BEMALEDANEK Telegram 2314
በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
2•  ንስሐ    2.2•  ንስሐ ለምን እንግባ? ክፍል - ፬                    ✞ አዲሱ ወይን እንዲሞላ ✞ "በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አቁማዳው ይፈነዳል፥ የወይን ጠጁም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል፤ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።" (የማቴዎስ ወንጌል 9፥17) አንድምታ ጸሐፊዎች ጥቅሱን እንዲህ…
2•  ንስሐ

   2.3•  ንስሐ እንዴት ብለን እንግባ?

ክፍል - ፭

             ✞ ኃጢአትን መጠየፍ

"እንደ እርሱም ርጉም እንዳትሆን ርኩስን ነገር ወደ ቤትህ አታግባ፤ ርጉም ነውና ተጸየፈው፥ ጥላውም።" (ኦሪት ዘዳግም 7፥26)

   ከእውቀት ዛፍ በልተናል፡፡ ስለዚህ መልካሙንና ክፉውን በማወቅ መለየት ችለናል፡፡ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የፈቃድ እቅፍ (ገነት) ሳለን ባሕሪያችን የክፉውን ቃል አላደመጠም ነበር፡፡  በኋላ ግን የእባቡን ምክር ተቀብለን ያለቀኑ አትንኩት የተባልነውን ፍሬ በልተን ከአምላክ ትእዛዝ በመውጣት ዓምፀናል፤ ኃጢአት ሠርተናል፡፡

   ከዚህ በኋላ አዳማዊ ባሕሪያችን ኃጢአትን መፈጸም የሚችል ባሕሪይ ሆኗል፡፡ ምክንያቱም ክፉውን እውቀት እንዲለይ ዓይኖቻችን ተከፍተዋል፡፡ ነገሩን ግልጽ ለማድረግ የሕፃናትን ሁኔታ እንመልከት፡፡ ልጆች እንደተወለዱ እውቀት የላቸውም፡፡ ስለ እዚህ ዓለም ሥርዓት፣ ስለ ራሳቸው ማንነት፣ ስለ ወላጆቻቸው፣ .. አያውቁም፡፡ በመሆኑም ኃጢአትን አይፈጽሙም፡፡ አይዋሹም፣ አይታልሉም፣ አይሰሩቅም፡፡ ለመዋሸት እንዲቻል መጀመሪያ እውነት የሆነውን በግርድፉ እንኳ ማወቅ ይገባልና፤ በአእምሮ ስሌት የማይመሩት ሕፃናት ልባቸው ወደሚስባቸው እየተጓዙ ያድጋሉ፡፡ ልብ ደግሞ የአባት ምሳሌ ነው፡፡ ከእርሱም የእውነት ቃል ይወለድበታል፥ ቅዱስ መንፈስ ይሠርጽበታል፡፡

   ማደግ ሲመጣ ግን እውቀት አብሮ ይመጣል፡፡ በሌላ አነጋገር ከእውቀት ዛፍ እንቀምሳለን፡፡ "ይሄ እሳት ነው እፉ ነው ያቃጥላል፣ ይሄ ቆሻሻ ነው ጣለው፣ ይሄ ብር ነው የምትፈልገውን ይገዛልሃል፣ .." እየተባልን ደጉንም ክፉውንም እንድንለይ እንማራለን፡፡ በተለምዶ ነፍስ ለማወቅ ደረስን እስከሚያሰኝበት ጊዜ ድረስ ወላጆቻችንና ታላላቆቻችን ያግዙናል፡፡ በአዳም ታሪክ ስናወራው የሰው ልጅ የእውቀትን ዛፍ ከበላ በኋላ መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ርኩስም የየራሳቸውን እውቀት ይነግሩናል፤ ያሳዩናል፡፡

   አዳም ከፈጣሪው ሕያው ፈቃድ ሲያፈነግጥ፤ ለባሕሪይው የተሰሙት መራቆት፣ መገፈፍ፣ መፍራትና ብቸኛ መሆን ከስሕተት ላይ እንደወደቀ አረጋግጠውለታል፡፡ የእግዚአብሔርንም ቃል በገነት ሲመላለስ በሰማ ጊዜ በዱሩ መካከል ለመመሸግ ጣረ፡፡ ግን የቀደመው ሰላም አልተገኘም፡፡ ከራሱም ከፈጣሪውም ማምለጥ አልተቻለም፡፡ የማንነቱ ቀውስ አልተረጋጋለትም፡፡

