BEMALEDANEK Telegram 2315
   ሥጋዊውን አኗኗር የሚቆጣጠረው ክፉ መንፈስ፤ የእርሱ ፈቃድና ምሪት ያለባቸውን ነገሮች ሁሉ ሲያቀርብልን ከጉድለታችን ትይዩ በመቆም ነው፡፡ ስለዚህ ኃጢአትን በመጠየፍ ንስሐ እንዳንገባ ከመኖር ሕልውናችን ውስጥ ያልተመለሱ ጥያቄዎችን፤ የተከለከልናቸው ትእዛዛትን፤ ያልደረስንባቸው ከፍታዎችን እንደ ውበት ማሳመሪያ ተጠቅሞ ኃጢአትን በማቆንጀት ያሳየናል፡፡ ኃጢአት መልከ መልካም ሆና ከታየች ደግሞ የእግዚአብሔርን ፍቅር ታኮስሰዋለች፡፡ ይህንን ጉዳይ መድኃኒቱ በአንድ ወቅት ሲናገር፦

"ከዓመፃም (ከኃጢአት) ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።" (የማቴዎስ ወንጌል 24፥12)

   ፍቅር የቀዘቀዘች እንደሆነ መንፈሳዊ ኑሮን እንድንመሠርት፤ ጉልበት፣ ጸጋ፣ ንቃትና ጽናት የምትሰጠን ንስሐ ጋር ለመድረስ የመነሳሳት አቅም እንኳ ያጥረናል፡፡ ምክንያቱም .. ፍቅር አልፋ (መነሻ)፥ ፍቅር ዖሜጋ (መጨረሻ) ስለሆነች!

   ንስሐ በአጭር ቋንቋ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ አድራሻ የመለወጥ መንፈሳዊ ጉዞ ነው፡፡ ወይንም በሮሜ መልእክት (12፥9) አጻጻፍ "ክፉውን ሁሉ በመጸየፍ ከበጎው ጋር መተባበር" ነው፡፡

   አንድ ሰው ንስሐ እንዴት ብዬ ልግባ ብሎ ሲጠይቅ፤ አስቀድመህ በኃጢአቶችህ ላይ ሁሉ ዓምፅ የሚል ቀጭን መልስ ሊያገኝ ይገባዋል፤ ዓመፃ ላይ ያላመፀ ሰው እግዚአብሔር ላይ ለማመፅ ቅርብ ነውና፡፡

   ሁሉም በሚል መጠቅለያ ለመደምደም በሚያስደፍር ገሐድ፤ ቆሻሻ የነካውን ልብስ ለብሶ ሠርግ መታደም አይፈልግም፡፡ ይቅርና ሠርግ ሰው የማያየንም ስፍራ ላይም ቢሆን ጸያፍ ነገር የነካው ልብስ መልበስ አንመርጥም፡፡ ግን በእግዚአብሔር ፊት አስቀያሚ የሆነውን የኃጢአት ድሪቶ ተሸክመን ስንመላለስ አንዳች አይከብደንም፡፡ ለምን? ተወዳጁን አባት ስለማንወደው!

   እግዚአብሔርን ያፈቀረ ልብ ኃጢአቶቹ ሁሉ ያጸይፉታል፡፡ እንደ መጥፎ ጠረን ይከረፉታል፡፡ እንደ ሰቅጣጫ ድምፅ ይሰቀጥጡታል፡፡ የዓመፃ ሰዓቶቹን ሲያስባቸው ይሰገጥጠዋል፡፡ እንዲህ ያለ ሥራ በአምላኩ ፊት መሥራቱን ባስተዋለ ጊዜ የሚያቃጥል እንባ ከጉንጮቹ ኮለል እያለ ይወርዳል፡፡ በልቡም ዘወትር ሳያቋርጥ ይዘምራል "ዓመፃን ጠላሁ ተጸየፍሁም፤ ሕግን ግን ወደድሁ" (መዝሙረ ዳዊት 119፥163) .. በቃ ንስሐ ማለት ይኸው ነው!

