንም ብያኔ ወደ አዳም ታሪክ መልሰን ስናየው፤ አዳም ከእውቀት ዛፍ በልቶ ራቁቱን መሆኑን ዓይኖቹን ገልጦ ባወቀ ጊዜ፤ የእግዚአብሔርን ሕግ በመተላለፉ ከውስጡ ጠባይ የነቃ ፍርሃት፣ ባዶነት፣ ብቸኝነትና መገፈፍ ተሰምቶታል፡፡ እነዚህ ስሜቶች በኋላ እጅ ለእጅ ተያይዘው አዳምን ንስሐ ወደምንለው ቦታ አምጥተውታል፡፡ አዳም ባጠፋው ጥፋት ራሱን እየወቀሰ (ቁጭት)፤ ለምን በላሁት በሚል አሳብ እየተብሰከሰከ (ጸጸት)፤ ስላጣው ጸጋና ኃይል እየተከዘ (ሐዘን)፤ እግዚአብሔር ይምረው ዘንድ ለመጠየቅ ለረጅም ጊዜያት ራሱን እየገሠጸና እያለቀሰ ሱባዔ ይዟል (ቅጣትና የበደል ካሳ)፡፡

   እስከአሁን በተነጋገርነው መሠረት ላይ ሆነን ንስሐን ጠቅልለን ስናየው፤ ንስሐ ማለት የሰው ልጆች ባሕሪይ አቅጣጫውን አስተካክሎ ፊቱን ወደ እግዚአብሔር ጀርባውን ወደ ውድቀት የሚያዞርበት ሰማያዊ ሂደት ነው፡፡

   አንድ አማኝ ሰው ንስሐ ገባ ስንል፤ እርምጃውን ወደ እግዚአብሔር መንገድ አቀና እያልን ነው፡፡ በአዳምኛው ቋንቋ ስንናገረው፤ "ወደ መጣችሁበት ተመለሱ" ሲል ወደ ወደድነው የሥጋ ፈቃድ እንድንመለስ ምርጫችንን አክብሮ ለለቀቀን አምላክ፤ "የለም የለም ጌታ ሆይ፥ ተሳስቼ ነውና ወዳንተ (ወደ ነፍስ ፈቃድ) መመለስ እፈልጋለሁ" ብለን የምንናገርበት የተቀደሰ ድምፅ ነው፡፡

   በአንጻሩ ንስሐ አልገባንም ማለት፤ ፊታችንን ወደ ዓለም ጀርባችንን ወደ እግዚአብሔር ሰጥተን እየተጓዝን ነው ማለት ነው፡፡ ንስሐ ሳንገባ የነፍስ ፈቃድ የሆነ መንፈሳዊ ሕይወት እንኳ ቢኖረን፤ የእምነት አካሄዳችን ጀርባውን ለእግዚአብሔር እንደሰጠ ወደ እግዚአብሔር እንደመሄድ ያለ የኋልዮሽ ጉዞ ነው የሚሆነው፡፡ ፊቱን ለአውራ ጎዳናው ቀጥ አድርጎ መጓዝ ሲችል፤ ወደኋላ እየሄደ መንገዱን የሚያቋርጥ መኪናን ጥሩ ምሳሌ አድርገን ለዚህ እንጠቅሳለን፡፡

በእርግጥም ከንስሐ ራቅ ብሎ የሚገኝ ኑሮአችንን አጢነን ስናየው፤ ፍላጎቱን፣ እቅዱን፣ ሩጫውን፣ ጉልበቱንና ጊዜውን ለሥጋ ጉዳዮች አብዝቶ እያዋለ፤ ከተፈጥሮው ውስጥ ሕይወት ሆና ስለምታንቀሳቅሰው ነፍሱ ግን አጥርቶ ማስተዋል ተስኖት ይታያል፡፡ ይሄ መሬት የረገጠ እውነት ነው ፊትን ወደ ዓለም ጀርባን ወደ አምላክ የሚያሰኘው፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2079
Create:
Last Update:

2•  ንስሐ

   2.1•  ንስሐ ምንድነው?