    ይባስ ብሎ ፍርድን ተቀበለ፡፡ ምርጫው ተከበረለት፡፡ "ሥጋህን ማድመጥ ፈቅደሃልና ሂድ ወደ ሥጋህ" ተባለ፡፡ የነፍሱን ኃይል አጣት፡፡ ሕያውነት ከእርሱ ሸሸች፡፡

   አዳም ይሄን ጊዜ ዛፉን የበላበትን ቅጽበት አዘነበት፤ ጠላውም፡፡ ለዚህ ያበቃው ኃጢአቱን ተጸየፈው፡፡ ዓመፃን የፈጸመበት ታሪክ ናቀው፡፡ ከአምላኩ መስመር ተሻግሮ ለተራመደበት ፈቃዱ ተጸጸተ፡፡ ስለዚህ .. ንስሐ ገባ! "አጥፍቻለሁና ምሕረትህ ይደረግልኝ" አለ፡፡

   በዚህ መሠረት፤ አንድ ሰው ንስሐ ለመግባት ወድዶ እርምጃ አንድ ሲል፤ ኃጢአቱን ሁሉ ከመጸየፍ፤ ክፉውን ሁሉ ከመቃወም፤ ዓመፃን ሁሉ ከመሸሽ ይጀምራል፡፡

   ታስታውሱ እንደሆነ በምዕራፍ አንድ ቆይታችን ስለ ፍቅር ስንጨዋወት፤ "ፍቅር አልፋ ነው፥ ፍቅር ዖሜጋ ነው" ብለን አውግተናል፡፡ ፍቅር በእግዚአብሔር ባሕሪይነቱ አልፋ ሲሆን ከሁሉ የቀደመ ፊተኛና መነሻ ነውና፤ ንሰሐንም ፍቅር ይቀድመዋል (በነገራችን፥ ፍቅር ዖሜጋ ሲሆን ደግሞ የሁሉ ነገር ኋላኛ መደምደሚያ በመሆኑ የንሰሐ መንገድ ማብቂያ ፍቅር ነው)፡፡

   በፍቅር በኩል አገላለጻችንን ሰንደግመው፤ መነሻ እርምጃ ብለን ኃጢአትን ለመጸየፍ የምንችለው እውነተኛ የእግዚአብሔር ፍቅር ሲኖረን ብቻ ነው፡፡ እንደ ሕፃናቱ በልብ ምሪት ስንሄድ!

   እግዚአብሔርን ያላፈቀረ ሰውነት ኃጢአትን መጥላት አይሆንለትም፡፡ ምክንያቱም ዓመፃ በመልኳ ውብ ናት፤ በጣም ቆንጆ! ይህንን ጉዳይ ከመጀመሪያቱ ሴት በበለጠ በሚገባ የሚያውቀው ያለ አይመስለኝም፡፡ እንዴት?

"ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነለዓይንም እንደሚያስጎመጅለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።" (ኦሪት ዘፍጥረት 3፥6)

   ሔዋኒቱ የዛፉን ፍሬ ከመቀንጠሷ በፊት ዛፉን አይታዋለች፡፡ ስታየው ደግሞ ያማረ፣ የሚያስጎመጅና ጥበብ ሰጪ ሆኖ ነው የታያት፡፡ በቀመደው ጊዜ ውስጥ በዔድን ጫካ መካከል ወዲህና ወዲያ ስትል ይህ እይታ አልነበራትም፡፡ "አማካሪው" መንፈስ ጠጋ ብሎ ካወያያት በኋላ ግን ቅርጫፎቹ ወዝተው፣ ፍሬዎቹ ተሽሞንሙነው፣ ቅጠሎቹ ቆንጅተው ታዯት፡፡ አበቃቀሉ ሳይቀር ሳባት፡፡ በዛ ላይ እንደሰማቺው ደግሞ እንደ አምላክ የሚያደርግ፤ ጥበብ ሰጪ ሆነባት፡፡ የምታየውና የምትሰማው ፍጹም እውነት መሰላት (ዛሬ እኛ እንደሚመስለን)፡፡ መቋቋም ተሳናት፤ ከሚያብለጨልጨው ፍሬ ወስዳ ቀጠፈች! (በኋላ ተቀጠፈቺበት እንጂ!)