   ፍቅርን ባልቋጠረ ሕይወት ንስሐ እንግባ ብንል ኃጢአትን መጥላት አንችልም፡፡ ኃጢአትን ካልጠላነው፤ በዓመፃችን አንጸጸትም፤ ካልተጸጸትን አንናዘዝም! (እውነትም ፍቅር አልፋ.. )

   ያዕቆብ በመልእክቱ "እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል" ሲል የጻፈልን ይህንኑ ነው፡፡ በመለኮታዊ መውደድ ተንበርክከን ሳለ ዲያቢሎስን በመቃወም ልናሸሸው ይቻለናል፡፡ ማለትም ኃጢአትን በመጸየፍ ዓመፃን ከኛ ማራቁ ይሳካልናል፡፡

   ከዚህ ባሻገር ግን የኃጢአትን እስራት በጥሰን የጽድቅ ነጻነትን ልንቀዳጅ አንችልም፡፡ ዓመፃን ካልጠላናት ተውባ መታየቷን ትቀጥላለች፡፡ እኛም እየቀነጠስን መቋደሳችን እንዲሁ ይቀጥላል፡፡

"ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።" (ዝኒ ከማሁ)

   ንስሐን የሚጋርድ የኃጢአትን ውበት ለመግፈፍ የእግዚአብሔርን ፍቅር መነጽር ማድረግ ታላቅ መፍትሔ ነው፡፡ እኛ ወደርሱ በፍቅር ስንቀርብ እርሱ ደግሞ ወደኛ ከኛ ሁለት እጥፍ ተራምዶ ይቀርበናል፡፡ "ማንም ሰው አንድ ምዕራፍ ትሄድ ዘንድ ቢያስገድድህ ሁለተኛውን ከእርሱ ጋር ሂድ" ሲል የመከረ ጌታ፤ በአንድ የንስሐ ምዕራፍ ወደርሱ ስንጠጋ፥ ሁለት ምዕራፍ ከኛ ደርቦ መጥቶ አይጠጋንም ማለት ዘበት ነው፡፡ እርሱ ባያደርገው ኖሮ አድርጉት አይልም ነበርና፡፡ (የማቴዎስ ወንጌል 5፥41)

   ንስሐ መግባት እግዚአብሔርን የማፍቀር አንድ መገለጫ ነው፡፡ የምንወደውን ሰው አይደለም ስናሰቀይም ያስከፋነው ሲመስለን እንኳ እንጨነቃለን፡፡ በቶሎ አግኝተን ይቅርታ እስክንጠይቅ እንቸኩላለን፡፡ ከተፈቃሪውም የይሁንታ መልስ መቀበል ብቻውን ያስደስተናል፡፡ ይሄ ግን ለእግዚአብሔር አይሰጠውም፡፡ የፈጠረንን አምላክ ፍቅር ነፈግነው!

    በመሆኑም ፍቅር ባጣው እኛነታችን በኩል የጥላቻው መንፈስ የፍቅርን ካባ ደርቦ እየታየ፤ እንወድቅበት ዘንድ ሳር ወደከለለው ጉድጎድ አቅጣጫችንን ለመቀየስ ከፊታችን ቀድሞ በመሄድ መራን .. መራንና፤ በመጨረሻው ጊዜያችንን፣ አስተሳሰባችንን፣ ፍላጎታችንን፣ እውቀታችንን፣ ሥራችንን፣ ኑሮአችንን፣ ትውልዳችንን .. ሁሉ እንደርሱ የወደቀ አደረገው፡፡

    ኃጢአትን ያለ ቅድመ ሁኔታና ድርድር ለመፈጸም ሳንቸገር፤ ንስሐ ገብተን የቅድስና ፍሬን ለመስጠት ግን አያሌ ሰበቦችን እንደረድራለን፡፡ የመረጥነውን ድርጊትና ውሳኔ መከተላችንን በሚገባ እያወቅነው፤ ስለ ንስሐ በተወሳ ቁጥር "ልብ ይሰጠኝ" እያልን ሁለተኛ ልብ ፍለጋ ከራሳችን ዘወር እንላለን፡፡ አፈር የሚረግጥ ጫማችንን ሳንንቅ ወልውለን ነፍሳችንን ግን ከኃጢአት እድፍ ለመጥረግ በጣም ከበደን፡፡ አዎ .. በእርግጥም ከዓመፃ ብዛት የተነሣ የእግዚአብሔር ፍቅር ከውስጣችን ቀዝቅዛብናለች፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2315
Create:
Last Update:

   ሥጋዊውን አኗኗር የሚቆጣጠረው ክፉ መንፈስ፤ የእርሱ ፈቃድና ምሪት ያለባቸውን ነገሮች ሁሉ ሲያቀርብልን ከጉድለታችን ትይዩ በመቆም ነው፡፡ ስለዚህ ኃጢአትን በመጠየፍ ንስሐ እንዳንገባ ከመኖር ሕልውናችን ውስጥ ያልተመለሱ ጥያቄዎችን፤ የተከለከልናቸው ትእዛዛትን፤ ያልደረስንባቸው ከፍታዎችን እንደ ውበት ማሳመሪያ ተጠቅሞ ኃጢአትን በማቆንጀት ያሳየናል፡፡ ኃጢአት መልከ መልካም ሆና ከታየች ደግሞ የእግዚአብሔርን ፍቅር ታኮስሰዋለች፡፡ ይህንን ጉዳይ መድኃኒቱ በአንድ ወቅት ሲናገር፦

"ከዓመፃም (ከኃጢአት) ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።" (የማቴዎስ ወንጌል 24፥12)

   ፍቅር የቀዘቀዘች እንደሆነ መንፈሳዊ ኑሮን እንድንመሠርት፤ ጉልበት፣ ጸጋ፣ ንቃትና ጽናት የምትሰጠን ንስሐ ጋር ለመድረስ የመነሳሳት አቅም እንኳ ያጥረናል፡፡ ምክንያቱም .. ፍቅር አልፋ (መነሻ)፥ ፍቅር ዖሜጋ (መጨረሻ) ስለሆነች!

   ንስሐ በአጭር ቋንቋ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ አድራሻ የመለወጥ መንፈሳዊ ጉዞ ነው፡፡ ወይንም በሮሜ መልእክት (12፥9) አጻጻፍ "ክፉውን ሁሉ በመጸየፍ ከበጎው ጋር መተባበር" ነው፡፡

   አንድ ሰው ንስሐ እንዴት ብዬ ልግባ ብሎ ሲጠይቅ፤ አስቀድመህ በኃጢአቶችህ ላይ ሁሉ ዓምፅ የሚል ቀጭን መልስ ሊያገኝ ይገባዋል፤ ዓመፃ ላይ ያላመፀ ሰው እግዚአብሔር ላይ ለማመፅ ቅርብ ነውና፡፡

   ሁሉም በሚል መጠቅለያ ለመደምደም በሚያስደፍር ገሐድ፤ ቆሻሻ የነካውን ልብስ ለብሶ ሠርግ መታደም አይፈልግም፡፡ ይቅርና ሠርግ ሰው የማያየንም ስፍራ ላይም ቢሆን ጸያፍ ነገር የነካው ልብስ መልበስ አንመርጥም፡፡ ግን በእግዚአብሔር ፊት አስቀያሚ የሆነውን የኃጢአት ድሪቶ ተሸክመን ስንመላለስ አንዳች አይከብደንም፡፡ ለምን? ተወዳጁን አባት ስለማንወደው!

   እግዚአብሔርን ያፈቀረ ልብ ኃጢአቶቹ ሁሉ ያጸይፉታል፡፡ እንደ መጥፎ ጠረን ይከረፉታል፡፡ እንደ ሰቅጣጫ ድምፅ ይሰቀጥጡታል፡፡ የዓመፃ ሰዓቶቹን ሲያስባቸው ይሰገጥጠዋል፡፡ እንዲህ ያለ ሥራ በአምላኩ ፊት መሥራቱን ባስተዋለ ጊዜ የሚያቃጥል እንባ ከጉንጮቹ ኮለል እያለ ይወርዳል፡፡ በልቡም ዘወትር ሳያቋርጥ ይዘምራል "ዓመፃን ጠላሁ ተጸየፍሁም፤ ሕግን ግን ወደድሁ" (መዝሙረ ዳዊት 119፥163) .. በቃ ንስሐ ማለት ይኸው ነው!