ክፍል - ፩

    ✞ ፊትን ወደ እግዚአብሔር ጀርባን ወደ ዓለም ✞

   አዳምን ወላጅ ሆኖ ያስገኘ የሥጋ ማኅፀን የለም፡፡ ለመጀመሪያው የሰው ልጅ የመጀመሪያ እናትና አባት አልነበረውም፡፡ የአዳም እናቱም አባቱም የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፡፡ አዳም የተጸነሰባት ማኅፀን የአምላክ ፈቃድ ነበረች፡፡

   ቀዳሚው የሰው ልጅ ከተጸነሰ በኋላ እስኪወለድ ድረስ በምቾት የኖረባት ስፍራ ዔድን ገነት ትባላለች፡፡ ልጅ ከእናት ማኅፀን ተወልዶ ዓይኑን በመግለጥ የመጣበትን ዓለም ለማወቅ እንደሚጀምር፤ የእውቀትን ዛፍ ገና ያልበላው አዳም በገነት ሳለ በእግዚአብሔር የፈቃድ ማኅፀን ውስጥ ነው የነበረው፡፡ ወይንም በቀላሉ ገነትን አዳምን አርግዛ እንዳለች አንዲት ነፍሰጡር በምናብ እንሳላት፡፡ የነፍሰጡሯ የእርግዝና ወራት (አዳም በገነት የሚቆይበት ጊዜ ማለት ነው) "በእግዚአብሔር አንድ ቀን በሰው ልጅ አንድ ሺህ ያህል ዓመት ነበር፡፡" (2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3፥8)

   ሺህውም ዓመት ሲፈጸም (ስድስተኛውን ቀን ሲጨርስ) አዳም ከገነት ይወለዳል፡፡ ማለት በሰባተኛው ቀን ላይ የሰው ልጅ ከእውቀት ዛፍ በልቶ ዓይኑን በመግለጥ በወላጁ (በእግዚአብሔር) ክንድ ውስጥ ይታቀፋል፡፡ ወደ ቀጣዩ ሥርዓት ማደግ (መርቀቅ) ይጀምራል፡፡

   የቀደመው ወንዱ ልጅ በገነት መኖሩን እንደቀጠለ፤ በራእየ ዮሐንስ ምዕራፍ ዐሥራ ሁለት ላይ የተጠቀሰው ዘንዶ ብዙ ነፍሳትን በልቶ ሳይወፍር በፊት "የቀደመው እባብ" ሳለ በአትክልቱ ስፍራ ውስጥ የቀደመቺው ሴት ፊት [አዳምን ሊበላ አስቦ] ቆመ፡፡

   ዘንዶው ከሰማይ ሥርዓት ከእግዚአብሔር እውነትና ፈቃድ በማፈንገጥ ወድቋል፡፡ በዚህም የተነሣ ውድቀት የክፉው መንፈስ ልዩ ማንነትና መገለጫ ባሕሪይ ሆኗል፡፡ ስለ መውደቅ ስናነሣ፤ ውድቀት ወደ ታች እንጂ ወደ ላይ አይመለከተውም፡፡ ምክንያቱም ወደ ላይ አይወደቅም፡፡ በመሆኑም ዲያቢሎስ በመውደቅ ውስጥ ባለ ጠባይ ራሱን ስለሚገልጥ፤ የአሳቡም ሆነ የሥራው መነሻና መድረሻ ሕግ ሁልጊዜ ራሱንም ሌላውንም ወደ ታች መጣል ነው፡፡

   ከላይ በተጨዋወትነው መሠረት፤ የአዳም ሰብአዊ ባሕሪይ ከስድስተኛው ቀን ወደ ላይኛው ሰባተኛው ቀን በመጓዝ ላይ ነበር፡፡ በማብራሪያ ግልጽ ለማድረግ፤ የሰው ልጅ መጀመሪያ የተፈጠረበት ሰብአዊ ተክለ ቁመና ሙሉ በሙሉ ሕያው በመሆንና ባለመሆን መካከል ቦታ ያለ ነበር፡፡ እናም የአዳም ባሕሪይ ከዚህ ከመካከል ላይ ተነሥቶ ፍጹም ሆኖ ወደ ሚቀጥለው ሥርዓት ወደ ሚረቅበት ልዕልና ለመሻገር ሺውን ዓመት በገነት ጨርሶ የሕይወትን እና የእውቀትን ዛፍ በየጊዜያቸው መብላት ያስፈልገው ነበር፡፡