   ኃጢአትን እንዳንጠላ፤ ዲያቢሎስ ኃጢአትን አስውቦ ያሳየናል (ኋላሳ፥ ቆንጆን ማን ይጠላል?)፡፡ በተጨባጭ ላለው የስሜት ሕዋሳችን የሚስማማ አድርጎ ዓመፃን ያለማምደናል፡፡ ቀላል ምሳሌ ልጥቀስ፡፡

   ከኑሮ ጉያችን ዘወትር የማትጠፋው ውሸት ኃጢአት እንደሆነች ሰምተንም ይሁን አንብበን እናውቃለን፡፡ "በሐሰት አትመስክር!" የሚል ሕግ እንዳለ ተምረናል፡፡ በገነቱ አነጋገር ዛፉን "አትንኩ!" ተብለናል (የጽድቅ ሕጎች ሁሉ ከዛፉ ክልከላ የወጡ ናቸው)፡፡ ነገር ግን ሐሰትን በባሕሪዩ የሚናገራት መንፈስ ዛፉን አስጊጦ ያሳየናል፡፡ ለመዋሸት የሚመቹ በቂ ምክንያቶችንና አጋጣሚዎችን ከፊታችን ያስቀምጥልናል፡፡ በዚህም ሳያበቃ ባሕሪያችንን ተጠግቶ ባሕሪዩን ያካፍልናል፡፡ አመለካከቱን ያጋራናል፡፡ የእርሱ እይታ ደግሞ ሁልጊዜ እንደርሱ "ከሰማይ ስፍራ የተለየ ነው"፡፡

    ውሸት ከዛፉ ፍሬዎች መካከል አንዷ ናት፡፡ ስለሆነ "አትናገራት!" ተብለናል፡፡ ግን አንችልም፤ ውሸት ውብ ነችና አንጠላትም፡፡ "ከእርሷ በተናገራችሁ ጊዜ ሥራው ይቃናል፤ ሐብት ይካብታል፤ ወዳጅ ይበረክታል፤ ዕድል ይከፈታል፤ ጨዋታ ይደራል፤ ስኬት ይቀላል" የሚል ስብከትን ዓለምና ሥርዓቷ በእጅ አዙር (አንዳንዴም በቀጥታ) ይሰብኩናል፡፡ ውሸት አንዴ ተገምጣ አታጠግብም፡፡ በየቀኑ ትርባለች፡፡ አልፎ ተርፎ ባልንጀሮቿ ግብዝነትን፣ ጉቦን፣ ሙስናን እና ሌሎቹንም ተራ በተራ ታስጎበኛለች፡፡ አንጠላት ነገር በውበቷ ታስደምማለች፡፡ ስትደመጥ ትጣፍጣለች፤ እንደ እውነት አትመርም፡፡

   የእባቡ ዓይን ያፈዛል፡፡ ዓመፃውን ያሳምራል፤ ውድቀቱን ለጊዜው ይሸፍናል፡፡ ዝሙትን የሚጠላት ማግኘት ይከብዳል፡፡ እስኪፈጽሟት ድረስ ታጓጓለች፡፡ ሐሴትን የምትለግስ ትመስላለች፡፡ በሥጋ ሲያዯት እንከን አያወጡላትም፡፡ መልክአ ኤዶምን የጻፉ ደራሲ ያሉት ትዝ አለኝ፦

"ዓለም እኮ የወደዳትን መልሳ ታጠፋዋለች፡፡  በወጥመዷም አስገብታ ብዙውን ሕዝብ በመርዟ እንደገደለች ይህን ሥራዋን የሚያውቅባት ከቶ እንደምን ያለ ብልህና አዋቂ ይሁን?"

   ዓለም ከሕይወት ብሌናችን ፊት ውበቷ የደመቀ ነው፡፡ ለጆሮም አትከብድም፡፡ መዝናኛዎቿና አኳኋኗ ሁሉ ቄንጠኛ ናቸው፡፡ ውደዱኝ በሚል ማባብያ ትቅለሰለሳለች፡፡ ፍቅር መሳይ ጥላቻ ግን ውስጧን ሞልቶታል፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2314
Create:
Last Update:

2•  ንስሐ

   2.3•  ንስሐ እንዴት ብለን እንግባ?