   ፍቅርን ባልቋጠረ ሕይወት ንስሐ እንግባ ብንል ኃጢአትን መጥላት አንችልም፡፡ ኃጢአትን ካልጠላነው፤ በዓመፃችን አንጸጸትም፤ ካልተጸጸትን አንናዘዝም! (እውነትም ፍቅር አልፋ.. )

   ያዕቆብ በመልእክቱ "እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል" ሲል የጻፈልን ይህንኑ ነው፡፡ በመለኮታዊ መውደድ ተንበርክከን ሳለ ዲያቢሎስን በመቃወም ልናሸሸው ይቻለናል፡፡ ማለትም ኃጢአትን በመጸየፍ ዓመፃን ከኛ ማራቁ ይሳካልናል፡፡

   ከዚህ ባሻገር ግን የኃጢአትን እስራት በጥሰን የጽድቅ ነጻነትን ልንቀዳጅ አንችልም፡፡ ዓመፃን ካልጠላናት ተውባ መታየቷን ትቀጥላለች፡፡ እኛም እየቀነጠስን መቋደሳችን እንዲሁ ይቀጥላል፡፡

"ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።" (ዝኒ ከማሁ)

   ንስሐን የሚጋርድ የኃጢአትን ውበት ለመግፈፍ የእግዚአብሔርን ፍቅር መነጽር ማድረግ ታላቅ መፍትሔ ነው፡፡ እኛ ወደርሱ በፍቅር ስንቀርብ እርሱ ደግሞ ወደኛ ከኛ ሁለት እጥፍ ተራምዶ ይቀርበናል፡፡ "ማንም ሰው አንድ ምዕራፍ ትሄድ ዘንድ ቢያስገድድህ ሁለተኛውን ከእርሱ ጋር ሂድ" ሲል የመከረ ጌታ፤ በአንድ የንስሐ ምዕራፍ ወደርሱ ስንጠጋ፥ ሁለት ምዕራፍ ከኛ ደርቦ መጥቶ አይጠጋንም ማለት ዘበት ነው፡፡ እርሱ ባያደርገው ኖሮ አድርጉት አይልም ነበርና፡፡ (የማቴዎስ ወንጌል 5፥41)

   ንስሐ መግባት እግዚአብሔርን የማፍቀር አንድ መገለጫ ነው፡፡ የምንወደውን ሰው አይደለም ስናሰቀይም ያስከፋነው ሲመስለን እንኳ እንጨነቃለን፡፡ በቶሎ አግኝተን ይቅርታ እስክንጠይቅ እንቸኩላለን፡፡ ከተፈቃሪውም የይሁንታ መልስ መቀበል ብቻውን ያስደስተናል፡፡ ይሄ ግን ለእግዚአብሔር አይሰጠውም፡፡ የፈጠረንን አምላክ ፍቅር ነፈግነው!

    በመሆኑም ፍቅር ባጣው እኛነታችን በኩል የጥላቻው መንፈስ የፍቅርን ካባ ደርቦ እየታየ፤ እንወድቅበት ዘንድ ሳር ወደከለለው ጉድጎድ አቅጣጫችንን ለመቀየስ ከፊታችን ቀድሞ በመሄድ መራን .. መራንና፤ በመጨረሻው ጊዜያችንን፣ አስተሳሰባችንን፣ ፍላጎታችንን፣ እውቀታችንን፣ ሥራችንን፣ ኑሮአችንን፣ ትውልዳችንን .. ሁሉ እንደርሱ የወደቀ አደረገው፡፡

    ኃጢአትን ያለ ቅድመ ሁኔታና ድርድር ለመፈጸም ሳንቸገር፤ ንስሐ ገብተን የቅድስና ፍሬን ለመስጠት ግን አያሌ ሰበቦችን እንደረድራለን፡፡ የመረጥነውን ድርጊትና ውሳኔ መከተላችንን በሚገባ እያወቅነው፤ ስለ ንስሐ በተወሳ ቁጥር "ልብ ይሰጠኝ" እያልን ሁለተኛ ልብ ፍለጋ ከራሳችን ዘወር እንላለን፡፡ አፈር የሚረግጥ ጫማችንን ሳንንቅ ወልውለን ነፍሳችንን ግን ከኃጢአት እድፍ ለመጥረግ በጣም ከበደን፡፡ አዎ .. በእርግጥም ከዓመፃ ብዛት የተነሣ የእግዚአብሔር ፍቅር ከውስጣችን ቀዝቅዛብናለች፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2315

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart. Step-by-step tutorial on desktop: With the administration mulling over limiting access to doxxing groups, a prominent Telegram doxxing group apparently went on a "revenge spree." Healing through screaming therapy According to media reports, the privacy watchdog was considering “blacklisting” some online platforms that have repeatedly posted doxxing information, with sources saying most messages were shared on Telegram.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American