   ሆኖም ውድቀትን በላዩ ይዞ የሚንቀሳቀሰው መንፈስ፤ የፍጡራን ከእግዚአብሔር ፈቃድ መውጣት ልክ እንደርሱ ወደታች መጣልን እንደሚያስከትል ከራሱ ስለተገነዘበ፤ "አትብላ!" ብሎ እግዚአብሔር ያለ ቀኑ እንዳይበላት የከለከለውን የዛፍ ፍሬ እንዲበላ "ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ" ባላት አካሉ በኩል አዳምን ገፋፋው (መንፈስ ከውስጥ ሲገባ ከገዛ አካላችን ጋር መፋለም የመሰለ ጦርነት ነው የሚከፍተው)፡፡ ያቀደውም ሆነለት፡፡ "አዳም ሆይ ከወላጅህ ከእግዚአብሔር ይልቅ የሚስትህን ፈቃድ ለመፈጸም ወድደሃልና፤ ወደ መጣህበት መሬት ተመለስ፡፡ አፈር ነህና፤ ወደ አፈርም ትመለሳለህ" የሚል ቃል ከአምላክ ተደመጠ፡፡ የሰው ልጅ ሕልውና ወደ ሰባተኛው ቀን መርቀቅ ትቶ ወደ ኋላ ወደ አንደኛው ቀን (አፈር የተፈጠረው በመጀመሪያው ቀን ነው) በመመለሱ ምክንያት ዲያቢሎስ ውጥኑ ሰመረለት፡፡ ወደ ላይ ከማረግ ይልቅ እንደርሱ ወደታች መውደቅን አዳም በባሕሪዩ እንዲያውቀው አደረገው፡፡

   አዳም ከገነት (ከፈቃደ እግዚአብሔር) ወጥቶ ወደ መጣበት ምድር (የእግዚአብሔር አሳብ ወዳልነበረው) መሬት ሲመለስ፤ መቼም ጀርባውን ለአምላክ ፊቱን ለምድር ሰጥቶ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ አዳም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ተለይቶ በመውጣት የሰው ፈቃድ ወዳመጣው ከፀሐይ ሥርዓት በታች በተወሰነ አኗኗር ውስጥ ገባ፡፡ የአዳምና የሔዋን ከገነት ተለይቶ መውጣት በአካል ብቻ የተከናወነ ሳይሆን፤ በባሕሪይም ጭምር የሚገለጥ እውነት ነው፡፡ ለምሳሌ በአዳም ባሕሪይ ውስጥ የተሰማው ሞት የሰውነትን ባሕሪይ በሚይዙት የአዳም ልጆች ላይ ሁሉ ይዋረሳል፡፡ በተለምዶ "የአዳም ኃጢአት" እየተባለ የሚነገረውም ጉዳይ ይህ ነው፡፡ ስለዚህ አዳም በባሕሪይው ጭምር ነው ከገነት የወጣው ስንል፤ የአዳም ልጆች የሆኑት ሰዎች ሁሉ የሕይወት ገጻቸውን  ወደ መጡበት ምድር (ሥጋ) አዙረው፤ ለእግዚአብሔር ፈቃድና እውነት (ለነፍስ) ጀርባ ሰጥተው ከአምላካቸው ፈቃድ እየወጡ .. እየወጡ ይኖራሉ እያልን ነው፡፡

   ንስሐ የምንላት መንፈሳዊ ሚስጢርም የምትመጣው እዚህ አዳም ፊቱን ከእግዚአብሔር አዙሮ ከወጣባት ቅጽበት ጀምሮ ነው፡፡ የሰው ልጅ "እንደ አምላክ" በመሆን ከንቱ ምክር ተታልሎ ከፈጣሪው ከተጣላ በኋላ፤ አስታራቂ ማኅተም ሆና ከመሃል የምትገባው ረቂቅ ኃይል ንስሐ የምንላት የምሕረት ክፍል ናት፡፡