ክፍል - ፭

             ✞ ኃጢአትን መጠየፍ

"እንደ እርሱም ርጉም እንዳትሆን ርኩስን ነገር ወደ ቤትህ አታግባ፤ ርጉም ነውና ተጸየፈው፥ ጥላውም።" (ኦሪት ዘዳግም 7፥26)

   ከእውቀት ዛፍ በልተናል፡፡ ስለዚህ መልካሙንና ክፉውን በማወቅ መለየት ችለናል፡፡ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የፈቃድ እቅፍ (ገነት) ሳለን ባሕሪያችን የክፉውን ቃል አላደመጠም ነበር፡፡  በኋላ ግን የእባቡን ምክር ተቀብለን ያለቀኑ አትንኩት የተባልነውን ፍሬ በልተን ከአምላክ ትእዛዝ በመውጣት ዓምፀናል፤ ኃጢአት ሠርተናል፡፡

   ከዚህ በኋላ አዳማዊ ባሕሪያችን ኃጢአትን መፈጸም የሚችል ባሕሪይ ሆኗል፡፡ ምክንያቱም ክፉውን እውቀት እንዲለይ ዓይኖቻችን ተከፍተዋል፡፡ ነገሩን ግልጽ ለማድረግ የሕፃናትን ሁኔታ እንመልከት፡፡ ልጆች እንደተወለዱ እውቀት የላቸውም፡፡ ስለ እዚህ ዓለም ሥርዓት፣ ስለ ራሳቸው ማንነት፣ ስለ ወላጆቻቸው፣ .. አያውቁም፡፡ በመሆኑም ኃጢአትን አይፈጽሙም፡፡ አይዋሹም፣ አይታልሉም፣ አይሰሩቅም፡፡ ለመዋሸት እንዲቻል መጀመሪያ እውነት የሆነውን በግርድፉ እንኳ ማወቅ ይገባልና፤ በአእምሮ ስሌት የማይመሩት ሕፃናት ልባቸው ወደሚስባቸው እየተጓዙ ያድጋሉ፡፡ ልብ ደግሞ የአባት ምሳሌ ነው፡፡ ከእርሱም የእውነት ቃል ይወለድበታል፥ ቅዱስ መንፈስ ይሠርጽበታል፡፡

   ማደግ ሲመጣ ግን እውቀት አብሮ ይመጣል፡፡ በሌላ አነጋገር ከእውቀት ዛፍ እንቀምሳለን፡፡ "ይሄ እሳት ነው እፉ ነው ያቃጥላል፣ ይሄ ቆሻሻ ነው ጣለው፣ ይሄ ብር ነው የምትፈልገውን ይገዛልሃል፣ .." እየተባልን ደጉንም ክፉውንም እንድንለይ እንማራለን፡፡ በተለምዶ ነፍስ ለማወቅ ደረስን እስከሚያሰኝበት ጊዜ ድረስ ወላጆቻችንና ታላላቆቻችን ያግዙናል፡፡ በአዳም ታሪክ ስናወራው የሰው ልጅ የእውቀትን ዛፍ ከበላ በኋላ መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ርኩስም የየራሳቸውን እውቀት ይነግሩናል፤ ያሳዩናል፡፡

   አዳም ከፈጣሪው ሕያው ፈቃድ ሲያፈነግጥ፤ ለባሕሪይው የተሰሙት መራቆት፣ መገፈፍ፣ መፍራትና ብቸኛ መሆን ከስሕተት ላይ እንደወደቀ አረጋግጠውለታል፡፡ የእግዚአብሔርንም ቃል በገነት ሲመላለስ በሰማ ጊዜ በዱሩ መካከል ለመመሸግ ጣረ፡፡ ግን የቀደመው ሰላም አልተገኘም፡፡ ከራሱም ከፈጣሪውም ማምለጥ አልተቻለም፡፡ የማንነቱ ቀውስ አልተረጋጋለትም፡፡

    ይባስ ብሎ ፍርድን ተቀበለ፡፡ ምርጫው ተከበረለት፡፡ "ሥጋህን ማድመጥ ፈቅደሃልና ሂድ ወደ ሥጋህ" ተባለ፡፡ የነፍሱን ኃይል አጣት፡፡ ሕያውነት ከእርሱ ሸሸች፡፡