   ንስሐ የሚለው ቃል በጥሬ ትርጓሜው ጸጸት፣ ሐዘን፣ ቁጭት፣ ቅጣት፣ የኃጢአት ካሳ ማለት ነው (የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት)፡፡ ይህንንም ብያኔ ወደ አዳም ታሪክ መልሰን ስናየው፤ አዳም ከእውቀት ዛፍ በልቶ ራቁቱን መሆኑን ዓይኖቹን ገልጦ ባወቀ ጊዜ፤ የእግዚአብሔርን ሕግ በመተላለፉ ከውስጡ ጠባይ የነቃ ፍርሃት፣ ባዶነት፣ ብቸኝነትና መገፈፍ ተሰምቶታል፡፡ እነዚህ ስሜቶች በኋላ እጅ ለእጅ ተያይዘው አዳምን ንስሐ ወደምንለው ቦታ አምጥተውታል፡፡ አዳም ባጠፋው ጥፋት ራሱን እየወቀሰ (ቁጭት)፤ ለምን በላሁት በሚል አሳብ እየተብሰከሰከ (ጸጸት)፤ ስላጣው ጸጋና ኃይል እየተከዘ (ሐዘን)፤ እግዚአብሔር ይምረው ዘንድ ለመጠየቅ ለረጅም ጊዜያት ራሱን እየገሠጸና እያለቀሰ ሱባዔ ይዟል (ቅጣትና የበደል ካሳ)፡፡

   እስከአሁን በተነጋገርነው መሠረት ላይ ሆነን ንስሐን ጠቅልለን ስናየው፤ ንስሐ ማለት የሰው ልጆች ባሕሪይ አቅጣጫውን አስተካክሎ ፊቱን ወደ እግዚአብሔር ጀርባውን ወደ ውድቀት የሚያዞርበት ሰማያዊ ሂደት ነው፡፡

   አንድ አማኝ ሰው ንስሐ ገባ ስንል፤ እርምጃውን ወደ እግዚአብሔር መንገድ አቀና እያልን ነው፡፡ በአዳምኛው ቋንቋ ስንናገረው፤ "ወደ መጣችሁበት ተመለሱ" ሲል ወደ ወደድነው የሥጋ ፈቃድ እንድንመለስ ምርጫችንን አክብሮ ለለቀቀን አምላክ፤ "የለም የለም ጌታ ሆይ፥ ተሳስቼ ነውና ወዳንተ (ወደ ነፍስ ፈቃድ) መመለስ እፈልጋለሁ" ብለን የምንናገርበት የተቀደሰ ድምፅ ነው፡፡

   በአንጻሩ ንስሐ አልገባንም ማለት፤ ፊታችንን ወደ ዓለም ጀርባችንን ወደ እግዚአብሔር ሰጥተን እየተጓዝን ነው ማለት ነው፡፡ ንስሐ ሳንገባ የነፍስ ፈቃድ የሆነ መንፈሳዊ ሕይወት እንኳ ቢኖረን፤ የእምነት አካሄዳችን ጀርባውን ለእግዚአብሔር እንደሰጠ ወደ እግዚአብሔር እንደመሄድ ያለ የኋልዮሽ ጉዞ ነው የሚሆነው፡፡ ፊቱን ለአውራ ጎዳናው ቀጥ አድርጎ መጓዝ ሲችል፤ ወደኋላ እየሄደ መንገዱን የሚያቋርጥ መኪናን ጥሩ ምሳሌ አድርገን ለዚህ እንጠቅሳለን፡፡

በእርግጥም ከንስሐ ራቅ ብሎ የሚገኝ ኑሮአችንን አጢነን ስናየው፤ ፍላጎቱን፣ እቅዱን፣ ሩጫውን፣ ጉልበቱንና ጊዜውን ለሥጋ ጉዳዮች አብዝቶ እያዋለ፤ ከተፈጥሮው ውስጥ ሕይወት ሆና ስለምታንቀሳቅሰው ነፍሱ ግን አጥርቶ ማስተዋል ተስኖት ይታያል፡፡ ይሄ መሬት የረገጠ እውነት ነው ፊትን ወደ ዓለም ጀርባን ወደ አምላክ የሚያሰኘው፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2079

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Administrators Unlimited number of subscribers per channel Healing through screaming therapy best-secure-messaging-apps-shutterstock-1892950018.jpg 1What is Telegram Channels?
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American