   አዳም ይሄን ጊዜ ዛፉን የበላበትን ቅጽበት አዘነበት፤ ጠላውም፡፡ ለዚህ ያበቃው ኃጢአቱን ተጸየፈው፡፡ ዓመፃን የፈጸመበት ታሪክ ናቀው፡፡ ከአምላኩ መስመር ተሻግሮ ለተራመደበት ፈቃዱ ተጸጸተ፡፡ ስለዚህ .. ንስሐ ገባ! "አጥፍቻለሁና ምሕረትህ ይደረግልኝ" አለ፡፡

   በዚህ መሠረት፤ አንድ ሰው ንስሐ ለመግባት ወድዶ እርምጃ አንድ ሲል፤ ኃጢአቱን ሁሉ ከመጸየፍ፤ ክፉውን ሁሉ ከመቃወም፤ ዓመፃን ሁሉ ከመሸሽ ይጀምራል፡፡

   ታስታውሱ እንደሆነ በምዕራፍ አንድ ቆይታችን ስለ ፍቅር ስንጨዋወት፤ "ፍቅር አልፋ ነው፥ ፍቅር ዖሜጋ ነው" ብለን አውግተናል፡፡ ፍቅር በእግዚአብሔር ባሕሪይነቱ አልፋ ሲሆን ከሁሉ የቀደመ ፊተኛና መነሻ ነውና፤ ንሰሐንም ፍቅር ይቀድመዋል (በነገራችን፥ ፍቅር ዖሜጋ ሲሆን ደግሞ የሁሉ ነገር ኋላኛ መደምደሚያ በመሆኑ የንሰሐ መንገድ ማብቂያ ፍቅር ነው)፡፡

   በፍቅር በኩል አገላለጻችንን ሰንደግመው፤ መነሻ እርምጃ ብለን ኃጢአትን ለመጸየፍ የምንችለው እውነተኛ የእግዚአብሔር ፍቅር ሲኖረን ብቻ ነው፡፡ እንደ ሕፃናቱ በልብ ምሪት ስንሄድ!

   እግዚአብሔርን ያላፈቀረ ሰውነት ኃጢአትን መጥላት አይሆንለትም፡፡ ምክንያቱም ዓመፃ በመልኳ ውብ ናት፤ በጣም ቆንጆ! ይህንን ጉዳይ ከመጀመሪያቱ ሴት በበለጠ በሚገባ የሚያውቀው ያለ አይመስለኝም፡፡ እንዴት?

"ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነለዓይንም እንደሚያስጎመጅለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።" (ኦሪት ዘፍጥረት 3፥6)

   ሔዋኒቱ የዛፉን ፍሬ ከመቀንጠሷ በፊት ዛፉን አይታዋለች፡፡ ስታየው ደግሞ ያማረ፣ የሚያስጎመጅና ጥበብ ሰጪ ሆኖ ነው የታያት፡፡ በቀመደው ጊዜ ውስጥ በዔድን ጫካ መካከል ወዲህና ወዲያ ስትል ይህ እይታ አልነበራትም፡፡ "አማካሪው" መንፈስ ጠጋ ብሎ ካወያያት በኋላ ግን ቅርጫፎቹ ወዝተው፣ ፍሬዎቹ ተሽሞንሙነው፣ ቅጠሎቹ ቆንጅተው ታዯት፡፡ አበቃቀሉ ሳይቀር ሳባት፡፡ በዛ ላይ እንደሰማቺው ደግሞ እንደ አምላክ የሚያደርግ፤ ጥበብ ሰጪ ሆነባት፡፡ የምታየውና የምትሰማው ፍጹም እውነት መሰላት (ዛሬ እኛ እንደሚመስለን)፡፡ መቋቋም ተሳናት፤ ከሚያብለጨልጨው ፍሬ ወስዳ ቀጠፈች! (በኋላ ተቀጠፈቺበት እንጂ!)

   ኃጢአትን እንዳንጠላ፤ ዲያቢሎስ ኃጢአትን አስውቦ ያሳየናል (ኋላሳ፥ ቆንጆን ማን ይጠላል?)፡፡ በተጨባጭ ላለው የስሜት ሕዋሳችን የሚስማማ አድርጎ ዓመፃን ያለማምደናል፡፡ ቀላል ምሳሌ ልጥቀስ፡፡

   ከኑሮ ጉያችን ዘወትር የማትጠፋው ውሸት ኃጢአት እንደሆነች ሰምተንም ይሁን አንብበን እናውቃለን፡፡ "በሐሰት አትመስክር!" የሚል ሕግ እንዳለ ተምረናል፡፡ በገነቱ አነጋገር ዛፉን "አትንኩ!" ተብለናል (የጽድቅ ሕጎች ሁሉ ከዛፉ ክልከላ የወጡ ናቸው)፡፡ ነገር ግን ሐሰትን በባሕሪዩ የሚናገራት መንፈስ ዛፉን አስጊጦ ያሳየናል፡፡ ለመዋሸት የሚመቹ በቂ ምክንያቶችንና አጋጣሚዎችን ከፊታችን ያስቀምጥልናል፡፡ በዚህም ሳያበቃ ባሕሪያችንን ተጠግቶ ባሕሪዩን ያካፍልናል፡፡ አመለካከቱን ያጋራናል፡፡ የእርሱ እይታ ደግሞ ሁልጊዜ እንደርሱ "ከሰማይ ስፍራ የተለየ ነው"፡፡

    ውሸት ከዛፉ ፍሬዎች መካከል አንዷ ናት፡፡ ስለሆነ "አትናገራት!" ተብለናል፡፡ ግን አንችልም፤ ውሸት ውብ ነችና አንጠላትም፡፡ "ከእርሷ በተናገራችሁ ጊዜ ሥራው ይቃናል፤ ሐብት ይካብታል፤ ወዳጅ ይበረክታል፤ ዕድል ይከፈታል፤ ጨዋታ ይደራል፤ ስኬት ይቀላል" የሚል ስብከትን ዓለምና ሥርዓቷ በእጅ አዙር (አንዳንዴም በቀጥታ) ይሰብኩናል፡፡ ውሸት አንዴ ተገምጣ አታጠግብም፡፡ በየቀኑ ትርባለች፡፡ አልፎ ተርፎ ባልንጀሮቿ ግብዝነትን፣ ጉቦን፣ ሙስናን እና ሌሎቹንም ተራ በተራ ታስጎበኛለች፡፡ አንጠላት ነገር በውበቷ ታስደምማለች፡፡ ስትደመጥ ትጣፍጣለች፤ እንደ እውነት አትመርም፡፡

   የእባቡ ዓይን ያፈዛል፡፡ ዓመፃውን ያሳምራል፤ ውድቀቱን ለጊዜው ይሸፍናል፡፡ ዝሙትን የሚጠላት ማግኘት ይከብዳል፡፡ እስኪፈጽሟት ድረስ ታጓጓለች፡፡ ሐሴትን የምትለግስ ትመስላለች፡፡ በሥጋ ሲያዯት እንከን አያወጡላትም፡፡ መልክአ ኤዶምን የጻፉ ደራሲ ያሉት ትዝ አለኝ፦

"ዓለም እኮ የወደዳትን መልሳ ታጠፋዋለች፡፡  በወጥመዷም አስገብታ ብዙውን ሕዝብ በመርዟ እንደገደለች ይህን ሥራዋን የሚያውቅባት ከቶ እንደምን ያለ ብልህና አዋቂ ይሁን?"

   ዓለም ከሕይወት ብሌናችን ፊት ውበቷ የደመቀ ነው፡፡ ለጆሮም አትከብድም፡፡ መዝናኛዎቿና አኳኋኗ ሁሉ ቄንጠኛ ናቸው፡፡ ውደዱኝ በሚል ማባብያ ትቅለሰለሳለች፡፡ ፍቅር መሳይ ጥላቻ ግን ውስጧን ሞልቶታል፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2314

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Activate up to 20 bots Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared the group Tuesday morning on Twitter, calling out the "degenerate" community, or crypto obsessives that engage in high-risk trading. Telegram channels fall into two types: During a meeting with the president of the Supreme Electoral Court (TSE) on June 6, Telegram's Vice President Ilya Perekopsky announced the initiatives. According to the executive, Brazil is the first country in the world where Telegram is introducing the features, which could be expanded to other countries facing threats to democracy through the dissemination of false content. SUCK Channel Telegram
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American